uz
Feedback
Werabe City Government Communication Affairs Office

Werabe City Government Communication Affairs Office

Kanalga Telegram’da o‘tish
2 909
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+37 kunlar
+2330 kunlar
Postlar arxiv
በወራቤ ከተማ አስተዳደር በ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም ዙሪያና ቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ትኩረት ያደረገ ከተማ ዓቀፍ የአመራር ዉይይት መድረክ ተካሂዷል! https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1294312526246991/?app=fbl

በወራቤ ከተማ አስተዳደር በ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ አፈጻጸም ዙሪያና ቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ትኩረት ያደረገ ከተማ ዓቀፍ የአመራር ዉይይት መድረክ ተካሂዷል! https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1294312526246991/?app=fbl

የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ተቋማት ከፖሊስ ጽ/ቤቶች ጋር በመቀናጀት ለነባር አሽከርካሪዎች የተሃድሶ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም በነገው ዕለት የሚሰለጥኑ አሽከርካሪዎች፦ የተሽከርካ
የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ተቋማት ከፖሊስ ጽ/ቤቶች ጋር በመቀናጀት ለነባር አሽከርካሪዎች የተሃድሶ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም በነገው ዕለት የሚሰለጥኑ አሽከርካሪዎች፦ የተሽከርካሪ ሰሌዳቸው/ታርጋ የመጨረሻው ቁጥር ሙሉ የሆነ ነገ እሁድ በቀን 07/10/2018 ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ መንጃ ፈቃድ እና መታወቂያ በመያዝ በወራቤ ከተማ ፓርክ አዳራሽ እንዲገኙ እናሳስባለን። ያለምንም ምክንያት ስልጠናውን ሳይወስዱ በመቅረት ቀጣይ እያሽከረከሩ በሚገኙ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን እናሳስባለን። የወራቤ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ከወራቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር

የከተማዉ ግብርና ጽ/ቤት የ2018/19 የምርት ዘመን የመኸር ወቅት የተቀናጀ ግብርና ልማት የንቅናቄ መድረክ አካሄደ! ሰኔ 06፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን] የወራቤ ከተማ አስተዳደር ግብርና ጽ/ቤት የ2018/19 የምርት ዘመን የመኸር ወቅት የተቀናጀ ግብርና ልማት የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ ለዉይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ በከተማ አስተዳደሩ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ በአቶ ጃፈር ጃቢር ቀርቦ ምክክር ተደርጓል። በምርት ዘመኑ የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት፣ ምርታማነትን ለማሳደግ እና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ ለማድረግ ያለመ እንደሆነም ነው የተገለጸው። መድረኩን የመሩት የወራቤ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ናስር ቡሽራ በእንስሳት ተዋጽኦ፣በከብት እርባታ እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች ትኩረት ሰጥቶ ከተሰራ ዉጤታማ መሆን እንደሚቻል በዘርፉ በከተማችን እየተሰሩ ያሉ የተለያዩ ጅምር ስራዎች አመላካች መሆኑን ተናግረዋል። የአርሶአደሩን ኑሮ በዘላቂነት ሊቀይር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎችን በመስራት ተጨባጭ ለዉጥ ማምጣት እንደሚገባም ዋና ተጠሪው አስገንዝበዋል። በከተማ አስተዳደሩ በቅመማ ቅመም ዘርፍ በተሰሩ ስራዎች ከፍጆታ አልፎ ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ጠቅሰዉ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የተሻለ ዉጤት ማምጣት ይገባል ነዉ ያሉት አቶ ናስር ቡሽራ። በሌላ በኩል የወራቤ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሻፊ ሙዜ እንደ ሀገር የተጀመሩ ዘርፈ-ብዙ የግብርና ልማት ስራዎችን በአግባቡ እንዲተገበሩ በማድረግ ብልጽግናን በቤተሰብ ደረጃ ማረጋገጥ ይገባል ። ከተለያዩ ቦታዎች የሚመጡ የግብርና ምርቶችን በአከባቢ ምርት ለመተካት በትኩረት መስራት እንደሚገባ ምክትል ከንቲባዉ አመላክተዋል። አቶ ሻፊ አክለውም አርሶአደሩን ከድህነት ለማዉጣትና ከተረጂነት ለማላቀቅ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በባለቤትነት በመምራት የሚታይ ለዉጥ ማምጣት ይጠበቃል ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጃፈር ጃቢር በበኩላቸው ከተማችን በሀገር ዓቀፍ የተጀመሩ የተለያዩ እንሼቲቮች ወደ ተግባር በመቀየር የተሻለ ዉጤት መምጣቱን ገልጸዋል። ገበያ ተኮር የሆኑ የግብርና ምርቶችን በስፋት በማምረት የማህበረሰቡን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ እና የገበያ መረጋጋትን መፍጠር እንደሚያስፈልግም አቶ ጃፈር አመላክተዋል።

