en
Feedback
ዳዕዋ በወልቂጤ

ዳዕዋ በወልቂጤ

Open in Telegram

✅የሰለፎች ሚዲያ

Show more
1 201
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1530 days
Posts Archive
መስጂድ'ኮ አይመለክም ~ ለጭንቅ ለችግራችሁ የምትጠሩት ዶሪሕ እንኳን ለናንተ ሊደርስ ራሱንም ጎርፍ ወሰደው ስል "ከሰሞኑ ሳውዲ ላይ አንድ ትልቅ መስጊድ በዝናብ ምክንያት ተደርምሷል አንተ እንደምትለው ከሆነ እሱም የሱፍዮች ይሆን እንዴ?" ይለኛል። እኛ በእምነታችን መስጂድ ለጭንቅ ለችግር ይደርሳል ብለን የምናመልክ አይደለንም'ኮ ያ ሱፊ! እናንተ መስጂድ ታመልካላችሁ እንዴ? "አቅም አለው፤ አገር አቆራርጦ የተቸገረን ይረዳል፤ በቀብሩ ዙሪያ የሚሰበሰቡ ተማፃኞችን ጩኸት ይሰማል ይረዳል፣ ..." እያልክ የምታመልከው ሙታን ቀብር ላንተ ሊደርስ ቀርቶ ራሱንም ማዳን አልቻለም ስትባል "ሳውዲ ላይ አንድ ትልቅ መስጊድ በዝናብ ምክንያት ተደርምሷል" ትላለህ? ሳዑዲ ውስጥ መስጂድ ይመለካል ብለህ ነው እንዴ የምታስበው? ሳዑዲ ውስጥ የስንት አኢማ ቀብር አለ። ግን አይመለክም። የነብዩ ﷺ ቀብር አለ። ግን አይመለክም። እንዲያውም ፖሊስ አቁመው፣ አስተማሪ መድበው ነው የሚከላከሉት። ደግሞ እወቅ! እንኳን ሌላ መስጂድ ከዕባም በጎርፍ ተጠቅቶ እንደገና የተሰራበት ጊዜ አለ'ኮ። የከዕባ መጋረጃ የተቃጠለበት ጊዜ አለ። ከዕባ ለጭንቅ ለችግር ሊደርስ ቀርቶ ራሱን ማዳን ይችላል ብለንም አናምንም። ባጭሩ እኛ ከዕባን አናመልክም። እንዲያውም የተከበረው ሐጀረል አስወድንም አናመልክም። ይህንን ድንቅ ታሪክ ተመልከት። ታላቁ ሶሐቢይ ዑመር ብኑል ኸጧብ ረዲየላሁ ዐንሁ ወደ ሐጀረል አስወድ (ጥቁሩ ድንጋይ) በመቅረብ ከሳሙት በኋላ እንዲህ አሉ:- إِنِّي أَعْلَمُ أَنَّكَ حَجَرٌ لَا تَضُرُّ وَلَا تَنْفَعُ، وَلَوْلَا أَنِّي رَأَيْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يُقَبِّلُكَ مَا قَبَّلْتُكَ. “እኔ አንተን የማትጎዳ የማትጠቅም ድንጋይ እንደሆንክ አውቃለሁ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሲስሙህ ባላይ ኖሮ ባልሳምኩህ ነበር፡፡” [ቡኻሪ፡ 1597] [ሙስሊም፡ 1270] ቁልፉ ነገር ሙታን አታምልኩ ነው። "አናመልክም" እያሉ መዋሸት ራስን ማታለል ነው። በደንብ ነው ሙታን የምታመልኩት። ለጭንቅ ለችግር ሙታንን መማፀን አምልኮት አይደለም? የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦ "الدُّعَاءُ هُوَ الْعِبَادَةُ، قَالَ رَبُّكُمُ : {ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ}" "ተማፅኖ አምልኮት ነው። ጌታችሁ፡ {ለምኑኝ፤ እቀበላችኋለሁና} ብሏል።" [አቡ ዳውድ፡ 1479] ከዚህም አልፈው መቃብር ዘንድ በመሄድ ስለት የሚፈፅሙ፣ እርድ የሚያርዱ፣ ሱጁድ የሚወርዱ፣ ... ብዙ ናቸው። ስለዚህ "ሙታን አናመልክም" እያሉ በገሃድ የሚታየውን ነገር መሸምጥጥ ራስን መሸወድ ነው። የመካ ሙሽ ሪኮች እንኳ ማመሀኛ ይደረድራሉ እንጂ ማምለካቸውን አልካዱም። ቁርኣን ምስክሬ ነው። 1. {وَٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۦٓ أَوۡلِيَآءَ مَا نَعۡبُدُهُمۡ إِلَّا لِيُقَرِّبُونَآ إِلَى ٱللَّهِ زُلۡفَىٰٓ} "እነዚያም ከርሱ ሌላ ረዳቶችን የያዙት 'ወደ አላህ ማቃረብን እንዲያቀርቡን እንጂ ለሌላ አንገዛቸውም' (ይላሉ።)" [አዙመር፡ 3] 2. {وَيَعۡبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ مَا لَا يَضُرُّهُمۡ وَلَا يَنفَعُهُمۡ وَيَقُولُونَ هَٰٓؤُلَآءِ شُفَعَٰٓؤُنَا عِندَ ٱللَّهِۚ} "ከአላህም ሌላ የማይጎዳቸውን እና የማይጠቅማቸውን ያመልካሉ። 'እነዚህ አላህ ዘንድ አማላጆቻችን ናቸው' ይላሉም።" [ዩኑስ፡ 18] ይሄ የአጋሪዎቹ ማመሀኛ ዛሬም የሙታን አምላኪዎች ማመሀኛ ነው። እንጂ ጣኦቶቻቸው ከአላህ በታች እንደሆኑ ያምኑ ነበር። ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ እንዲህ ይላሉ፡- كَانَ الْمُشْرِكُونَ يَقُولُونَ: لَبَّيْكَ لَا شَرِيكَ لَكَ، قَالَ: فَيَقُولُ رَسُولُ اللهِ ﷺ: «وَيْلَكُمْ، قَدْ قَدْ» فَيَقُولُونَ: إِلَّا شَرِيكًا هُوَ لَكَ، تَمْلِكُهُ وَمَا مَلَكَ، يَقُولُونَ هَذَا وَهُمْ يَطُوفُونَ بِالْبَيْتِ “አጋሪዎቹ 'አቤት ለአንተ ተጋሪ የለህም' ይሉ ነበር። ይህን ሲሉ የአላህ መልእክተኛ ﷺ 'ወዮላችሁ በቃ በቃ!' ይሏቸው ነበር። እነሱ ግን 'የምትቆጣጠረው የማይቆጣጠርህ ላንተ የሆነ ተጋሪ ቢሆን እንጂ' ይላሉ። ይህን የሚሉት ከዕባን እየዞሩ (ጠዋፍ ሲያደርጉ) ነው።” [ሙስሊም፡ 1185] በሱፊያ ማደንዘዣ የተሸወድክ ወገኔ ሆይ! ንቃ! = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ጓደኛህ ማነው? ~ ጓደኛህ ወደ ተሻለ የምትወስደው ወይም ወደተሻለ የሚወስድህ ይሁን። ካልሆነ ግን ወይ ያጠፋሀል። ወይ ታጠፋዋለህ። ወይ ተያይዛችሁ ትጠፋላችሁ። ሰው ውሎውን ይመስላል። ውሎህ የት ነው? ከማን ጋር? ሰዎች ጠጪ የሚሆኑት በጓደኛ ሰበብ ነው። ቃሚ፣ አጫሽ የሚሆኑትም በጓደኛ ተፅእኖ ነው። ያለ ምክንያት አይደለም "ጓደኛህን ንገረኝና ማንነትህን ልንገርህ" የሚባለው። ከመጥፎ ሱስ መውጣት፣ ባህሪህን መግራት ትፈልጋለህ? ከልብህ ከሆነ ውሎህን አስተካክል። ልጅህ ከመጥፎ አዝማሚያ እንዲመለስ፣ መስመር እንዲይዝልህ ትፈልጋለህ? ሰበብ ሳታደርስ ጠዋት ማታ አትጨቃጨቅ። ይልቁንም ውሎው ላይ አጥብቀህ ስራ። ካልሆኑ ጓደኞች ጋር ገጥሞ ከሆነ የምትችለውን ሁሉ መስዋእትነት ከፍለህ ለየው። ለብዙዎች በዲንም ይሁን በዱንያ መቃናት መልካም ጓደኛ ትልቅ ድርሻ አለው። እስኪ በህይወት ጉዟችሁ ላይ አነሰም በዛ ላገኛችሁ ስኬት ወይም መልካም ለውጥ አስተዋፅኦ ያላቸውን ጓደኞቻችሁን ለአፍታ አስቧቸው። በተቻለ መጠን ውለታ መላሽ ሁኑ። እሱ ቢቀር አመስጋኝ ሁኑ። ከዚያም በላይ በዱዓእ አስታውሷቸው። ጓደኝነት ኣኺራን ከነጭራሹ ሊያጨልም፣ ኩ. ፍ. ር ላይ ሊጥል ይችላል። በጓደኛ ሰበብ ስንቶች ለተረዱት እውነት እጅ መስጠት አቅቷቸዋል?! በጓደኛ ሰበብ ስንቶች ውስጣቸው እያወቀ እምነት ቀይረዋል? ስንት ወንዶች ሴት ተከትለው፤ ስንት ሴቶችም ወንድ ተከትለው ዘላለማዊ ህይወታቸውን አጨልመዋል?! የተሰጠን እድል ከእጃችን ሳያፈተልክ፣ ነፍሳችን ሳትሾልክ በፊት ሳይመሽ እናስብበት። እንወስን በጊዜ። ነገ ፀፀት እንዳይበላን። ጌታችን እንዲህ ይላል:- { وَیَوۡمَ یَعَضُّ ٱلظَّالِمُ عَلَىٰ یَدَیۡهِ یَقُولُ یَـٰلَیۡتَنِی ٱتَّخَذۡتُ مَعَ ٱلرَّسُولِ سَبِیلࣰا (27) یَـٰوَیۡلَتَىٰ لَیۡتَنِی لَمۡ أَتَّخِذۡ فُلَانًا خَلِیلࣰا (28) لَّقَدۡ أَضَلَّنِی عَنِ ٱلذِّكۡرِ بَعۡدَ إِذۡ جَاۤءَنِیۗ وَكَانَ ٱلشَّیۡطَـٰنُ لِلۡإِنسَـٰنِ خَذُولࣰا (29) } {በዳይም፡ «ምነው ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በሆነ ዋ ምኞቴ!» እያለ (በጸጸት) ሁለት እጆቹን የሚነክስበትን ቀን (አስታውስ)። «ዋ ጥፋቴ! ምነው እገሌን ወዳጅ አድርጌ ባልያዝኩ ኖሮ። (የእምነት ቃልን) ከመጣልኝ በኋላ ከማስታወስ በእርግጥ አሳሳተኝ» (ይላል)። ሰይጣንም ለሰው በጣም ለውርደት አጋላጭ ነው።} [አልፉርቃን፡ 27-29] (ኢብኑ ሙነወር፣ ግንቦት 2/2016) = የቴሌግራም ቻናል :- https://t.me/IbnuMunewor

