Diinii kee Anaakara (Md Ali)
Open in Telegram
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
Show more1 609
Subscribers
No data24 hours
+47 days
-530 days
Posts Archive
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
ምክር ለባለ ትዳሮች‼
===============
✍ ትዳር ውስጥ የተሟላ ትክክለኝነት (ምንም ጎደሎ የሌለበት perfection) አትጠብቁ።
ምንም ጎደሎ የሌለባት ሙሉ የሆነች ሚስት አትገኝም።
ምንም ጎደሎ የሌለበት ሙሉ የሆነ ባል አይገኝም።
በተቻለ መጠን መቻቻል፣ መቀራረብ፣ አንዱን በአንዱ ማሟላት ነው እንጂ!
ሁሉንም ነገር ቀጥ አድርጌ አስኬዳለሁ ካልክ አትችልም፤ እንደማትችል ዲንህ ነግሮሃል። ቀጥ አደርጋለሁ ስትል ትሰብረዋለህ፤ መስበሩ ደግሞ መፋታት ነው።
የሚሻለው ከትዳር አጋራችሁ አንዳች ነገሩን/ሯን ብትጠሉ፤ ሌላ ሰው ላይ የሌለ ሌላ የምትወዱላቸው ነገር በርግጠኝነት ይኖራል። ስለዚህ አንዱን -Ve በሌላው +Ve እያተካካችሁ ነፃ ሰው (ኔውትራል) ሆናችሁ በሰላምና በፍቅር የትዳር ህይዎታችሁን ምሩ።
#علمني_ديني:
أنه لا توجد زوجة صالحة كاملة، لا عيب فيها و لا نقص،
و لا يوجد زوج صالح كامل، لا عيب فيه و لا نقص.
فسددوا وقاربوا.
عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: "لَا يَفْرَكْ مُؤْمِنٌ مُؤْمِنَةً، إِنْ كَرِهَ مِنْهَا خُلُقًا رَضِيَ مِنْهَا آخَرَ" أَوْ قَالَ: «غَيْرَهُ» أخرجه مسلم حديث رقم (1469).
#محمد_بازمول
||
t.me/MuradTadesse
Repost from قناة تعليم التجويد والقراءات (باللغة العفرية)
Assalaamu qaleykum Waracmatullaahi wabarakaatuhMeqe toobokoy aham Qhur-aan tajwiid kee qhiraa-aat baritto elle gexsitta faageega kinni massakaxxaay kunnabna luk katattaanam sin kassisna #addâ fakootu:- 👇👇👇 1️⃣ ummaan sabtii kee caadah laqot kak asan baritte live (online) telegiramal gexsita #Link👉 https://t.me/qhuraantajwid 2️⃣ Muhimmik tan qunxa qunxa video Tiktok gabbeelol (golil) #Link👉 https://www.tiktok.com/@siraj.hummo.nur?_t=8sF16P2fwgw&_r=1 3️⃣ inkih tan kaxxa video kee addâ fakoot YouTub gabbeelol (golil) #Linki 👉https://youtube.com/@shn09p?si=XvkwsIIdQaOFzeKV 4️⃣ feerayso (kutbee) kee dagoo dagoo video Facebook gabbeelol (golil) #Linki👉 https://www.facebook.com/sirajhummo.nur.9
"Mogo"
[Repost, qagu]
★ Assalaamu Qaleykum
Waracmatullaahi
Wabarakaatuh
[ >>>>>>>>><<<<<<<<<<<<]
★ Naharsi saaku mogo quukaanam kaxxam gibdim kinnim dagoom muduqqa siinih heeh suge.
★ Asaaku jumqatta elle abeh an masjidil imaam khutba " mogo" wagsiisak nee kassiise(Meqe Jaza Yalli kaah yaaxagay ).
★ Anu khutba edde yabbateemit inkih miyabnammay, baxsaluk sidiica ximmo kak kassiisam gibbateyyo(Insha Allaah).
① Ibnu Qumar (R.qanhum) baahe xaagul, Meqe NABI ﷺ " Yallih gital jihaadah rabe numuh Yalli zambitte inkih cabah mogo kak raqtay immay" iyye. Muslim xaagise.
② Abuu qhatada (R.qanhu) baahe xaaguk, iyyaamah "Inki saaku Meqe NABI ﷺ jihaadah rabaanamaay, Yallal yaaminenim Yallih garil kaxxam muxxolem kinnim kassiisak suge.
Tokkel inki sacaabiti sollayeh " Yallih farmoytaw (ﷺ) anu Yallih gital jihaadah rabek, Yalli anu abe zambitte inkih yoh cabelee?" iyye.
~ Tokkem Meqe NABI ﷺ " yeey, gibdaabinal isbirraay, wohut Yallak geyuwaa galtot loowitakaay, wadirih hinnnay, naqboytat foocah koositak naddoowek, abe uma taama Yalli kaah cabah" iyye.
~ Dagoom xokobbaye waqdi,...
Meqe NABI ﷺ " (woo essero hee sacaabittak) aninnaay kah itteh sugtem? " kaak iyye.
Qagseh "Anu Yallih gital jihaadah rabek, Yalli anu abe zambitte inkih yoh cabelee?" iyye.
~ Meqe NABI ﷺ kaal gacseh "yeey, Kaa gufu xiqa gibdaabinal isbirraay, wohut Yallak geyuwaa galtot loowitakaay, wadirih hinnnay, naqboytat foocah koositak naddoowek, abe uma taama Yalli kaah cabah, #mogo kak koh raqtay immay, away Jibriil yol yemeeteh tutucca yot iyyeeh tamannah yok iyye" iyye. Muslim xaagise.
★Cubbusa,
★ Jibriil qaraanak amok kah yemeetem kaxxam gibdi caagid kinnim sinnih cubbusa!!
② Gersi cadiisil tanim,...
Sacaabak num rabeeh, kaa kaqlissaay, kaffaanissaay, bicissa heenih Salaatul Janaaza kaal abâ gidah Meqe NABIH ﷺ farmo ruuben.
yemeeteh, kabbaye waqdi " sin kataysih amol mogo tanim maayle?" iyye.
~ Sacaaba " yeey 2dirham kaal tan" iyyen.
→ Meqe NABI ﷺ " sinni wakliital salaatita hay" keenik iyyeh kaal salaate kal isih yuduure.
~ Tokkel Abuu qhataada xeqsita sacaabiiti " kay amol tan mogo anu akkuqeyyo" iyye.
~ Tooway, mogo kaak nukkuqehik, salaat kaal abâ gidah ama iyyenih, Meqe NABIH ﷺ farmo ruuben.
~ Meqe NABI ﷺ Mogo yukkuqe numuk " a mogo kay fillak kattateh, ku fillal haytee?" Iyye.
Woo sacaabiiti " Yeey Yallih farmoytaw " iyye.
Tooway kaal salaateh, gersi saaku " mogo mekeltee" axcuk woo num essere, naharsi saaku " mamekliyyo" iyye. Gersi saaku kas essere " mekleh Yallih farmoytaw ﷺ " iyye.
Meqe NABI ﷺ "ku kataysal digaala tawayvxabbocowteh " iyye.
★ Akkel ta cadiswak baritnam,....
① Yalli gersi zambitte inkih caba way, mogo sinaamah cabewaam...!
② Mogo fillal kak anuk rabe numuk, woo mogo mekella haanam fan kah diggalsimak sugam....!
③ Mogo elle tan numul salaatul janaaza abaanam taqabilem...!
④ Mogo fillal kak tan num faxe meqe taama yaalle way, jannatti culma taqabi kaaklem!
★ Meqe toobokoy, meqe maqanxiixow, ......
=> Marin cakki fillal siinik quukaanam meqem hinna!