የከተማዉ ግብርና ጽ/ቤት የ2018/19 የምርት ዘመን የመኸር ወቅት የተቀናጀ ግብርና ልማት የንቅናቄ መድረክ አካሄደ! ሰኔ 06፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን] የወራቤ ከተማ አስተዳደር ግብርና ጽ/ቤት የ2018/19 የምርት ዘመን የመኸር ወቅት የተቀናጀ ግብርና ልማት የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ ለዉይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ በከተማ አስተዳደሩ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ በአቶ ጃፈር ጃቢር ቀርቦ ምክክር ተደርጓል። በምርት ዘመኑ የተያዙ የልማት ግቦችን ለማሳካት፣ ምርታማነትን ለማሳደግ እና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ ለማድረግ ያለመ እንደሆነም ነው የተገለጸው። መድረኩን የመሩት የወራቤ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ናስር ቡሽራ በእንስሳት ተዋጽኦ፣በከብት እርባታ እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች ትኩረት ሰጥቶ ከተሰራ ዉጤታማ መሆን እንደሚቻል በዘርፉ በከተማችን እየተሰሩ ያሉ የተለያዩ ጅምር ስራዎች አመላካች መሆኑን ተናግረዋል። የአርሶአደሩን ኑሮ በዘላቂነት ሊቀይር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎችን በመስራት ተጨባጭ ለዉጥ ማምጣት እንደሚገባም ዋና ተጠሪው አስገንዝበዋል። በከተማ አስተዳደሩ በቅመማ ቅመም ዘርፍ በተሰሩ ስራዎች ከፍጆታ አልፎ ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ጠቅሰዉ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የተሻለ ዉጤት ማምጣት ይገባል ነዉ ያሉት አቶ ናስር ቡሽራ። በሌላ በኩል የወራቤ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሻፊ ሙዜ እንደ ሀገር የተጀመሩ ዘርፈ-ብዙ የግብርና ልማት ስራዎችን በአግባቡ እንዲተገበሩ በማድረግ ብልጽግናን በቤተሰብ ደረጃ ማረጋገጥ ይገባል ። ከተለያዩ ቦታዎች የሚመጡ የግብርና ምርቶችን በአከባቢ ምርት ለመተካት በትኩረት መስራት እንደሚገባ ምክትል ከንቲባዉ አመላክተዋል። አቶ ሻፊ አክለውም አርሶአደሩን ከድህነት ለማዉጣትና ከተረጂነት ለማላቀቅ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በባለቤትነት በመምራት የሚታይ ለዉጥ ማምጣት ይጠበቃል ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጃፈር ጃቢር በበኩላቸው ከተማችን በሀገር ዓቀፍ የተጀመሩ የተለያዩ እንሼቲቮች ወደ ተግባር በመቀየር የተሻለ ዉጤት መምጣቱን ገልጸዋል። ገበያ ተኮር የሆኑ የግብርና ምርቶችን በስፋት በማምረት የማህበረሰቡን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ እና የገበያ መረጋጋትን መፍጠር እንደሚያስፈልግም አቶ ጃፈር አመላክተዋል።

የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ በስርቆት ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ! ሰኔ 6፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን] የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ የተሽከርካሪ ጎማዎችን
+2
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ በስርቆት ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ! ሰኔ 6፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን] የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ የተሽከርካሪ ጎማዎችን ሰርቀው በቤት መኪና ጭነው በማምለጥ ላይ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በተደረገ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል። ተጠርጣሪዎቹ ንብረትነቱ የክልል ጤና ቢሮ እና የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የሆነን የተሽከርካሪ ጎማ ሰርቀው፤ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 2-አአ 69589AA በሆነ ኮሮላ/COROLLA የቤት መኪና ላይ ጭነው ሊያመልጡ ሲሉ ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ በተደረገው ክትትል የወራቤ ከተማ ፖሊስ፣ የሚቶ ወረዳ እና የላንፉሮ ወረዳ ፖሊስ እንዲሁም ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በተደረገ ቅንጅት የተሰረቁ ጎማዎችን እና ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል። መረጃውን ያደረሰን የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ነው

