en
Feedback
☀ሁዳ መልቲሚዲያ |HUDA MULTIMEDIA

☀ሁዳ መልቲሚዲያ |HUDA MULTIMEDIA

Open in Telegram

☀ሁዳ መልቲሚዲያ - ‌🇭‌🇺‌🇩‌🇦 ‌🇲‌🇺‌🇱‌🇹‌🇮‌🇲‌🇪‌🇩‌🇮‌🇦 -قناة هدى الاسلامية ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ንፁህ ኢስላማዊ እውቀት ይደርሳቸው ዘንድ እንሰራለን! ለአስተያየት @nuugaa

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ☀ሁዳ መልቲሚዲያ |HUDA MULTIMEDIA

Channel ☀ሁዳ መልቲሚዲያ |HUDA MULTIMEDIA (@huda4eth) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 908 subscribers, ranking 3 599 in the Religion & Spirituality category and 1 526 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 908 subscribers.

According to the latest data from 08 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -196 over the last 30 days and by -5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 11.26%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 5.99% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 2 467 views. Within the first day, a publication typically gains 1 313 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 13.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
☀ሁዳ መልቲሚዲያ - ‌🇭‌🇺‌🇩‌🇦 ‌🇲‌🇺‌🇱‌🇹‌🇮‌🇲‌🇪‌🇩‌🇮‌🇦 -قناة هدى الاسلامية ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ንፁህ ኢስላማዊ እውቀት ይደርሳቸው ዘንድ እንሰራለን! ለአስተያየት @nuugaa

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

21 908
Subscribers
-524 hours
-267 days
-19630 days
Posts Archive
የጁሙዓህ ኹጥባህ በኡስታዝ ሙከሚል ከማል የሐዲሥ መረጃነት በሚል ርዕስ

ምርጫ ቦርድ ሰብዓዊ መብቷን አክብሮ፣ ነፃነቷን በመጠበቅ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በእኩልነት ቀጥሮ ታስመርጥ ዘንድ የቀጠራትን ኒቃቢስት ሙስሊም ኢትዮጵያዊ ተመልከቱ ... ይህ ኒቃብን በመመሪያ ከል
ምርጫ ቦርድ ሰብዓዊ መብቷን አክብሮ፣ ነፃነቷን በመጠበቅ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በእኩልነት ቀጥሮ ታስመርጥ ዘንድ የቀጠራትን ኒቃቢስት ሙስሊም ኢትዮጵያዊ ተመልከቱ ... ይህ ኒቃብን በመመሪያ ከልክሎ ሙስሊም ተማሪዎችን ከመማር ማስተማሩ እያደናቀፈ ላለው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና መሠል ተቋማት ትልቅ ትምህርት ይሆናል። ኒቃብ እሴታችን፣ ባህላችን፣ ማንነታችን፣ እምነታችን ነው። ከመማር፣ ከመስራት አያግድም። እንደለበሱ ይማራሉ፤ እንደለበሱ ይሰራሉ፤ እንደለበሱ ሀገርን ያገለግላሉ። አትልበሱ፣ አይለብሱም ለሚሉት ጥያቄ አለን፤ ፍትሐዊ መልስ እስኪሰጡ ጥያቄ አለን! @aaumsu

ሙስሊም ሴቶች ሒጃባቸውን (ኒቃብ) እንደለበሱ መንግስታቸውን ሲመርጡ የሚያሳይ ምስል ነው። ምርጫ ቦርድ የሁሉንም ሀይማኖት እና ባህል ባማከለ መልኩ አግላይ ያልሆነን የምርጫ ስርዓት መዘርጋቱ የሚበረታ
ሙስሊም ሴቶች ሒጃባቸውን (ኒቃብ) እንደለበሱ መንግስታቸውን ሲመርጡ የሚያሳይ ምስል ነው። ምርጫ ቦርድ የሁሉንም ሀይማኖት እና ባህል ባማከለ መልኩ አግላይ ያልሆነን የምርጫ ስርዓት መዘርጋቱ የሚበረታታ ነው። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጀምሮ ሒጃብ (ኒቃብ) ለባሽ ሙስሊም ዜጎችን ባገለለ መልኩ የትምህርት ስርዓታቸውን ለመዘርጋት የሚሞክሩ ተቋማት ከዚህ መማር አለባቸው። መንግስቷን ስትመርጥ ኒቃብ ስለለበሽ ተብላ ያልተከለከለች ኢትዮጵያዊ በመንግስት ተቋም ልትማር ስትሄድ ኒቃብ ስለለበሽ ተብላ የምትከለከለው በየትኛው አመክንዮ ነው?! ከዚህ ታልፎ ይህንን መድሎ ሕጋዊ ለማድረግ የሚሞክር ሕገ-ወጥ መመሪያ ማውጣትስ ምን ማለት ነው?! ሊታረም ይገባል!! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

'ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፦ "ይህ የወርቅ ሜዳሊያ ድል የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና የኮሚቴ አባላት መስዋዕትነት ፍሬ ነው"' ሲሉ ተደምጠዋል ::
+2
'ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፦ "ይህ የወርቅ ሜዳሊያ ድል የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና የኮሚቴ አባላት መስዋዕትነት ፍሬ ነው"' ሲሉ ተደምጠዋል ::

ታሪካዊው የ“አልማዝ” የክብር ሽልማት ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ የሐጅ ልዑክ ሀገር ቤት ገባ የዘንድሮው የ1447 ዓ.ሒ የሐጅ ጉዞ እጅግ በላቀ ሁኔታ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ፣ የኢትዮጵያ እስል
ታሪካዊው የ“አልማዝ” የክብር ሽልማት ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ የሐጅ ልዑክ ሀገር ቤት ገባ የዘንድሮው የ1447 ዓ.ሒ የሐጅ ጉዞ እጅግ በላቀ ሁኔታ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ዛሬ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ታሪካዊ የምስራች አብስረዋል። የኢትዮጵያ የሐጅ ልዑክ ከ160 በላይ ከሚሆኑ የዓለም ሀገራት መካከል ቀዳሚ በመሆን፣ ከፍተኛውን እና ታሪካዊውን የ“አልማዝ” የክብር ሽልማት ማሸነፉን ይፋ አድርገዋል። ቀደም ባሉት ጊዜያት ወገኖቻችን ጥሪታቸውንና ከብቶቻቸውን እየሸጡ፣ በየበረሃው ወራትን በሚፈጅ መንገድ ይንገላቱበት የነበረው የሐጅ ጉዞ ዛሬ ላይ ታሪክ ሆኗል። ይህ ታላቅ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ በተለይም ከታች እስከ ላይ ያሉ የየደረጃው የኮሚቴ አባላት ሌት ተቀን በከፈሉት ታላቅ መስዋዕትነትና ባደረጉት የጋራ ርብርብ ነው። የሳዑዲ አረቢያ የሐጅ እና ዑምራ ሚኒስቴር “ኺታሙሁ ሚስክ” በተባለው ታላቅ መርሃ-ግብሩ ላይ ሽልማቱን ለኢትዮጵያ በይፋ አስረክቧል። ክቡር ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ዛሬ በምክር ቤቱ ቅጥር ግቢ በተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፦ “ጅማሮውንም መጨረሻውን ላሳመረው አላህ ምስጋና ይገባው፤ ከዚህ በፊት የነበረው የሑጃጆች እንግልት አብቅቶ ለመላው ዓለም አርአያ የሆነ አገልግሎት መስጠት ችለናል!” በማለት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና ለምክር ቤቱ አባላት በሙሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በ ሀያት ሁሴን

ለሙስሊሞች ተቆርቋሪዋ ሀገር ኤምባሲ የእንኳን አደረሳችሁ መልክት አስተላልፏል😁 አዞ የውሀ ውስጥ እንስሳቷን አስታወሳችዃት? ወፈር ያለ እንስሳ እንደ የበግ ግልገል የመሰለ ልትውጥ ስትታገል አይኗ ያ
ለሙስሊሞች ተቆርቋሪዋ ሀገር ኤምባሲ የእንኳን አደረሳችሁ መልክት አስተላልፏል😁 አዞ የውሀ ውስጥ እንስሳቷን አስታወሳችዃት? ወፈር ያለ እንስሳ እንደ የበግ ግልገል የመሰለ ልትውጥ ስትታገል አይኗ ያለቅሳል አሉ!! አይኗ ያለቀሰው ለግልገሉ እዝነት አይደለም! ነገር ግን የበላችው ነገር ትልቅ ስለሆነ አንቋት ነው! እስከምትውጠው ታለቅሳለች አሉ!! ኢምባሲውም ስለሚወደን የአዞ እምባ እያነባልን መሆኑ ነው¡¡