=> Kak daccarsimnam faxximta.
=> Mogo net tenekaa tekkek le waktil xayuk tet mekellam faxxinta.
~~\\~~~~
✍ Md Ali
( Diinii kee Anaakara)
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሰው መሳይ በሸንጎዎችን እየተጠነቀቅን
~
ከሸሪዐ አንፃር የፖለቲካና አስተዳደር ርእስ ከፊቅህ ርእሶች የቀለለ አይደለም። ስለ ጦሀራ፣ ስለ ዘካ፣ ስለ ... የረባ ግንዛቤ እንደሌለን አውቀን ፀጥ ብለን እያሳለፍን ፖለቲካው ላይ ሲደርስ ነብር፣ ነብር የሚሰራን በሁለት ምክንያቶች ነው።
1ኛው ምክንያት ስለ ፖለቲካ ማውራት፣ የሃገራት መሪዎችን ማብጠልጠል የንቃት ማሳያ ስለሚመስለን ነው። "ሁሉም ስለ ፖለቲካ እያወራ ነው። እኔ ከማን አንሳለሁ" አይነት ስሜት። በዚህ ግልብ ድምዳሜ የተነሳ ከኛ የተለየ ሃሳብ የያዘውን ሁሉ ዑለማኦችን ጭምር በአሸርጋጅነት፣ በአሽቃባጭነት በመፈረጅ "ችሎታችንን" ልናሳይ እንጋጋጣለን።
ሁለተኛው ምክንያት አለማወቃችን እየሰጠን ያለው ድፍረት ነው። ፖለቲካ 1 + 1 = 2 አይነት የልጅ ሂሳብ አይደለም።
* ፖለቲካ ጥልቅ ንባብ ይፈልጋል። ዛሬ ስለ ፖለቲካ የሚፈተፍተው ግን ጥልቅ ንባብ ሊኖረው ቀርቶ ዘለግ ያለ የፌስቡክ ልጥፍ ጨርሶ ለማንበብ ትእግስት የለውም።
* ፖለቲካን በኢስላም መነፅር ለመመልከት ጥልቅ የሸሪዐ ግንዛቤም ይፈልጋል። ግንዛቤው ግልብ የሆነ ሰው ከጋዜጠኛ፣ አክቲቪስት እና ተንታኝ ኋላ ሳይሆን ከዓሊሞች ኋላ ነው መሰለፍ ያለበት። አላህ እንዲህ ይላል:-
{وَإِذَا جَاۤءَهُمۡ أَمۡرࣱ مِّنَ ٱلۡأَمۡنِ أَوِ ٱلۡخَوۡفِ أَذَاعُوا۟ بِهِۦۖ وَلَوۡ رَدُّوهُ إِلَى ٱلرَّسُولِ وَإِلَىٰۤ أُو۟لِی ٱلۡأَمۡرِ مِنۡهُمۡ لَعَلِمَهُ ٱلَّذِینَ یَسۡتَنۢبِطُونَهُۥ مِنۡهُمۡۗ وَلَوۡلَا فَضۡلُ ٱللَّهِ عَلَیۡكُمۡ وَرَحۡمَتُهُۥ لَٱتَّبَعۡتُمُ ٱلشَّیۡطَـٰنَ إِلَّا قَلِیلࣰا}
"ከጸጥታ ወይም ከፍርሃት አንዳች (ወሬ) በመጣላቸውም ጊዜ እርሱን ያናፍሳሉ። ወደ መልክተኛውና ከእነርሱ ወደ ትዕዛዙ ባለቤቶች (ወደ ዐዋቂዎቹ) በመለሱት ኖሮ እነዚያ ከእነርሱ (ነገሩን) የሚያውጣጡት ባወቁት ነበር። በእናንተም ላይ የአላህ ችሮታና እዝነቱ ባልነበረ ኖሮ ከጥቂቶች በስተቀር ሰይጣንን በተከተላችሁ ነበር።" [አኒሳእ፡ 83]