የወራቤ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት፣ የዳሎቻ ከተማና የዳሎቻ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ተቋማት፣ የሁልባራግ ወረዳ እና የአሊቾ ውሪሮ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤቶች ከፖሊስ ተቋማት ጋር በመሆን የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የአሽከርካሪዎች የተሃድሶ ስልጠና በወራቤ ከተማ እየሰጡ ይገኛሉ! https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1290717383273172/?app=fbl

የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የዞኑ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል በወራቤ ከተማ የወንዝ ዳርቻ ፓርክ ላይ የጃክፍሩት (Jackfruit) ተከላን አስጀምረዋል! https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1290807389930838/?app=fbl

በረካ የልማትና በጎ አድራጎት ማህበር ከአት-ተዓውን የዳዕዋና እስላማዊ አስተምህሮ ማህበር ጋር በመተባበር ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የተዘጋጀ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በወራቤ ከተማ ተሰጠ! https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1290989936579250/?app=fbl

#የፋይዳ_ፋይዳው_የጎላ_ነው! ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ/ፋይዳ በሀገራችን በይፋ ተግባራዊ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማግኘት ፋይዳ መታወቂያ መያዝ የግድ እየሆነ መ
+9
#የፋይዳ_ፋይዳው_የጎላ_ነው! ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ/ፋይዳ በሀገራችን በይፋ ተግባራዊ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማግኘት ፋይዳ መታወቂያ መያዝ የግድ እየሆነ መጥቷል፡፡ አገራችን የጀመረችው ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ /ፋይዳ/ ከመታወቂያነት ባለፈ ለሀገራዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ለዘመናዊ የኢኮኖሚ ስርዓት ግንባታ መሰረት ተደርጎ እየተሰራበት ሲሆን ከተለያዩ የስራ ዘርፎች ጋር እንዲተሳሰር በማድረግ አገልግሎቶች በዲጂታል መንገድ እንዲሳለጡ እየተደረገ ነው። የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ በከተሞች ሳይወሰን እስከ ገጠር ቀበሌ ድረስ በማውረድ ለአርሶ አደሩም ተደራሽ እየተደረገም ነው የሚገኘው። በዚህም በወራቤ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ ቀበሌዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ሰኔ 6፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]

የወራቤ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ማጠቃለያ ፈተና ፍጹም ሰላማዊ እና ስኬታማ በሆነ መልኩ ለመምራትና ለማጠናቀቅ የሚያስችል ለባለድርሻ አካላት ኦረንቴሽን ሰጥቷል! https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1290062776671966/?app=fbl

የወራቤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ በ20 ቀናት ዕቅዱ መሰረት እስካሁን የተከናወኑ ተግባራትን ከተጠሪ ተቋማት አመራሮች ጋር በመሆን ገምግሟል! https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1290048423340068/?app=fbl

አቲር ትምህርት ቤት ህፃናት ተማሪዎቹን የወራቤ ከተማ መዝናኛ ፓርክን አስጎበኘ! ሰኔ 5፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን] በወራቤ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው አቲር የግል ትምህርት ቤት የዩኬጂ ተመ
+9
አቲር ትምህርት ቤት ህፃናት ተማሪዎቹን የወራቤ ከተማ መዝናኛ ፓርክን አስጎበኘ! ሰኔ 5፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን] በወራቤ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው አቲር የግል ትምህርት ቤት የዩኬጂ ተመራቂ ተማሪዎቹን የወራቤ ከተማ የወንዝ ዳርቻ እና መዝናኛ ፓርክን አስጎብኝቷል። ህፃናት ተማሪዎቹ ፓርኩን ከመጎብኘታቸው ባሻገር የፓርኩ አካል በሆነው የህፃናት መጫወቻ ላይ ተዝናንተዋል።