ዒድ ሙባረክ! ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም 🎈✨ አላህ መልካም ስራችንን ይቀበለን። ይህ ቀን የመብላት፣ የመጠጣትና አላህን በብዛት የማውሳት ቀን ነው። 💬 ከሐዲስ፡ ነቢዩ (ﷺ) ስለ ዒድ እና ከዒድ በኋላ ስላሉት ቀናት (አያመተሽሪቅ) ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦ "የአያመተሽሪቅ ቀናት (ከዒድ በኋላ ያሉ ሶስት ቀናት) የመብያ፣ የመጠጫና አላህን የማውሻ (የዚክር) ቀናት ናቸው።" (ሶሒህ ሙስሊም) 🤝 የተቀያየማችሁትን ይቅርታ ጠይቁ፣ የታመሙትን ጠይቁ፣ ድሆችንና የቲሞችን በደስታችሁ መሀል አስታውሷቸው። ዒዳችሁን ያማረ ያድርግላችሁ!

https://vt.tiktok.com/ZSxHs4GkS/ይህን ቪዲዮ እስከ መጨረሻ ተመልከቱ 👀🔥 የዛሬው መልእክት ለልብህ… 🤍

📌ዙልሂጃ 8: "ለነገው ታላቅ ቀን ተዘጋጅተሃል?" ነገ 9ኛው ቀን (የአረፋ ቀን) ነው። የአመቱ እጅግ በላጭና ምርጡ ቀን! ሐጅ ላይ የሌለን ሙስሊሞች ነገን በመፆም ከአላህ ትልቅ ምንዳ የምንቀበልበ
📌ዙልሂጃ 8: "ለነገው ታላቅ ቀን ተዘጋጅተሃል?" ነገ 9ኛው ቀን (የአረፋ ቀን) ነው። የአመቱ እጅግ በላጭና ምርጡ ቀን! ሐጅ ላይ የሌለን ሙስሊሞች ነገን በመፆም ከአላህ ትልቅ ምንዳ የምንቀበልበት ቀን ነው። 💬 ነቢዩ (ﷺ) ስለ አረፋ ቀን ፆም ሲጠየቁ እንዲህ አሉ። "የአለፈውን አመትና የመጪውን አመት (ትናንሽ) ወንጀሎች ያስምራል።" (ሶሒህ ሙስሊም) 🚨 ሼር ያድርጉት፦ ዛሬ ሌሊት ሰሑር ለመነሳት ስልክህን አላርም ሙላ፣ ቤተሰቦችህንም ቀስቅስ። አንተ በላክኸው መልእክት ምክንያት አንድ ሰው ቢፆም፣ የአንተ ምንዳ ሳይቀነስ የሱ አይነት አጅር ታገኛለህ!

ዙልሂጃ 7: የአባታችን ኢብራሂምን ፈለግ መከተል! 🐑🔪 አቅም ላለው ሰው በዙልሒጃህ 10ኛው ቀን (የዒድ እለት) ወይም ከዒድ በኋላ ባሉት ሶስት ቀናት (አያመተሽሪቅ) ኡድሒያ ማረድ ትልቅ አጅር አለው። 📖 ከቁርዓን፡ "ለጌታህ ስገድ፤ እረድም (ኡድሒያ አድርግ)።" (ሱረቱ አል-ከውሰር፡ 2) 💬 ከሐዲስ፡ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ "ኡድሒያ ማረድ ለምትፈልጉ ሰው፤ የዙልሒጃህ ጨረቃ ከታየች ጀምሮ ኡድሒያውን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩም ሆነ ከጥፍሩ ምንም እንዳይቆርጥ (እንዳይነካ)።" (ሶሒህ ሙስሊም) ⚠️ ማሳሰቢያ፦ እርድ ለማረድ ያሰባችሁ ወንድሞችና እህቶች ጥፍርና ፀጉር ከመቁረጥ ተቆጠቡ። አቅሙ የሌለን ደግሞ አላህ በኒያችን አጅሩን እንዲሰጠን እንለምነው።

