en
Feedback
Diinii kee Anaakara (Md Ali)

Diinii kee Anaakara (Md Ali)

Open in Telegram

دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol

Show more
1 611
Subscribers
+224 hours
+87 days
+1430 days
Posts Archive
Repost from Kassis Faage
Janaaza elle kaqlisan inna! ⤵️⤵️⤵️ https://t.me/Kassisfaage

🎞 ከክርክር ራስን ማራቅ በሸይኽ ኢልያስ አህመድ (ከ 30 ምክሮች) https://youtu.be/jmEiUeI_ssM?si=vJ9K4obeU5EQh-RR

✍️Yalli cakki cakkiinot yableeh, katya mara nee abay! 🤚Baatil baatiliinot yableeh, kak yaxxeere mara nee abay!! ✍️Md Ali

ትምህርት ቅንጦት አይደለም ~ ያ ኡመተል ኢስላም! ልጆችህን ትምህርት አስተምር። ካልሆነ ግን በገዛ ምድርህ ባይተዋር ትሆናለህ። ካልሆነ ግን ሌላው በተቋም እና በመዋቅር ሲዋጋህ አንተ በለቅሶ ነው የምትከላከለው። ካልሆነ ግን በገዛ ቀየህ ላይ "የእስላም አገሩ መካ፣ የአሞራ አገሩ ዋርካ" ይተረትብሃል። ካልሆነ ግን ግብር የምትከፍልበት ተቋም የምትወገርበት ዱላ ይሆናል። ካልሆነ ግን ለሚደርስብህ መድሎና መገለል ምላሽህ ለቅሶ ብቻ ይሆናል። ካልሆነ ግን መብትህን የምታገኘው ሌሎች ሰፍረው ለክተው በሚሰጡህ መጠን ብቻ ይሆናል። ካልሆነ ግን በአስተማሪነት፣ በሰራተኝነት በሚመጡ አካላት በገዛ ቀየህ ላይ የባህል ወረራ ይፈፀምብሃል። ማንነትህ ይደባለቃል። አለመማር አንድምታው ብዙ ነው። አላስተምርም ካልክ ሚሽነሪ ገብቶ ልጆችህን በትምህርትና በጤና አገልግሎት ስም ይወስድልሃል። እነ ላጲሶ የሚሸነሪ ሰለባዎች ናቸው። አላስተምርም ካልክ ሴረኛ ፖሊሲዎችና ደንቦች እየተረቀቁ ከንግዱ ሴክተር ሳይቀር በካልቾ ትባረራለህ። አላስተምርም ካልክ ታሪክህን እያወላገደ፣ እምነትህን እያንጋደደ ለሚያጠለሽ አካል ቦታውን ትለቃለህ። አለመማር በጤናው፣ በፀጥታው፣ በአስተዳደሩ፣ ... ሴክተር የሚኖረው ክፍተት ከምናስበው በጣም የራቀ ነው። በዚህ ዘመን በስልኩ የተላከለትን መልእክት የማያነብ፣ የሰፈሩ አጥር ላይ የተለጠፈን ማሳሰቢያ የማያውቅ፣ ባንክ ቤት ገብቶ ስሙን መፃፍ አቅቶት ሰው የሚጠብቅ ወጣት ማፍራት እጅግ አደገኛ ነገር ነው። አስተምር ልጆችህን። በትምህርት ተቋማት ውስጥ ያሉ ችግሮችን ልጆችህን በማራቅ አትፈታቸውም። እያስተማርክ ታገል። ጎን በጎን ክፍተቶችን በራስህ በቤትህ ወይም ተደራጅተህ ሙላ። ብታስተምር ይሻልሃል! ልጆችህን አስተምር። በተለያዩ የዓለም ጫፎች የምንሰማቸው ሙስሊሞች ላይ የሚደርሱ ግፎች አንዱ ምክንያታቸው የተራቀቁ ቴክኖሎጂዎችን እና ጠላትን መገዳደር የሚያስችሉ ዘመኑን የዋጁ የጦር መሳሪያዎችን ማምረት ላይ ስለሌለን ነው። እነዚህ ቴክኖሎጂዎችና የተራቀቁ የጦር መሳሪያዎች ደግሞ የዘመናዊ ትምህርት ውጤቶች ናቸው። ጠላት እጅግ አውዳሚና ጅምላ ጨራሽ፣ አህጉር አቋራጭ መሳሪያ እስከ አፍንጫው ታጥቆ ሳለ አንተ በኮንትሮባንድ ያገኘኸውን ጥቂት ክላሽንኮቭ ይዘህ እንገጅ እንገጅ ብትል ውጤቱ የትም የማይደርስ ሰሞንኛ መፈራገጥ ብቻ ነው የሚሆነው። ባጭሩ ስለ ትምህርት ሲወራ ስለ ቅጥር እንጀራ ብቻ አናስብ። የመማር ትርጉሙ ከዚያ ያለፈ ነው። ስለ ትምህርት ሲወራ ከአንድ ከሁለት አቅጣጫ ብቻ መልከት አይገባም። መማርም፣ አለመማርም ተጽእኗቸው መልኩም አይነቱም ብዙ ነው። በሚያሳዝን ሁኔታ አካባቢያችን፣ ወገናችን ከሌሎች በትምህርት ወደ ኋላ እንዳይቀር እንዴት የተሻለ ስራ እንስራ በሚል ልንመካከር በሚገባን ጊዜ ከፊሉ ገና የመማርን አስፈላጊነትና ያለመማርን አደጋ ለመረዳት ማገዶ እየፈጀ ነው ያለው። (ትንሽ ተነካክቶ በድጋሜ የተለጠፈ) = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

Matara‼ Daqwa gexsittam qimbisseh ustaaz Qabdulqhaadir Ibraahim Arac: samarak kaxxa masjiidi (100 qarwah gari) Afar Kassis Me
Matara‼ Daqwa gexsittam qimbisseh ustaaz Qabdulqhaadir Ibraahim Arac: samarak kaxxa masjiidi (100 qarwah gari) Afar Kassis Media

Daqwa qimbisnam fanxa, annihim siiniiy? Arac samarak kaxxa masjid (100 qarawah gari)

Beerih Acaadah samaral kaxxa masjiidil daqwa anele. Dr. Idiriis ismaaqil edde anuuk daqwal ustaazitte geytimele. Maraaqina.

"Nanu mawliid akah assakaxxe waynam macaay?" #shekh_qali_qabdalla https://youtube.com/watch?v=-zB_5uB7DmY&si=TTvAaaU5fquNQwg5

د. محمد النووي 45.m4a14.00 MB

3 Essero Mawliid yassakaxxe maral esserna. 1) Mawliid Akah abtaanam yallih taaqat inna? Maqsiyataay? Yallih maqsiyata inteenik toh uma gitaay tooba abtaanam siinik faxxinta. Yallih taaqatah abna inteenik: 2) Yallih farmoyti (q.s.w) yeexegeh inna? Maaxiginnaay? Yallih farmoyti (q.s.w) yeexegemeh inteenik toh kufrinna. Wonna hinnay yallih farmoyti yeexegeh inteenik geeri essero ciggiilisna. Yeexegeh inteenik 3) Isi ummatta gudduyseh inna? Magudduysinnaay? Magudduysinnaay isi ummattah mawarsinna yooqoreh ikkah inteenik kaadu toh kufrinnah sinam bahtaama. Macah yalli isi nabiyyiki يَٰٓأَيُّهَا ٱلرَّسُولُ بَلِّغۡ مَآ أُنزِلَ إِلَيۡكَ مِن رَّبِّكَۖ وَإِن لَّمۡ تَفۡعَلۡ فَمَا بَلَّغۡتَ رِسَالَتَهُۥۚ “ A-farmoytaw (Nabii Mucammad kinnuk) ku-Rabbik wacyih kol obsimtem Sinam guddus atu ku-Rabbih farmo guddussam abe waytek dagom takke way, toysa kay farmo magudduysinnito” kaak iyye. Gudduuse weeh woo risaalat yooqoreh yeneki yalli guddus kaak iyyeeh wohu khiyaanat deqsittaah yallih farmoyti (q.s.w) khiyaanat le yaanamaay, wohu kaadu kufrinnak exxa yallih farmoyti (q.s.w) khiyaanat le yaanam. Wonna hinnay usuk yeexegehiiy gudduyseh inteenik قُلْ هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ Siinik inna. Baahay elle gudduyseh yan ikke qhur'aan kee cadiisik siinik inna. Dr. Macammad Cuseen (محمد ويعسى) xongoloy kutbrh korisne. Afar Kassis Media