አዲስ ተከታታይ ደርስ ⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯ «الأخلاق الإسلامية» ☞ኢስላማዊ ስነ_ምግባሮች ! ⊰ ክፍል  03 ⊱√الأمانة  !  √ አማናን መወጣት !የኪታብ 𝐩𝒅𝐹 ❜ t.me/abu_reyyis_arreyyis/9559 🎙በአቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም t.me/abu_reyyis_arreyyis/9592

አዲስ ተከታታይ ደርስ ⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯ «الأخلاق الإسلامية» ☞ኢስላማዊ ስነ_ምግባሮች ! ⊰ ክፍል  02 ⊱√ الألفة !  √ መግባባት  !የኪታብ 𝐩𝒅𝐹 ❜ t.me/abu_reyyis_arreyyis/9559 🎙በአቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም t.me/abu_reyyis_arreyyis/9579

አዲስ ተከታታይ ደርስ ⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯⎯ «الأخلاق الإسلامية» ☞ኢስላማዊ ስነ_ምግባሮች ! ⊰ ክፍል 01 ⊱ ⓵√ الإحسانበጎ መዋል !!የኪታብ 𝐩𝒅𝐹 ❜ t.me/abu_reyyis_arreyyis/9559 🎙በአቡ ረይስ ሙሀመድ ኢብኑ ኢማም t.me/abu_reyyis_arreyyis/9566

مختصر موسوعة الأخلاق.pdf13.73 MB

#ግጥም1 •ማረኝ ጌታየ ሆይ!! 🎙በ ኡስታዝ፦ሙሓመድሲራጅ  ተገጥሞ፤በ ወንድም አቡ ሱፍያን ድምፅ የቀረበ― t.me/+CL_1nL1UHLFhZjU8

+2
ውሸት - አስከፊው ወንጀል ! ወደ አላህ መንገድ እንጣራለን እያሉ መዋሸት ... ! https://t.me/Muhammedsirage

☞«ማንም ጋር  በገባበት ልንገባ  በወጣበት ልንወጣ  የህይወት ዘመን ዉል የለንም። መንሀጅ ያገናኘናል::  መንሀጅ ይለያየናል:: መንሀጅ ከለያየን  ከትላንት ቀርቶ ከዛሬ ወዳጅም ጋር እነለያያለን  :: መንሀጅ   ካገናኘን  ዛሬ  ከምንርቃቼዉ  አካላት ጋር  እጅ ለእጅ ተያይዘን  እንጓዛለን  :: መለኪያችን የሰለፊያ  መንሀጅ  ብቻ ነዉ «ትላንት አንድ የነበርን  የተለየናቼዉ አሉ :: ትላንት  ተወጋግዘን ዛሬ ከልብ የምንወዳቼዉ  ብዙ ናቼዉ  ።አላህ በሰለፍያ ላይ ያፅናን :: ከኢብኑ መነወር ወርቃማ ንግግሮች አጥጋቢ ንግግር አልተረዳችሁም ? =          t.me/asselfya

የኹጥባ አቀራረባችን ምን መምሰል አለበት.? 🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዘሁላህ         t.me/Darutewhide

ኹጥባ የሱና ደረጃ https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/6485
ኹጥባ የሱና ደረጃ https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/6485

+1
አሁን ላይ ብዙ ነገሮች በቴክኖሎጂ ምክንያት ቀለዋል ቀልቦች ግን ደፍርሰዋል ከደርስ የተቆረጠ አጭር ምክር ሙሐመድ ሲራጅ ሙ/ኑር https://t.me/MedrestuImamuAhmed https://t.me/Muhammedsirage

