Werabe City Government Communication Affairs Office
الذهاب إلى القناة على Telegram
Werabe Communication Social Media Links👇 @ https://m.facebook.com/Werabecommunication @ https://twitter.com/Werabecommu @https://www.werabecity.com
إظهار المزيد2 947
المشتركون
-124 ساعات
+17 أيام
+2930 أيام
أرشيف المشاركات
የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ዘይኔ ቢልካ መልዕክት!
ተስፋን እንትከል - 800 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀምበር!
በሀገር ደረጃ ላለፉት ስምንት ዓመታት በተለያዩ መሪ ሀሳቦች በተከናወኑ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች በመላው ኢትዮጵያዊያን ንቁ ተሳትፎ በቢሊየኖች የሚቆጠሩ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያላቸው ችግኞች መትከል ችለናል።
ከአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሮች ባሻገር በተለያዩ ሀገራዊና አከባቢያዊ ንቅናቄዎች የተተከሉ ችግኞች የተፈጥሮን ሚዛን በማስጠበቅ፣ የአፈርና ውሃን ጥበቃ ስራዎችን በማገዝ፣ ምርታማነትን በማሳደግ፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥና የአካባቢን ውበት በማጉላት በኩል ከፍ ያለ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ።
በዚህም በተደጋጋሚ ጊዜያት በተካሄደው የችግኝ ተከላ የዞናችን፣ የክልላችን እንዲሁም የሀገራችን የደን ሽፋን ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሻሻለ ይገኛል።
"ተስፋ እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ እለት ሰኞ ሐምሌ 27/2018 የሚካሂደው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት በተቀናጀ ሁኔታ ሲካሄዱ የቆዩ ሀገራዊ ዘመቻዎች አካል ሲሆን በንቅናቄው በመላው ሀገሪቱ 800 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ቀን ለመትከል ግብ ተጥሏል።
በዞናችንም በሁሉም አከባቢዎች የሚደረጉ መርሃ ግብሮች እንደተጠበቁ ሆነው ዞናዊ ማስጀመሪያው በሁልባራግ ወረዳ አምበርቾ አጫሞና ዋጮ ኦብሶ ቀበሌያት መካከል በሚገኘው ዲኔና ገርባ ተፋሰሶች ላይ በከፍተኛ ንቅናቄ ይታወጃል።
ስለሆነም በመላው የዞናችን አካባቢዎች በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ነገ ሐምሌ 27/2018 ከጧቱ 12 ጀምሮ በየ አከባቢው በነቂስ በመውጣት ልክ እንደ ባለፈው ጊዜ የዚህ ታሪካዊ ንቅናቄ አካል እንዲሆንና አሻራውን እንዲያሳርፍ የከበረ ጥሪዬን አቀርባለሁ!
ዘይኔ ቢልካ - የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
ሐምሌ 26/2018 - ወራቤ
#ተስፋን_እንትከል🌱
በወራቤ በአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከ312 ሺህ በላይ ችግኝ ነገ ይተከላል!
ሐምሌ 26፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
በወራቤ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ ቀበሌዎች በአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከ312 ሺህ በላይ ችግኝ በነገው ዕለት ይተከላል።
አረንጓዴ አሻራ የአገራችንን አካባቢ ለመጠበቅ፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና ለቀጣይ ትውልድ አረንጓዴ ከተማ ለማስረከብ የሚካሄድ ሀገራዊ ልማት ነው።
❝ተስፋን እንትከል❞ በሚል መርህ በነገው ዕለት የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በወራቤ ከተማ አስተዳደር የሚካሄድ ሲሆን በዚህም ከ312,000 በላይ የተለያዩ ችግኞች እንደሚተከሉ ተገልጿል።
ችግኝ መትከል ዛሬን ከማስዋብ በላይ የነገን ህይወት መጠበቅ ነውና ሁሉም የከተማው የማህበረሰብ ክፍል በዚህ መርሃ-ግብር በንቃት በመሳተፍ አረንጓዴ፣ ውብ እና ለኑሮ ምቹ አካባቢ መፍጠር እንደሚገባ ከተማ አስተዳደሩ መልዕክት አስተላልፏል።
"አረንጓዴ አሻራ ለአሁኑ ትውልድ ሀብት፣ ለመጪው ትውልድ ምቹና ምርታማ አካባቢ ማቆየት ነው!"