አንዳንዴ ሁላችንም የምናውቀው ግልፅ እውነታ የሚይያዝበት መንገድ ሊለያይ ይችላል። በወቅታዊ ወሳኝ ክስተቶችና ሃይሎች የተነሳ፣ በሚታዩ ስጋቶችና ተግዳሮቶች ሳቢያ፣ በአቅም ውስንነትና ጥንካሬ ምክንያት፣ ባጭሩ በተለያዩ ለኛ በሚታዩንም ይሁን በማይታዩን ሃገራዊም ይሁን ህዝባዊ መስለሐዎች እና መፍሰዳዎች የተነሳ ጉዳዮች የሚያዙበት እና የሚተነተኑበት አቅጣጫና መጠን ከጊዜ ጊዜ፣ ከቦታ ቦታ የሚለያይበት ብዙ ሁኔታ አለ። “Politics is more difficult than physics” ይላል አይንስታይን። ፖለቲካ ከፊዚክስ ይከብዳል ማለቱ ነው። ብዙዎቻችን ዘንድ ደግሞ ፖለቲካ ከፊዚክስ ይቀላል። የእውነት ቀሎን ሳይሆን ድንቁ - ርናችን የወለደው ድፍረት ነው።
የምስል ማስታወሻ፦
ሰብሎችን ለመጠበቅ በማለም ከሩቅ ሲያዩት ሰው እንዲመስል ተደርጎ የሚሰራ ነገር በሸንጎ ይባላል። "ሰው መሳይ በሸንጎ" የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር እንደሚታሰበው ያልሆነ አስመሳይ፣ ወስላታ ማለት ነው። ኢስላምን እየታከኩ የሚጽፉ ብዙ ሰው መሳይ በሸንጎዎች አሉ። እነዚህን ቃላት እየከሸኑ ፖለቲካ በመፈትፈት የተጠመዱ አካላት ዑለማእ ላይ ሲዘምቱ እየተከተልን ባንሸወድ መልካም ነው። አብዛኞቹ ከሩቅ እንደሚታዩት አይደሉም። ነገሮች በሸሪዐ ሚዛን እንዴት እንደሚያዙ አያውቁም። መሰረታዊ የተውሒድና የሽርክ ግንዛቤ የላቸውም። ስለ ጀናባ ቢጠየቁ ውሃ የሚያነሳ ነገር መናገር አይችሉም። ዜና በመለቃቀም በድፍረት ከመለቅለቅ ባለፈ መሬት ላይ ያለውንም ተጨባጭ አይረዱም። ለራሳችን ስንል ብንጠነቀቃቸው መልካም ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Arbaquuna Cadiis Darsi
TaShricem:
Dr. Mucammad Cuseen Weeqisa.
Arac: Qafar Ra/Logyah Magaalak Icsaan Masjidi.
Cadiis Loowo: 32)
"شرح كتاب الأربعين حديثًا"
الشارح: فضيلة الشيخ الدكتور محمد حسين ويعسى
اللغة: العفرية.
المكان: جامع الإحسان، مدينة لوغيا.
الحديث الثالث: (3)
https://t.me/AfarMahaNetwork/937?single
👆🏻👆🏻👆🏻
📚 #ማን ይፍረድ ሙፍቲ ወይስ ቃዲ?
🎙በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
🔗 ቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/ustazilyas/1334
🔗 ቪዲዮውን ለመከታተል
https://www.facebook.com/share/v/18T1bejFZB/?mibextid=qi2Omg
____
🏳️ የኡስታዝ ኢልያስ አሕመድ የትምህርት መድረክ
https://www.facebook.com/ustathilyas
Arbaquuna Cadiis Darsi
TaShricem:
Dr. Mucammad Cuseen Weeqisa.
Arac: Qafar Ra/Logyah Magaalak Icsaan Masjidi.