ለበይክ አላሁመ ለበይክ ~ ሐጅ የኢስላም ልዩ መስህብ የሚሰተዋልበት፣ ድንቅ የአላህ ተዐምር የሚታይበት፣ የተውሒድ ነፀብራቅ ጎልቶ የሚነግስበት፣ ባእድ አምልኮ ከፍ ባለ ድምፅ ባደባባይ የሚወገዝበት ድንቅ ስርአት ነው። ሴት ወንዱ፣ ነጭ ጥቁሩ፣ መሪው ተመሪው በተመሳሳይ ቦታ እኩል ለአላህ የሚሰለፍበት ትንግርት። ሐጅ - አምስተኛው የኢስላም ምሰሶ። በሐጅ "በሰዎችም ውስጥ በሀጅ ትእዛዝ ተጣራ" ለሚለው የአላህ ጥሪ “ለበይክ አላሁመ ለበይክ፣ ለበይከ ላሸሪከ ለከ ለበይክ፣…” /አቤት ጌታችን ሆይ አቤት፣ አቤት ጥሪህን ተቀብለን መጥተናል/” እያሉ መልስ በመስጠት ሚሊዮኖች ይተማሉ። * ከዚያ ጭው ካለ በረሃ “ከአላህ ሀገራት ሁሉ ይበልጥ አላህ ዘንድ የተወደድሽ ነሽ። ከአላህ ሀገራት ሁሉም እኔ ዘንድ የተወደድሽ ነሽ። ህዝቦችሽ ካንቺ ባያስወጡኝ ኖሮ አልወጣም ነበር” የሚለውን የነብዩን ﷺ የቁጭት ንግግር፣ አሜኬላ የበዛበት ህይወታቸውን ልበዎ በሀዘን እየተከፈለ ያስታውሳሉ። * ከዚያ ጭው ካለ በረሃ አስራ አራት ክፍለ-ዘመናት ወደ ኋላ አጠንጥነው የተውሒድ ጮራ ሲፈነጥቅ በአይነ-ህሊናዎ ይመለከታሉ። * ከዚያ ጭው ካለ በረሃ የመካ ሙሽ - ሪኮችን ለከት የለሽ ጭካኔና የነዚያን ፈርጥ የሆኑ ሰሐቦች ከብረት የጠነከረ ፅናት እያሰቡ በትዝታ ይነጉዳሉ። * ከዚያ ጭው ካለ በረሃ የነ ቢላልን ስቃይ፣ የነ ሱመያን የጣር ድምፅ አይነዎ እንባ እያቀረረ በሰመመን ያያሉ። ልበዎ በቁጭት እየደማ ይሰማሉ። * ከዚያ ጭው ካለ በረሃ የአላህ የመጀመሪያ ቤት አለ - የሙስሊሞች ቂብላ፣ ከአለም ሁሉ ምርጡ ቦታ፣ መካ። إِنَّ أَوَّلَ بَيْتٍ وُضِعَ لِلنَّاسِ لَلَّذِي بِبَكَّةَ مُبَارَكًا وَهُدًى لِلْعَالَمِينَ (96) فِيهِ آيَاتٌ بَيِّنَاتٌ مَقَامُ إِبْرَاهِيمَ وَمَنْ دَخَلَهُ كَانَ آمِنًا "በርግጥም ለሰው ዘር (መፀለያ) ሆኖ መጀመሪያ (ምድር ላይ) የተኖረው ቤት ያ በበካህ (በመካ) ያለው የተባረከና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ የሆነው ነው። በውስጡ (እንደ) የኢብራሒም መቆሚያ (ያሉ) ግልፅ የኾኑ ተዓምራቶች አልሉ። ወደ ውስጡ የገባም ሰው ደህንነቱ የተጠበቀ ሆኗል።" [ኣሊ ዒምራን፡ 96] - መስጂደል ሐራም መጤው ካገሬው እኩል የሚሆንበት ተአምራዊ ቦታ። የተውሒድ ቦታ፣ የእዝነት ቦታ። የኢብራሂም፣ የሐጀር፣ የኢስማዒል ትዝታ። - መስጂደል ሐራም በረከት የበዛበት፣ ሰላም የሰፈነበት፣ እዝነት የነገሰበት፣ ተውሒድ የፈነጠቀበት ቅዱስ ቦታ። - መስጂደ ልሐራም ልቦች ዘወትር የሚናፍቁት፣ አይኖች