የወራቤ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የመረጃ አያያዙን ለማዘመንና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ያስችል ዘንድ አዲስ ዌብ ፖርታል አበለጸገ!
ሐምሌ 25፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የመረጃ አያያዙን ለማዘመንና ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ያስችል ዘንድ አዲስ ዌብ ፖርታል አበልጽጎ በዛሬው ዕለት በይፋ ወደ ስራ አስገብቷል።
የከተማው ብልጽግና ፓርቲ የመረጃ አያያዙን በዘመናዊ መንገድ ለማደራጀት እና ሁል-አቀፍ ሥራዎችን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ያዘጋጀው አዲሱ የዌብ ፖርታል ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ እንደሚኖረውም ነው የተገለጸው።
ሀገራችን የጀመረችውን የዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ እውን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በተግባር ለማሳየትና በዘርፉ ውጤታማ ለመሆን የከተማው ብልጽግና ፓርቲ በተጨባጭ እየሰራ እንደሆነ ተገልጿል።
ፓርቲው ያበለጸገው አዲሱን የዌብ ፖርታል በቀላል መንገድ፤ በስልክ እና በኮምፒውተር መጠቀም የሚቻል ሲሆን የፓርቲውን ፖሊሲዎችን፣ መመሪያዎችን፣ ዘገባዎችን እና ሌሎች በርካታ መረጃዎችን የያዘ እንደሆነ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ከዚህ ቀደም የነበረውን አሰልቺ የመረጃ አያያዝን ወደ ዲጂታል ሲስተም የቀየረው ይህ የዌብ ፖርታል ስርዓት የፓርቲውን የውስጥ ስራዎች በእጥፍ የሚያቀላጥፍ፣ ጊዜና ገንዘብ የሚቆጥብ፣ የመረጃዎችን ጥራትና ደህንነት የሚያስጠብቅ ነው ተብሏል።
ዌብ ፖርታሉ በኢንቴል ሃብ ቴክኖሎጂ የበለጸገ ሲሆን የዚሁ ቴክኖሎጂ መስራችና ባለቤት ወጣት መንሱር ሀምዛ ስለ አዲሱ ዌብ ፖርታል ሰፊ ገለጻና ማብራሪያ ሰጥቷል።
ታዲያ የፓርቲውን ስራዎች ለማዘመን የዌብ ፖርታሉን በማበልጸግ ላደረጉት አስተዋጽኦ ለኢንቴል ሃብ ቴክኖሎጂስ መስራችና ባለቤት ለወጣት መንሱር ሀምዛ የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶለታል።
የፓርቲው ዌብ ፖርታል ሊንክ እንደሚከተለው ተመላክቷል
👉 www.werabeprosperity.org.et
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት "ከምርጫ ማግስት ጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ሀሳብ የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ ስራዎች ዕቅድ አፈጻጸም የማጠቃለያ መድረክ አካሂዷል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1331563935855183/?app=fbl
“ችግኝ እንተክላለን ስንል የሚበላ፣ ለመድኃኒት የሚውል፣ አካባቢን የሚያክም፣ ከተፈጥሮ ጋር የሚያስታርቅ ስራ እንሰራለን ማለታችን መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
+1
3️⃣ቀናት ቀሩት!
የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር
📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
#ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር
#PMOEthiopia #GreenLegacy
Werabe City Government Communication Affairs Office
የወራቤ ከተማ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ዘርፍ አብይ ኮሚቴ "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" ለመሸጋገርና የሰብዓዊ እርዳታ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት የእስካሁን አፈጻጸም ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የዉይይት መድረክ አካሄደ!