Cadiis Loowo: (1)
"شرح كتاب الأربعين حديثًا"
الشارع: فضيلة الشيخ الدكتور محمد حسين ويعسى
اللغة: العفرية.
المكان: جامع الإحسان، مدينة لوغيا.
الحديث: (1)
https://t.me/AfarMahaNetwork/937?single
🧶 Qhur-aan yicfize marih fayu
🔊 : Dr Macammad cuseen
https://t.me/diini_goori_media
"Nanu Yalli Islaaminâ diinih sabbath fayya hee mara kinnino, Diiniksa taniimit mayso/fayya gorrisnek, Yalli ramma nee heele!! "
🔏Qumar Ibnul khattaab
@httpsDiiniKeeAnaakara
Repost from 𝐃𝐈𝐈𝐍𝐈 𝐆𝐎𝐎𝐑𝐈 𝐌𝐄𝐃𝐈𝐀
Rufto le xaagu Qilmi barisiyyaKitab: arbaqiin alcadiis sharci Arac: logyak markazul icsaan Barseeni: dr Macammad cusen Uddur: ummaan sabtii kee caadah saaki saalitih laka Mamaata edde bicta marak maraaqina edde bice wayta marak inshaa-allaah a group'il siinih ruubenno https://t.me/diini_goori_media
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ጫት
~
ጫት የዲን፣ የጤና፣ የኢኮኖሚ፣ የቤተሰብ፣ የማህበራዊ ህይወት፣ የሃገር እድገት ፀር ነው። በጫት የተነሳ ትውልዱ ወኔው የፈሰሰ፣ ሞራሉ የላሸቀ የወጣት ጡረተኛ ሆኗል። በጫት ሱስ በደነዘዙ ቤተሰቦች ጭካኔ የተነሳ እህቶቻችንና ወንድሞቻችን ለአመታት በሰው ሃገር ደክመው ያጠራቀሙት ጥሪት እንደ ዋዛ መና ቀርቷል። የጫት ጉዳት ከሚገለፀው በላይ የከፋ ነው።
ለችግሩ መባባስ አንዱ ሰበብ ደዕዋ ላይ ያሉ ሰዎች የችግሩን ስፋትና ጥልቀት ባገናዘበ መልኩ ተገቢ ትኩረት ሰጥተው አለማስተማራቸው ነው። አሁንም በሚገባ ልንነቃ ይገባል። የወገናችን ጉዳት የሚያመው ሁሉ! በሚችለው መድረክ ሁሉ ከዚህ መርዛማ ቅጠል ሰዎችን ሊያስጠነቅቅ ይገባል። በዚህ ቅጠል የተለከፉ ወገኖችን ከሱስ ማውጣት ቢያቅተን እንኳ ቢያንስ ልጆቻቸውን በሚጠብቁበት መልኩ በቂ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ብናደርግ ቀላል ስኬት አይደለም።
~
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ለመጀመሪያ ጊዜ ወይም ለሁለተኛ ጊዜ የተፈታች ሴት ዒዳዋ እስካልተጠናቀቀ ድረስ ለባሏ ፊቷን መግለጥ፣ መዋዋብ፣ ከሱ ጋር ማውራት፣ ተገልሎ መቀመጥ ትችላለች። ግንኙነት የሚፈፀመው ግን ከመለሰ በኋላ ወይም በመመለስ ኒያ ሲሆን ነው።
ዒዳዋ ካላለቀ በቀላሉ መመለስ ይችላል። ዒዳዋ ከተጠናቀቀ በኋላ መመለስ ቢፈልግ ግን አዲስ ኒካሕ ነው በወሊይና ሁለት ምስክር የሚያስረው።
ለሶስተኛ ጊዜ ከፈታ ግን ከዚህ በኋላ መመለስ የሚችለው በትክክለኛ ኒካሕ ሌላ ሰው አግብታ ግንኙነት የተፈፀመበት ጋብቻ ሆኖ ከተፈታች ብቻ ነው። በሃገራችን የተለመደው ለቀድሞ ባሏ ሐላል ለማድረግ ታስቦ የሚፈፀም ጊዜያዊ ጋብቻ እጅጉን የተወገዘ ተግባር ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ልጅህን አባት ያለው የቲም አታድርገው!