አይተውት የማይጠግቡት፣ ያላዩት ሊያዩት የሚቋምጡት ድንቅ ቦታ። - መስጂደል ሐራም! “የማያውቁት ሀገር አይናፍቅም” የሚለው ሀገርኛ ብሂል ፉርሽ የሚሆንበት ልዩ መስህብ። ለካስ ይናፍቃል! ደካማ አዛውንቶች በሽተኞች ሳይቀሩ ህመም ድካማቸውን ረስተው፣ ስቃይ እንግልቱን ዘንግተው፣ ባላዩት ሀገር ናፍቆት ተብሰክስከው፣ እልፍ አእላፍ ማይሎችን አቋርጠው ይተማሉ። وَإِذْ بَوَّأْنَا لِإِبْرَاهِيمَ مَكَانَ الْبَيْتِ أَنْ لَا تُشْرِكْ بِي شَيْئًا وَطَهِّرْ بَيْتِيَ لِلطَّائِفِينَ وَالْقَائِمِينَ وَالرُّكَّعِ السُّجُودِ "ለኢብራሂምም የቤቱን (የካዕባን) ስፍራ መመለሻ ባደረግንለት ጊዜ “በኔ ምንንም አታጋራ፣ ቤቴንም ለሚዞሩትና ለሚቆሙበት ሩኩዕ ሱጁድ ለሚያበዙት ንፁህ አድርግላቸው” (ባልነው ጊዜ አስታውስ)።" [አልሐጅ፡ 26] ከዕባ፣ ሐጀረል አስወድ፣ መቃም ኢብራሂም፣ ሶፋና መርዋ፣ ሚና፣ ዐረፋ፣ ሙዝደሊፋ፣… የሙስሊሞችን ቀልብ የሚማርኩ ልዩ የዒባዳ አውድማዎች ናቸው። ተልቢያ፣ ጦዋፍ፣ ሶላት፣ ዱዐ፣ እርድ፣ የጠጠር ውርወራ፣… ለፈፀማቸው ቀርቶ ለተነገረው የሚያጓጉ ሐጅ ላይ የሚፈፀሙ፤ ተቅዋን የሚያላብሱ የዚያኛው ዓለም ስንቆች ናቸው። (ذَلِكَ وَمَنْ يُعَظِّمْ شَعَائِرَ اللَّهِ فَإِنَّهَا مِنْ تَقْوَى الْقُلُوبِ) ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ሐዲሥ አላህ አድሎት የተዋጣለት ሐጅ ያደረገ እናቱ ስትወልደው እንደነበረው እንደ ህፃንነቱ ከወንጀል ሙሉ በሙሉ እንደሚፀዳ ነው መልእክተኛው ﷺ ያመላከቱት። በሐጅ ልቦች በኢማን ይታደሳሉ፣ አማኞች ከወንድሞቻቸው ጋር ይተዋወቃሉ፣ ደካሞች ይታገዛሉ፣ ሙስሊሞች ከቅዱሱ ስፋራ፣ ከበረሃው፣ ከሐጁ ስርአት፣ ከተዳሚው ሁኔታ፣ ከዚያ የሚሊዮኖች ስብሰባ ብዙ ተፈኩር ይወስዳሉ። አላህ አድሎት የሐጅ ስነ-ስርኣት ላይ ለተካፈለ ሰው ልብሳቸው የበሰበሰ፣ ሰውነታቸው የኮሰሰ፣ ኑሮ ያጎሳቆላቸው ስንት አይነት ሰዎችን ከተለያዩ የአለም አፅናፋት ታድመው ይመለከታል። አንዳንዶቹ ለዘመናት አጠራቅመው ለዚህ ስኬት እንደበቁ ሲቃ እየተናነቃቸው ይናገራሉ። በተሽከርካሪ ወንበር የሚገፉ፣ በጀርባ የታዘሉ አዛውንቶችን ሲመለከቱ፣ አቅሙም ጤናውም ተሟልቶ ከሐጅ ስለቀረው ወገን በእጅጉ ያዝናሉ። ሐጅ የወጀበባችሁ ወገኖቼ ሆይ! ጤናን አቅምን ያደላችሁ ጌታ፣ ሐጅን ግዴታ አድርጎባችኋል። ወንድሞቼ እህቶቼ፣ አባቶቼ እናቶቼ ሆይ! ለአላማ እንደተፈጠራችሁ አትዘንጉ። የተሰጣችሁ ገንዘብ ያንን አላማ ማሳኪያ እንጂ መጎረሪያም መባከኛም አይደለም። ሐጁን