ሐምሌ 23፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
የወራቤ ከተማ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ዘርፍ አብይ ኮሚቴ "ከተረጅነት ወደ ምርታማነት" ለመሸጋገርና የሰብዓዊ እርዳታ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት የእስካሁን አፈጻጸም ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የዉይይት መድረክ አካሂዷል።
በመድረኩ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተሰሩ ስራዎች አፈፃፀም ሪፖርት እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም የቀጣይ ዕቅድ በከተማ አስተዳደሩ ግብርና ጽ/ቤት ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ስመኝ ገዛኸኝ ቀርቦ ዉይይት ተደርጎበታል።
ዜጎችን ከዕለት እርዳታ ጠባቂነት በማውጣት ወደ አምራችነትና ምርታማነት ለማሸጋገር የተሰሩ ስራዎች ተገምግመዋል።
በሴፍትኔት ልማት ፕሮግራም ተጠቃሚዎችንና ሌሎችንም የህብረተሰብ ክፍሎችን ከእርዳታ ጥገኝነት በማላቀቅ በዘላቂነት ራሱን እንዲችል ለማድረግና የምግብ ዋስትናን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ስራዎች ላይ መድረኩ ትኩረት አድርጓል።
የዉይይት መድረኩን የመሩት የወራቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ያሲን ከሊል: ወቅታዊ የዝናብ ሁኔታን ከግምት በማስገባት በአጭር ግዜ ዉስጥ የሚደርሱ የእህል አይነቶችን በመዝራት በተፈጥሮና በሌሎችም ሳቢያ የሚደርሱ አደጋዎችን ለመከላከል በቂ ዝግጅት ማድረግ ይገባል ብለዋል።
የአርሶ አደሩን የምርታማነት አቅምን በማሳደግ እና የአምራች ኃይሉን በቴክኖሎጂና በግብዓት በመደገፍ ወጥ የሆነ የባለሙያዎች ክትትል በማድረግ ምርትና ምርታማነትን መጨመር እንደሚገባም አቶ ያሲን ከሊል አመላክተዋል።
እንደ ከተማችን ከእርዳታና ከተረጂነት ጋር ተያይዘው ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ቁርጠኛ አቋም በመያዝ የተረጂነት አስተሳሰብ በመቅረፍ እና የመልማት አቅማችንን በመጠቀም ተረጂ ዜጎችን ወደ አምራችነት ለማሸጋገር በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየቱን ከንቲባዉ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የወራቤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ናስር ቡሽራ በከተማዉ ለሚደርሱ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ አደጋዎች በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት እንዲያስችለን ባዶ መሬትን ጭምር በማረስ፣ እህል በማሰባሰብ እና በማከማቸት አፋጣኝ ምላሽ የመስጠት አቅም ማጎልበት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
በዕዉቀት፣በቴክኖሎጂ እና በሌሎችም የድጋፍና ክትትል አግባብ በማጠናከር የአርሶአደሩን ምርታማነት ማሳደግ እንደሚያስፈልግ አቶ ናስር አክለዋል።
በከተማ የተለያዩ ቀበሌዎች ተጠቃሚዎች ተረጂነትንና ልመናን እንዲጠየፉ በማድረግ በተለይም በንብ ማነብ፣ በችግኝና ፍራፍሬ፣ በሰብል ልማት፣ በዶሮ እርባታ እና በሌሎችም መስኮች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን የተናገሩት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጃፈር ጃቢር ናቸዉ፡፡
#አረንጓዴ_አሻራ🌱
❝አረንጓዴ አሻራ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅኖን የሚቋቋም ግብርናና የግብርና ቤተሰብ መፍጠር ያስችላል!❞
የወራቤ ከተማ ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ ዓመት የህዝብ ፎረም አካሄደ!