~
ልጆች ከአላህ የተሰጡ አማናዎች ናቸው። አማናን ባግባቡ አለመጠበቅ ነውር ነው። ዘመኑ እንደምናየው ከባድ ነው። የልጆችን ህይወት የሚያበላሹ ነገሮች በጣም በዝተዋል። የአደጋ ስጋት ሲጨምር ጥንቃቄያችን መጨመር ነበረበት። እኛ ግን ይበልጥ እየተዘናጋን ነው። በገዛ ገንዘብህ፣ እጅህ ላይ ባለው ሞባይል፣ ቤትህ ውስጥ ባለው ቴሌቪዥን ልጆችህን እያጠፋሃቸው እንዳይሆን ተጠንቀቅ። ልጅህ ልጅ ነው። የነገ ህይወቱን ሳይሆን የዛሬ ደስታውን ነው የሚያየው። ቅፅበታዊ ኩርፊያውን ፈርተህ፣ የእለት ደስታውን ብቻ እያየህ የጠየቀውን ሁሉ አትስጥ። የሚያስፈልገውን እንጂ የሚፈልገውን ሁሉ አታድርግ።
ትንፋሽ እስከሚያጣ አስጨንቀው እያልኩህ አይደለም። ግን ዛሬ ቁርኣን ካልቀራ፣ ዲኑን ካላወቀ፣ ትምህርት ካልተማረ መቼ ሊማር ነው? አባትነት ልጆችን ቆፍጠን ብሎ በስርአት ለማሳደግ ካልሆነ ምን የረባ ትርጉም አለው? አኺራውንም ይሁን ዱንያውን በተመለከተ ስለ ነገ ህይወቱ አንተ ካልተጨነቅክለት ማን ይጨነቅለት? አባትነትህ ለዚህ ካልሆነ ለምን ይሁን?
ስለ ልጅህ ስታስብ ልብሱና ጉርሱ ላይ አትቁም። ነጣ ገረጣ፣ ከሳ ኮሰሰ፣ ሳቀ አኮረፈ ላይ ብቻ አታተኩር። "ለነገ ምን ይዟል?" በል። ለሃላፊነት አዘጋጀው። ህይወት ከባድ ትምህርት ቤት ናት። ብዙ መውጣት መውረድ አላት። ነገ ምን እንደሚገጥመው አታውቅም። ሁሌ አብረኸው አትሆንም። ብትሆንም አቅምህ ውስን ናት። ጥገኝነትን አታለማምደው። ካንተ የተሻለ እንጂ ያነሰ እንዲሆን አትተወው። ከመስመር ወጥቶ ከሆነ በጊዜ ወደ ቦዩ መልሰው።
ይጫወት ፋታ ስጠው። ግና ቁም ነገረኝነትን አስተምረው። ያለበለዚያ አካሉ ቢያድግም ከልጅነት ስነ ልቦና አይወጣም። በሰላሳ አመቱም የሰው እጅ የሚጠብቅ ጥገኛ ይሆናል። ሌሎችን በሚጦርበት እድሜው ተዘፍዝፎ በአዛውንቶች ይጦራል። ከእህቱ እየነጠቀ ሱስ የሚያሳድድ ጅል ፈጥረት ይሆናል።
ባጭሩ ለልጅህ የእውነት አባት ሁነው። ከልብ አንፀው። መኖርህ በልጅህ አስተዳደግ ላይ ትርጉም ያለው ልዩነት ይኑረው። ልጅህን በአደብ፣ በእውቀት ተከትኩቶ እንዲያድግ ካላገዝከው በህይወት እያለህ የቲም አድርገኸዋል። የአባትን መኖር ትርጉም ነፍገኸዋል። የምታሳድገው ልጅ የቤተሰብ ማፈሪያ፣ የማህበረሰብ እዳ፣ የሃገር ሸክም ከሆነ በሃገርም በወገንም ላይ ትልቅ በደል ነው የፈፀምከው። ይሄ ህዝብ ጀርባውን ያጎበጠው ብዙ ሸክም አለበት። ሌላ ሸክም አትጨምርበት። ለራስህም ቢሆን ነገ በፀፀት እጅህን ከመንከስህ በፊት ዛሬ ሃላፊነትህን ባግባቡ ተወጣ። አባት ሁን። አባት!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሰዑዲያ ዑለማኦች ጥፋት እያዩ ዝም ይላሉ ለሚሉ!