ብትፈፅሙት ጥቅሙ ለራሳችሁ ነው። ወንጀላችሁ ይረግፋል፣ ልባችሁ ይፀዳል፤ የዒባዳ ወኔያችሁ ይነሳሳል። እመኑኝ አንዴ ቆርጣችሁ ከፈፀማችሁት በያመቱ ገና ጊዜው ሲቃረብ ነው ልባችሁ የሚቆመው። “ወዴት” እንዳትሉኝ። ወላሂ ስንቶች ናቸው ሐጅ አጠናቀው መካን ሲለቁ፣ በእንባ የሚታጠቡት! ባትፈፅሙትስ ማነው የሚጎዳው? በርግጠኝነት አላህ ምንም አይቀርበትም! መቼስ ከሚታረደው እርድ አይደርሰው ነገር! ያበላል እንጂ አይበላምና። ከፍጡር ሁሉ የተብቃቃ ጌታ ነውና። وَلِلَّهِ عَلَى النَّاسِ حِجُّ الْبَيْتِ مَنِ اسْتَطَاعَ إِلَيْهِ سَبِيلًا وَمَنْ كَفَرَ فَإِنَّ اللَّهَ غَنِيٌّ عَنِ الْعَالَمِينَ "ለአላህም በሰዎች ላይ ወደርሱ መሄድን በቻለ ሁሉ ላይ ቤቱን መጎብኘት ግዴታ አለባቸው። የካደም ሰው አላህ ከዓለማት ሁሉ የተብቃቃ ነው።" [ኣሊ ዒምራን: 97] ዱዓቶች ሆይ ሰዎችን ቀስቅሱ። አላህ የጣለባችሁን ሀላፊነት አድርሱ። ተሳክቶላችሁ በናንተ ሰበብ አንድ ሰው ለሐጅ ቆርጦ ቢነሳ የሚኖራችሁን አጅር አስታውሱ። ወገን ወደ ግራም ወደ ቀኝም ተመልከት። ከራሳችን፣ ከቤተሰብ፣ ከጎረቤት ብዙ ሐጅ ያላደረጉትን ፍቀድ። ዘንድሮ ባይደርስ ለቀጣይ አስታውስ። "አስታውስ ማስታወሱ አማኞችን ይጠቅማልና።" [አዛሪያት፡ 55] ባይሆን አደራ! ለሐጅ ቆርጠው ከተነሱ፡- በሚገባ ይዘጋጁ። ስለሐጅ ይጠይቁ፣ ይወቁ፣ ያንብቡ፣ የሚያነቡትም ይያዙ። ከተቻለም ቀድሞ ሐጅ ያደረገ የዲን ግንዛቤ ያለው ሰው ጓደኛ ማድረገዎን አይርሱ። "ወደ ኸይር ያመላከተ (ኸይሩን) እንደሚሰራው ሰው ነው (አጅሩ አለው)" ይላሉ ነብዩ ﷺ። ለበይክ አላሁመ ለበይክ ለበይከ ላሸሪከ ለከ ለበይክ ኢነል ሐምደ ወኒዕመተ ለከ ወልሙልክ ላሸሪከ ለክ! . ያ ረሕማኑ ቤትህን ለመጎብኘት አንተ ወፍቀን። (ኢብኑ ሙነወር፣ ጳጉሜ 3/2006) = የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor

የሸይኽ ሙሐመድዘይን አደም ትምህርቶች በ pdf 1- የኪታቡን ስም መጫን፣ 2- Open የሚለውን መጫን፣ 3- Chrome ፣ Telegram ... ሲመጣ ቴሌግራምን መምረጥ። ቀጥታ ወደ ደርሱ ያመራል።

ወደኸኝ እንጂ አትውሰደኝ ! ወንጀሌ የበዛ የአላህ ባሪያ መሆኔ ሲታወሰኝ የወዳጅ ውዳሴም ሆነ የጠላት ዘለፋ  ከንቱ መሆኑ የበለጠ ፍንትው ብሎ ይታየኛል ! ፈጣሪየ አላህ ሆይ! የወንጀል ሸክሜ የገዘፈብኝ ደካማ ባሪያህ ነኝና ይቅር በለኝ ! በሰራሁት አትያዘኝ ! ቀልቤንና ስራየን አጽድተህልኝ እንጂ ሞቴን አታምጣው! ወደኸኝ እንጂ አትውሰደኝ ! https://t.me/Muhammedsirage