ሐምሌ 23፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
የወራቤ ከተማ ጤና ጣቢያ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል እና ከህብረተሰቡ ጋር ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ የ2018 በጀት ዓመት የ4ኛ ሩብ ዓመት የህዝብ ፎረም መድረክ አካሂዷል።
በዕለቱም ባለፉት 12 ወራት በጤና ጣቢያው የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና የተመዘገቡ ስኬቶች ሪፖርት በጤና ጣቢያዉ ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ ሻሚል ባድሌ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በበጀት ዓመቱ የእናቶችና ህጻናት ጤና አጠባበቅ፣ የክትባት ተደራሽነት፣ የመድሃኒት አቅርቦት እና የህክምና አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል የተሰሩ ስራዎች በሪፖርቱ ተዳስሰዋል።
መድረኩን የመሩት የወራቤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ በህረዲን ሀሰን፡ ለወራቤ ጤና ጣቢያ ዞኑ ብሎም ክልሉ እየሰጠው ያለዉ ዕዉቅና የስራ ዉጤት መሆኑን አንስተው በመሪዎች ቆራጥነት ከተማው በሰጠዉ ትኩረት በበላሙያዎች እና በሌሎችም ድጋፍ የአገልግሎት አሰጣጡ እንዲሻሻል ተደርጓል።
የጤና ጉዳይ ለማንም የሚሰጥና የተወሰኑ አካላት ተግባር አለመሆኑን ያነሱት አቶ ባህረዲን የሁሉንም ማህበረሰብ የነቃ ተሳትፎና ርብርብ የሚፈልግ መሆኑን ተናግረዋል።
በቤተሰባችን ላይ እንዲደርስ የማንፈልገውን በሌሎች እንዲከሰት መፈለግ የለብንም ያሉት ሃላፊዉ እያንዳንዱ የጤና ባለሙያ ሙያዊ ስነ-ምግባርን በመላበስ ማህበረሰቡን በታማኝነትና በቅንነት ማገልገል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የከተማው ጤና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ታጁዲን ሁሴን በበኩላቸው በጤና ጣቢያዎች በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ጉድለቶችን ለማረም ያለመ መድረክ እንደሆነ ተናግረዋል ።
የዚህ መድረክ ዋና ዓላማ የጤና ጣቢያውን ተጠያቂነት ማረጋገጥና የተገልጋዩን ማህበረሰብ የህክምና አገልግሎቱን ደረጃ በደረጃ ማዘመን እንደሆነ የገለጹት አቶ ታጁዲን፥ በቀጣይም ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የአገልግሎት ክፍተቶች ለመሙላት በትኩረት እንደሚሰራም አመላክተዋል።
አቶ ታጁዲን ሁሴን አክለውም አዳዲስ ፕሮግራሞችን ተግባራዊ እያደረገ ያለ ጤና ጣቢያ መሆኑን በመግለፅ የሰዉ ሀይልና የህክምና መሳሪያ በማሟላት ወቅቱ የሚፈልገውን እና ዘመኑ የደረሰበትን ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጠናቀቀው ዓመት የማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት እና አጠቃላይ በጤናዉ ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆኑ ሲገለጽ በቀጣይም የተስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ የተሻለ ስራ መስራት እንደሚገባ ተመላክቷል።
የወራቤ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ በፐብሊክ ሰርቪስ ተቋም የሪፎርም ስራዎችና በካይዘን ትግበራ ላይ በሴክተሮች የመስክ ምልከታ አድርጓል!
https://www.facebook.com/100070047665762/posts/1329885739356336/?app=fbl
+7
በወራቤ ከተማ የአረጋውያን የቤት ግንባታ መርሃ-ግብር ተጠናክሮ ቀጥሏል!
ሐምሌ 23፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]
በወራቤ ከተማ አስተዳደር አንሸቤሶ ቀበሌ በ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ-ግብር አካል የሆነው ለሁለተኛ ዙር የአረጋውያን የመኖሪያ ቤት ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል።
በመርሃ-ግብሩ መሠረት በከተማው አንሸቤሶ ቀበሌ ዲያ ጢሶ መንደር ነዋሪ ለሆኑት ወ/ሮ ኢልፎ ረዲ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ስራ ተጀምሮላቸዋል።
በዕለቱም የወራቤ ከተማ አስተዳደር ሰረተኛና ማህበራዊ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድረህማን ሸመሀመድ፣ የአልከሶ 01 ቀበሌ ሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ነጃ ከድር እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ተወካይ ባለሙያዎች፣ በጎ ፈቃደኞች፣ የቀበሌው አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤን ከከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ጋር ያቀናጀው አዲሱ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ!