ሸይኽ ሷሊሕ አልዑሶይሚይ - አላህ ይጠብቃቸውና - ድንቅ ምላሽ ይሰጣሉ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሰዑዲያ ዑለማኦች ጥፋት እያዩ ዝም ይላሉ ለሚሉ!
ሸይኽ ሷሊሕ አልዑሶይሚይ - አላህ ይጠብቃቸውና - ድንቅ ምላሽ ይሰጣሉ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ለምንድን ነው ስደውል ያላነሳሽው?
አስተማሪ ታሪክ
~
ለሆነ ጉዳይ ለሶስት ቀናት መንገድ ወጣሁ። ሌላኛው ሃገር እንደደረስኩ ሚስቴንና አንድ ልጄን ደህንነታቸውን ለማስረገጥ ደወልኩ። ከዚህ በፊት ከነሱ ተለይቼ አላውቅም። እነሱም መራቄን አያውቁትም። ካገባሁ ሶስት አመቴ ነው። የሆነ ሆኖ ስልኬ አልተነሳም። ስልኬ ከእጄ ሳይነጠል ሶስት ቀናት አለፉ። ያለ ግነት በየ እሩብ ሰዓቱ ቢበዛ በየ ግማሽ ሰዓት እደውላለሁ። ምላሽ የለም።
በሃይለኛ ተበሳጨሁ። ወንድሜ እና እህቴ ላይ ደወልኩ። የትንሿን ቤተሰቤን ደህንነት እንዲያረጋግጡልኝ ጠየቅኳቸው። ሰላም እንደሆኑ ነገሩኝ። አላመንኳቸውም።
የሚስቴ እናት (አክስቴ) ላይ ደወልኩ። ሰላም እንደሆኑ ነገረችኝ። ስልካቸውን እንደምጠብቅ ነገርኳት። ብጠብቅ ብጠብቅ አንድም የሚደውል የለም።
ሶስቱ ቀናት ረጃጅም ሶስት ወራት ያክል ሆነው አለፉ። አንዳንዴ ቁጣዬ ከውስጥ ሲገነፍል ይሰማኛል። ሌላ ጊዜ በሁኔታው በጣም እየተገረምኩ ምክንያቱን ለማወቅ እሞክራለሁ።
ሸይጧን አስፈሪ ጉትጎታዎችን ደግሞ ደጋግሞ ያመጣብኛል። ቀናቱ አለፉ። ወደ ሃገሬ ተመለስኩ። እግሬ እንደረገጠ ወደ ቤቴ ነበር የበረርኩት። እንደደረስኩ በሩን አንኳኳለሁ። እሱም ሳይበቃኝ ደወሉን ላይ በላይ እደውላለሁ። ባለቤቴ በሩን ከፈተች። ከነ ሙሉ ውበቷ፣ ከነ ሙሉ ድምቀቷ። ባማረ በደመቀ ሁኔታ ተቀበለችኝ። ከባድ አጋጣሚ ነበር። ልጄ ከኋላዋ አለ። አይኖቹ በደስታ ይጨፍራሉ። ሊያቅፈኝ እየሮጠ መጣ። እኔ እንደደነዘዘ ሰው ሆኛለሁ። ሰበቡም ጠፋኝ። በፍጥነት በቁጣዬ ቦታ ግርምት ተተካ።
ባለቤቴን የዚህ ሁሉ ቸልትኝነት ምክንያቱ ምን እንደሆነ ጠየቅኳት። ጉዞዬን አቋርጬ በፍጥነት ልመለስ ተቃርቤ ነበር። አጉል ጥርጣሬ ከያቅጣጫው ወሮኝ ነበር።
