Werabe City Government Communication Affairs Office
الذهاب إلى القناة على Telegram
Werabe Communication Social Media Links👇 @ https://m.facebook.com/Werabecommunication @ https://twitter.com/Werabecommu @https://www.werabecity.com
إظهار المزيد2 930
المشتركون
+424 ساعات
+167 أيام
+2930 أيام
أرشيف المشاركات
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አማካሪ አቶ አበበ ኤርቲሮ የተመራው ሱፐርቪዥን ቡድን በወራቤ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ተገኝቶ በተቋሙ ባለፉት 12 ወራት የተከናወኑ ተግባራት ላይ እና በ2019 የስራ ዓመት እቅዶች ዙሪያ ድጋፋዊ ክትትል አድርጓል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1312272134451030/?app=fbl
በወራቤ ከተማ አስተዳደር ከዋናው አስፋልት እስከ ኢቅራዕ አደባባይ ያለውን የአስፋልት መንገድ ዳር ኮሪደር ለማልማት ከተቋራጮች ጋር የውል ስምምነት በማድረግ የሳይት ርክክብና የስራ ማስጀመሩያ መርሃ-ግብር ተከናውኗል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1312249581119952/?app=fbl
"የልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ለማስፈጸም፣ የመሠረተ ልማት ሥራዎችን ለማስፋፋትና ለህብረተሰቡ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ይበልጥ ለማሻሻል የገቢ አቅምን ማሳደግ ያስፈልጋል"
አቶ ነስሬ አማን - የወራቤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ
❝የመረጃ አያያዝን ዲጂታላይዝድ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥን ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ተደራሽ ማድረግ ይገባል❞
አቶ ሻፊ ሙዜ - የወራቤ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት እና የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ጽ/ቤት በጋራ በመሆን የ2019 ዓ.ም የንግድ ሥራ ፈቃድ አሰጣጥ፣ እድሳት እና የሀምሌ ወር ገቢ አሰባሰብ ሥራዎችን በተቀናጀ እንቅስቃሴ ለማሳካት የውይይት መድረክ አካሂደዋል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1310355987975978/?app=fbl
"የጀመርነው ስራ ለኢትዮጵያም ለአፍሪካውያንም ምሳሌ ነው፤ ምሳሌ መሆን ግን ፍጻሜ ማለት አይደለም፡፡"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ጽ/ቤት የመረጃ አደረጃጀትና ልውውጥ ስርዓቱን ለማዘመንና ወደ ዲጂታል አሠራር ለማሸጋገር ያለመ ፕሮግራም አካሂዷል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1310251544653089/?app=fbl
+9
በወራቤ ከተማ መስማት የተሳናቸው የምልክት ቋንቋ ማስተማሪያ ማዕከል የ2018 የትምህርት ዘመን መዝጊያ ፕሮግራም አካሄደ!
ሰኔ 28፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
በወራቤ ከተማ የሚገኘው መስማት የተሳናቸው የምልክት ቋንቋ ማስተማሪያ ማዕከል የ2018 የትምህርት ዘመን የዓመቱን መዝጊያ ፕሮግራም አካሂዷል።
በተካሄደው የትምህርት መዝጊያ ስነ-ስርዓት ላይ በዓመቱ የላቀ ዉጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የማበረታቻ ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል።
በፕሮግራሙ የተገኙት የወራቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ያሲን ከሊል ባደረጉት ንግግር፡ ማዕከሉ መስማት ለተሳናቸው ወገኖች እያደረገ ያለው እገዛ የጎላ መሆኑን ገልጸው በቀጣይም ተደራሽነቱን ለማስፋት የሁሉም አካላት ድጋፍ እንደሚያስፈልግ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ማዕከሉን ለማጠናከር እና እራሱን ችሎ ትምህርት ቤት እንዲሆን ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር በመሆን በትኩረት እንደሚሰራ ከንቲባው አመላክተዋል።
በዝግጅቱ ላይ የወራቤ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ናስር ቡሽራ እና የማዕከሉ መስራች ወጣት ፈድሉ መሀመድን ጨምሮ የተማሪዎች ወላጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ሌሎችም አካላት ተገኝተዋል።
"እርካታ አደገኛ በሽታ ነው። በትንሹ የሚረኩ ሰዎች ማደግ አይችሉም። በትንሹ የሚረኩ ሰዎች ለልጆቻቸው የበለጠ የላቀ ነገር ማኖር አይችሉም"