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብሯ አፈርን ከመጠበቅና የተጎዳ ሥነ ምህዳርን ከማከም ጀምሮ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤን ከከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ጋር ያቀናጀ አዲስ ስትራቴጂ እየተገበረች ትገኛለች።
ይህ ስትራቴጂ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትኩረት ተሰጥቷቸው በስፋት እየተተከሉ ባሉ እንደ ማካዴሚያ እና ኮኮነት ያሉ የኢኮኖሚ ተክሎች ይበልጥ እየተጠናከረ መጥቷል።
እነዚህ ተክሎች የኢትዮጵያን የግብርና መዋቅር በመቀየር ለዜጎች አስተማማኝ የገቢ ምንጭ፣ ለኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃ እና ለሀገር የውጭ ምንዛሬ ማግኛ ታላቅ ተስፋ ሆነው ብቅ ብለዋል።
በዓለም ገበያ ከፍተኛ ፍላጎት እና ዋጋ ያለውን ማካዴሚያ በስፋት ማልማት የሀገራችንን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ከማሳደግ ባለፈ የግብርና ምርትን የሚያሻሽል ትልቅ እርምጃ ነው።
ማካዴሚያ ለበርካታ ዓመታት ዘላቂ ገቢ የሚያስገኝ በመሆኑ፣ በተለይ ለባለ አነስተኛ ማሳ አርሶአደሮች የዕለት ተለት ኑሯቸውን ከማሻሻል ባለፈ ዘላቂ የሀብት ማፍሪያ መንገድ ይከፍታል።
ለአግሮ ኢንዱስትሪ ዘርፍም ግብዓት በመሆን በተለይ ለወጣቶች ሰፊ የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅም አለው።
በኢትዮጵያ ተስማሚ በሆነ ሥነ ምህዳር መልማት የጀመረው የኮኮነት ተክልም ዘይትን ጨምሮ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት አዲስ አቅጣጫ ያመላከተ ስትራቴጂያዊ ምርት ነው።
ኮኮነት ለምግብነት እንዲሁም የምግብ ዘይት እና ኮስሞቲክስን ጨምሮ በፋብሪካ ጥሬ ዕቃነት ከሚያስገኘው ትልቅ የፋይናንስ ፋይዳ ባሻገር ከፍተኛ መጠን ያለው የካርቦን ዳይኦክሳይድ ጋዝን በመሳብ አየር ንብረትን የማመጣጠን ልዩ ተፈጥሯዊ ጥቅም አለው።
ተክሉ የምግብ ዋስትና የማረጋገጥ ሂደትን ከማገዝ ባለፈ በኢንዱስትሪ ግብዓትነት የሚኖረው ድርሻ ሀገራዊ ጥገኝነትን የሚቀንስ ነው።
ሁለቱም ተክሎች የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመመከት ከሚደረገው ሀገራዊ ጥረት ጋር በቀጥታ የተሳሰሩ በመሆናቸው፤ አፈርን ከመሸርሸር በመጠበቅ፣ የከርሰ ምድር ውኃ መጠንን በመጨመር እና የአካባቢ ሙቀትን በመቀነስ በኩል የሚጫወቱት ሚና እጅግ የላቀ ነው።
ይህ አካሄድ የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በፅኑ መሠረት ላይ የሚያቆመው ሲሆን፣ ሀገራችን በምግብ ራስን ለመቻል እና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የምታደርገውን ጥረትም በልዩ ሁኔታ ያግዛል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ከተለመደ ችግኝ ተከላ ወጥቶ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እሴት ያላቸውን እንደ ማካዴሚያ እና ኮኮነት ያሉ ተክሎችን ማካተቱ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት ላመጣችው ትልቅ ለውጥ አንዱ ማሳያ ነው።(ኢቢሲ)