1) Shekh Macammad Awwal Cayaat ....saqal 2) Dr. Macammad Cuseen..... ciggiila saqal 3) Shekh Saadiqh Cuseen..... kutbaabeena Akkuk doorimen Afar Kassis Media

Qafár rakaakayak taama selta makaado inki xongolol faaticisen. 1) Shekh Macammad Awwal Cayaat 2) Dr. Macammad Cuseen 3) Shekh
Qafár rakaakayak taama selta makaado inki xongolol faaticisen. 1) Shekh Macammad Awwal Cayaat 2) Dr. Macammad Cuseen 3) Shekh Saadiqh Cuseen 4) Shek seqid Qabdulqhaadir 5) Shek Qabdul qaziiz muheyta 6) Shek Qumar noor Qali 7) Shekh Macammad Saalic Qabdalla Federaal Awlaytu Shekh Macammad Acmad Yaasiin Afar Kassis Media

Qafar rakaakayak majlisul Aqla qusba majlis elle xissiimu waa gud gud qimbisseh geytinta. አፋር ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክሪ ቤት መስረታ መካሄድ
+2
Qafar rakaakayak majlisul Aqla qusba majlis elle xissiimu waa gud gud qimbisseh geytinta. አፋር ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክሪ ቤት መስረታ መካሄድ ጀመረ Afar Kassis Media