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በወራቤ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ የግል ተቋማት መካከል የአርዲ ትምህርት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን ያስተማራቸውን 100 የኬጂ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1308625188149058/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ጽ/ቤት ከከተማው የፕሮጀክቶች ቴክኒክ ኮሚቴ ጋር በመሆን በፌደራል፣ በክልል፣ በዞንና በከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም በማህበረሰብ ተሳትፎ በመገንባት ላይ ያሉ የካፒታል ፕሮጀክቶችን በመስክ በመጎብኘት የድጋፍና የክትትል ስራ አከናውኗል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1307909044887339/?app=fbl
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ከህዝብ ክንፍ ጋር በመሆን የሴክተሩን የ2018 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም ገምግሟል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1307860031558907/?app=fbl
"ከተሞችን ፅዱ፣ አረንጓዴና ውብ በማድረግ የከተሞችን ብልፅግና እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል በከተሞች ፅዱና አረንጓዴ ልማት ላይ ያተኮረ ዞን አቀፍ የንቅናቄ መድረክ በወራቤ ከተማ ተካሂዷል!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1307764274901816/?app=fbl
+8
በወራቤ ከተማ አልከሶ ጤና ጣቢያ ተጨማሪ ግንባታ ለመገንባት የሳይት ርክክብ ተደረገ!
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ሰኔ 26፣ 2018 [ወራቤ ኮሙኒኬሽን] በወራቤ ከተማ አስተዳደር ጤና ጣቢያ ማስፋፊያ ተጨማሪ ብሎክ 5,157,337 ብር ለመገንባት የቦታ ርክክብ ተደርጓል።
የጤና ጣቢያውን አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ለማሻሻል የተጨማሪ ብሎክ ማስፋፊያ ግንባታ ጨረታ ካሸነፈው የግንባታ ስራዎች ተቋራጭ ከሆነው ከኢናያ እና ስፒል ግንባታ ስራዎች ተቋራጭ በዛሬው ዕለት በ5,157,337 ብር ውል በመግባት የሳይት ርክክብ ተደርጓል።
የሚገነባው ተጨማሪ ብሎክ የእናቶች ማቆያ ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
በርክክቡ ወቅት ንግግር ያደረጉት የወራቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ያሲን ከሊል፡ የተጨማሪ ብሎክ ግንባታው የጤና ጣቢያውን አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት የሚያሻሽልና በተለይም የእናቶችና ህጻናት ጤና አገልግሎቶች ጥራት የሚጨምር መሆኑን ገልጸው ግንባታው በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንዳለበት አሳስበዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ናስር ቡሽራ፣ የጤና ጽ/ቤቱ ኃላፊ የሆኑት አቶ ታጁዲን ሁሴን፣ የወራቤ ከተማ መዘጋጃ ቤት ኮንስትራክሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሀመድ ጁሀር፣ የአልከሶ ቀበሌ ዋና እስተዳደር አቶ አብዱረኡፍ ኪያርን ጨምሮ የኮንስትራክሽን ባለሙያዎች፣ የከተማው ፋይናንስ ጽ/ቤት ተወካይ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
+6
በወራቤ ከተማ የአረጋውያን የቤት ግንባታ መርሃ-ግብር ተጠናክሮ ቀጥሏል!
~~~~~~~~~~~~~~~
በወራቤ ከተማ አስተዳደር ፉጌ ቀበሌ በ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ-ግብር አካል የሆነው የአረጋውያን የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በመርሃ-ግብሩ መሠረት በፉጌ ቀበሌ ነዋሪ ለሆኑት ወ/ሮ ረሂማ አብዲላ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሥራ ተጀምሮላቸዋል።
በዕለቱም የመሩት የወራቤ ከተማ አስተዳደር ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ናስር ቡሽራ፣ የከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አህመድ ባሙድ ጨምሮ ሌሎችም አካላት ተገኝተዋል።
ሰኔ 26፣ 2018 [ወራቤ ኮሙኒኬሽን]
የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ዘይኔ ቢልካ በወራቤ ከተማ አስተዳደር እየተከናወኑ ባሉ ልዩ ልዩ የኢንቨስትመንትና መሰረተ ልማት ግንባታ እንቅስቃሴዎች ላይ የመስክ ምልከታ አካሂደዋል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1306276135050630/?app=fbl