4 ሚሊየን አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ እየታተመ ነው! የተለያዩ የደህንነት መስፈርቶችን ያሟላ 4 ሚሊየን አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ እየታተመ ነው አለ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር። በአዲስ አ
+1
4 ሚሊየን አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ እየታተመ ነው! የተለያዩ የደህንነት መስፈርቶችን ያሟላ 4 ሚሊየን አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ እየታተመ ነው አለ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ መሰጠት ጀምሯል። የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ አሰፋ ሀዲስ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳስታወቁት ÷ የተሽከርካሪ ሰሌዳው ወጥ፣ ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎችን ያከበረ እና አመሳስሎ ለመስራት ተጋላጭ ያልሆነ ነው። የተሽከርካሪ ሰሌዳው ዋጋ እንደ ተሽከርካሪው አይነት የሚለያይ መሆኑን ጠቁመው÷ የሰሌዳ ዋጋው የአገልግሎት ዘመኑን ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል። በግለሰብ፣ በብዙሃን ትራንስፖርት እና በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል ያለው የሰሌዳ ዋጋ የተለያየ መሆኑንም አንስተዋል። አማካሪው እንዳሉት÷ ለኤሌክትሪክ እና ለብዙሃን ትራንስፖርት የሰሌዳ ዋጋ ድጎማ ይደረግለታል። ይህ ሰሌዳ "ኪው አር ኮድ"፣ ማይክሮ ችፕስ እና ሌሎች የደህንነት መስፈርቶችን እንዲሁም የግለሰቦችን የሰሌዳ ፍላጎት ያሟላ እንደሆነም ጠቁመዋል። በአዲስ አበባ ከተማ አሁን ላይ 800 ሺህ ተሽከርካሪዎች ሲስተም ላይ ተመዝግበው እንደሚገኙ ተመላክቷል።(ኤፍ.ኤም.ሲ)

የወራቤ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ከከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት ከሰኔ 7/10/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለከተማው ነባር አሽከርካሪዎች የተሃድሶ ስልጠና ይሰጣል! የአሽከርካሪዎች ብቃት ማነስ፣ ከመጠን በላይ ፍጥነት፣ የግንዛቤ ማነስ፣ የእግረኞች የመንገድ አጠቃቀምና የተሽከርካሪዎች ቴክኒክ ብቃት መውረድ እንደዋነኛ የትራፊክ አደጋ መንስኤ ይጠቀሳሉ። በሚከሰቱ የትራፊክ አደጋዎች ምክንያት በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን የህይወት መጥፋት፣ የአካል መጉደልና የንብረት ውድመትና ሌሎች የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከልና ለመቀነስ የነባር አሽከርካሪዎች የተሃድሶ ስልጠና ወሳኝ ነው። በመሆኑም አጠቃላይ የትራፊክ አደጋ መንስኤዎችን ለመከላከልና በዘርፉ የሚስተዋሉ ጉድለቶችን ለማረም ዓላማ ያደረገ የተሃድሶ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን። የሚሰጠው ስልጠና ለህዝብ እና ለደረቅ ጭነት፤ ለግልና ለመንግስት አሽከርካሪዎች፣ ለባለ ሶስት እግር/ባጀጅ አሽካሪከሪዎች፦ የትራንስፖርት ደንብ መመሪያዎች፣ የተሽከርካሪ የቴክኒክ ብቃት፣ የአሽከርካሪዎች ስነ-ባህሪ፣ የትራፊክ ህግና ደንብ ጠብቆ ስለማሽከርከር፣ በሙያ ስነ-ምግባር ዙሪያ እና አደጋዎችን ተከላክሎ ማሽከርከር ላይ ትኩረት ያደርጋል። ታዲያ ማንኛውም የከተማችን አሽከርካሪዎች፦ የተሽከርካሪ ሰሌዳቸው ጎዶሎ ቁጥር የሆነ የፊታችን ቅዳሜ በቀን 07/10/2018 እንዲሁም የሰሌዳ/ታርጋ የመጨረሻው ቁጥር ሙሉ የሆነ ዕለተ እሁድ በቀን 08/10/2018 ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ መንጃ ፈቃድ እና መታወቂያ በመያዝ ስልጤ ዞን ባህል አዳራሽ እንዲገኙ እናሳስባለን። ያለምንም ምክንያት ስልጠናውን ሳይወስዱ በመቅረት ቀጣይ እያሽከረከሩ በሚገኙ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ከወዲሁ እናሳስባለን። የታሃድሶ ስልጠናን መውሰድ ግዴታ ከመሆኑም ባሻገር የመልካም አሽከርካሪዎች ስነ-ባህሪም ጭምር ነው። የወራቤ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ከወራቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ሰኔ 4፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]