د. محمد النووي 45.m4a14.00 MB

ከልጅነት ትዝታዎቼ! እያንዳንዳችሁ የዱንያን ቀርቶ የግል ሕይወታችሁን መለዋወጥ እንኳን በሚገባ ካስተዋላችሁ! የዱንያ ሁኔታዎቿ ከጊዜ ወደጊዜ የመለዋወጡ ነገር በጣም ያስገርማችኋል።ለምሳሌ እኔና ጓደኞቼ ከሀያ ምናምን አመታት በፊት በለውሕ አሊፍ፣ባ፣ታ ከትበን ቀርተን «ኢቅረዕ እና አመ» ስንደርስ እናቶቻችን የማዳ(ማዒዳ)ሰደቃ አውጥተውልን፣ቁርዓንን በለፍዝ ስናኸትም ደግሞ እነ አባዬ አርደው ሰደቃ አውጥተውልን ያሳለፍንበት ዘመን ነበር።አሁን ሁል ነገር በገር በገር ሆኖም የማይቀራ ብዙ ትውልድ ኣለ፣ቀርቶ አኽትሞም ከምንም አይቆጠርም።በተቃራኒው በ KG ተማሪዎች ምርቃት ሀገር ይቀወጣል። የምንጫማው ጫማ ሳይኖረን በባዶ እግራችን ከቆላ ደጋ፣ከሀሪማ ወደ ሀሪማ፣ለቂራዓት፣ለመውሊድ፣ለለቅሶ...ወዘተ ለምነን እየበላን፣ምንም በማናውቃቸው ቤተ-ሰቦች ቤት ደረሳነት ቁጭ ብለን እየጦሩንና እየቀለቡን ያለፈውን ሁኔታ ዞር ብዬ ሳስበው፣የሕዝቡ ባለ-ዕዳዎች እንደሆንን ይሰማኛል።አሁን ግን ደረሳ የሚቀልበው ቁጥሩ አናሳ ነው፣ደረሳም ብር ካልተከፈለው አያስቀራም። አይ ዱንያ! መሻይኾች በመቶዎች የሚቆጠር ደረሳ ሲያስቀሩ ምንም ዓለማዊ ጥቅም ጠይቀው አያውቁም ነበር።ደረሶችም በኢልም ጥንካሬ እንጂ በልብስና ጫማ ብሎም በሞባይል አይፎካከሩም ነበር።ኪታብ ሳይቀር በመድ ተበጥብጦ ነስኽ እየተደረገ ነበር የሚቀራው። የድሮው ጊዜ ሌላኛውና የማያስደስተው ክፍሉ ግን፦ በደረሳነት ብዙ አመታትን እያሳለፍንም ስለ ተውሂድ ምንም አለማወቃችን፣ስለ ሱናም ሆነ ሀዲስ ሰምተን አናውቅም።ቁርዓን በተጅዊድ አይቀራም፣ተፍሲሩም በመጨረሻ የደረሳነት ደረጃ ነካ ነካ ብቻ ይደረጋል፣እሱም በሙተከሊሞች አካሄድ።ከዝያ ባለፈ ቁርዓንን በቁርዓን፣በሀዲስ፣በኣሳሩ-ሰለፍ መፈሰር ያልተለመደ ነበር። በተለየ መልኩ ትኩረት የምንሰጠው ለጧትና ማታ አውራድ፣በየ ዛውያውና ሀድራው የሚቀሩ መንዙማዎችን ስለ መሸምደድ፣የመሻይኾችንና መሻይኾቻቸውን ፈድል ስለ መዘርዘር...በእነርሱም ሆነ ሪጃሉላሂ ተብለው በሚነገሩን ተወሱል ስለማድረግ...፣ይሄንን ነው በትኩረት የምትከታተለው።ይሄንን ያልኩት ለምሳሌነት ያህል እንጂ ቢፃፍ መፅሐፍ ይወጣዋል ወላሂ።ግን በፊቅሂ፣በነህው፣በሷርፍ፣በመንጢቅ...ወዘተ ጠንከር ያሉ ብዙ ደረሶች ይኖራሉ። ሁሌ ግን እያስታወስኩት የሚያስቀኝን አንድ ወይም ሁለት ገጠመኝ ላውጋችሁ፦ አንዴ የዳንጌው ሸይኽ ሶስተኛ(ሸይኽ አብዱልባሪ አላህ ይርሀማቸውና) ወደ ሻማ ሜዳ ለዚያራ በመጡበት (የሀጂ ሳዲቅነቴ ባርዛፈ የፈለጢ ወክተ) የሻም ሸኽ ልጅ በሬ አርዶ መውሊድ አውጥቶ ነበር፣ታሪኹ ያኔ የተከሰተ ነው። መውሊድ የወጣ ማታውን በጣም የነሸጠው መሻይኽና ደረሳ የሞቀ መንዙማ ተቀምጦ ጀመረና ከመረቀነ ቦኋላ ሁሉም ተነስቶ ቆመ።እኛ ልጆች ስለሆንን ከዋና ተዋናይነት በበለጠ ለወደፊቱ ልምድ ለመቅሰም ከዳር ሆኖ መመልከት ይቀለናል።መንዙማው (ሰለላሁ አለይከ ወሰለም አለይከ ወኣሊከ ወሰሃበቲከ) ወይም ራሱ በመሃል እየተቀየረ (ሰለላሁ ወሰለም አለኑሪልአዕዘም ወኣሊሂ ወሰህቢሂልአክረም) የሚል ነው። በዝህ ሁኔታ በነሻጣ ጡዘት ውስጥ ከገባው ደረሳ መካከል አንዱ በጣም ነሽጦ እራሱን ሳተ፣በሌላ አገላለፅ (ሀራራ ወሰደውና ወደቀ) አስተግፊሩላህ!።ሕዝቤ መንዙማ ጨርሶ ተመልሶ ቢቀመጥም ባለ ሀራራው ራሱን ስቶ በወደቀበት መንዙማውን መለፈፍ አላቆም ኣለ።ውሃ ቢረጭበት፣ለማነፋፈስ ብያራግቡ፣ልብሱ ቢወልቅ፣ወይ ፍንክች...በመጨረሻም አቅሙ ሲደክም ራሱ ባትሪ ጨረሰና እንደ እንቅልፍ አሸለበው።በሂደትም ቀስ እያለ ነቃ። አቤት እኛ እንዴት እንደቀናንበት! ተበርቼ ሰላም። በቃ ጀነት የተመሰከረለት ነው የመሰለን! ምን ያህል ተቂይ ቢሆን ነው ሀራራ የወሰደው? እያልን። ግማሹ ሄዶ ይተሻሸዋል፣ከፊሉ ከመውሊዱ ስጋ የተወሰነ ያጎርሰዋል፣ሌላው መንቃቱን ለማረጋገጥ የት ነው ያለነው? ይለዋል። አስባችሁታል ይሄንን የተሰውፍ እብደት?! አልሀምዱሊላህ የሱናን ኩታ ላለበሰን አላህ፣ቁርዓንን እንደወረደ በወረደበት ስፍራ የመቅራትን እድል ላጎናፀፈን፣በሱና አኑሮ በርሷ እንዲወስደንም በርሱ መልካም ስሞቹና ባህሪያቱ ተወሱል አድርገን እንለምነዋለን። ኢንሻአላህ ይቀጥላል። ©: Mukemil Kemal Abdellaah