ባለቤቴ ተረጋግታ መለሰችልኝ። "ለእናትህ ደውለሃል?" አለችኝ። ለምን እንደጠየቀችኝ ምክንያቷ ባይገባኝም እንዳልደወልኩ ነገርኳት። ንግግሯ ገዳይ ነበር ። እንዲህ አለችኝ፡ "በነዚህ ቀናት ውስጥ ስሜትህ ምን እንደሆነ አየህ አይደል? የእናትህም ስሜት ይሄው ራሱ ነው፣ ለቀናት ሳትደውልላት ስትቆይ። ናፍቆት ለብልቧት፣ ስጋት ገብቷት እሷ ካልደወለች በቀር አንተ ደውለህ ድምጿን አትሰማም። ይሄን ጉዳይ በተደጋጋሚ ላስረዳህ ሞክሬያለሁ። የምትረዳ ግን አልሆንክም። ክቡር ባለቤቴ! ከዚህ የተሻለ መልእክቴን የማደርስበት መንገድ አላገኘሁም።
እድሜዋ ትንሽ ዐቅሏ ግን ትልቅ የሆነችዋን ሚስቴን አፈርኳት። አንገቴን ደፋሁ። ትምህርቱ በሚገባ ነው የደረሰኝ። የመኪናዬን ቁልፍ እያቀበለችኝ ወደ ጀሮዬ ጠጋ ብላ "ጀነትህ እየጠበቀችህ ነው" አለችኝ።
እድሜ ልኬን የማልረሳውን ትምህርት ከጠቢቧ ሚስቴ ተምሬ ወደ መጀመሪያዋ ውዴ ወደ እናቴ ሄድኩኝ። ፀፀት በማይጠቅምበት ቀን ከመፀፀት ነፍሴን ስላተረፈችኝ ውለታዋን መቼም አልረሳም። ለዚች ጠቢብና አስተዋይ ሚስት ምስጋና ይገባታል። አሳምራ ኮትኩታ ላሳደገቻት እናቷ ምስጋና ይገባታል። እሷን ለመረጠችልኝ እናቴ ምስጋና ይገባታል።
እሷን ሰበብ አድርጎ በእዝነቱ ከእንቅልፌ ያነቃኝ ጌታ ምስጋና ይገባዋል።
እናቴ! እናታቶቻችሁ ! በዱንያ ያሉ ጀነቶቻችን ናቸው። ሌላው ቢቀር በየቀኑ በመደወል እንኳ ቢሆን አትርሷቸው። ይሄ ትንሹ ነገር ነው። ልቦቻቸው እኛን ይጠብቃሉ። ለኛ ዱዓእ ያደርጋሉ። በየ ሰዓቱ ስለኛ ይጨነቃሉ። እያሰቡ እየተጨነቁም ደጋግመው በመደወል እንዳይረብሹን በመስጋት ከመደወል ይታቀባሉ። ባሎቻችሁን፣ ሚስቶቻችሁን ወላጆቻቸውን እንዲያስቡ በማስታወስ አግዙ።
ከ0ረብኛ የተመለሰ
የብዙዎቻችን በተለይም የወንዶች ችግር ነውና እንድንማርበት ብታሰራጩት ባረከላሁ ፊኩም።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 26/ 2017)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