መፈታት ጠዋፈል አኢፋደአ እና 3ቱ ቀናቶች (አያመ ተሽሪቅ) በተቀሩት 3 ቀናት የሚሰሩ ስራዎች ቪዲዮ ቁ 04 ሸይኽ ኢልያስ አህመድ ለመካ አያ ሆቴል ሁጃጆች ከተሰጠ ትምህርት የተወሰደ ሁዳ መልቲሚዲያ T.me/huda4eth #hajj #ሐጅ #ሀጅ #ሸይኽ_ኢልያስ_አህመድ@huda4eth

ሙዝደሊፋ ማደር፣ ጀምረተል ዓቀባ እና ነህር (እርድ መፈፀም) ቪዲዮ ቁ 03 ሸይኽ ኢልያስ አህመድ ለመካ አያ ሆቴል ሁጃጆች ከተሰጠ ትምህርት የተወሰደ ሁዳ መልቲሚዲያ T.me/huda4eth #hajj #ሐጅ #ሀጅ #ሸይኽ_ኢልያስ_አህመድ@huda4eth

ሚና እና የዓረፋ ቀን ውሎ ሸይኽ ኢልያስ አህመድ ለመካ አያ ሆቴል ሁጃጆች ከተሰጠ ትምህርት የተወሰደ ሁዳ መልቲሚዲያ T.me/huda4eth #hajj #ሐጅ #ሀጅ #ሸይኽ_ኢልያስ_አህመድ@huda4eth

የሐጅ ዝግጅት እና የሐጅ ኢህራም ቦታና ግዜ ሸይኽ ኢልያስ አህመድ ለመካ አያ ሆቴል ሁጃጆች ከተሰጠ ትምህርት የተወሰደ ሁዳ መልቲሚዲያ T.me/huda4eth #hajj #ሐጅ #ሀጅ #ሸይኽ_ኢልያስ_አህመድ@huda4eth

1. ሜክሲኮ ተባረክ መስጂድ 2. ስታዲየም 3. ፍልውሃ መስጂድ ### ራሳችንን ከፖለቲካ ማፅዳትና የተከለከሉ ነገሮች የፖሊስ ተወካዮች ባደረጉት ንግግር፣ ባለፈው የረመዳን በዓል የታዩ አንዳንድ ክፍተቶችን በማንሳት፣ በበዓሉ ላይ የኢራንና የፍልስጤም ባንዲራዎችን ይዞ መንቀሳቀስ ፍጹም የተከለከለ መሆኑን አስገንዝበዋል። > "ይሄ ፖለቲካ ነው፣ ልክ አይደለም። እንዲያውም ዱዓ በማድረግ ወገኖቻችንን ማሰብ ነው ያለብን። በፕሮግራሙ ላይ ህፃናትና አዛውንቶች ስለሚገኙ፣ የመጣንበትን ዓላማ ብቻ አሳክተን መመለስ አለብን። ራሳችንን ከፖለቲካ ማፅዳት ይኖርብናል" ሲሉ የጸጥታ አካላቱ አሳስበዋል። > በባነርና በቲሸርት ላይ የተዘጋጁ፣ የጸጥታ አካላት ሊረዷቸው የማይችሏቸውን የዓረብኛ ፅሁፎችንም ይዞ መግባት እንደማይቻልና ፍተሻ ላይ እንደማይለፉ ተገልጿል። ይህ ወቅት የበዓል ብቻ ሳይሆን ቀጣዩ ጊዜ የምርጫም ጭምር በመሆኑ፣ የሀገሪቱን ሰላም ሊያውኩ ከሚችሉ ነገሮች ሁሉም ሰው ራሱን እንዲጠብቅ ጥሪ ቀርቧል። ### ፍተሻን፣ ስርዓትንና አጠቃቀምን የተመለከቱ መመሪያዎች በዕለቱ የሚከናወኑ የፍተሻና የአስተናገጃ ስራዎችን ስኬታማ፣ ፈጣንና ከሕግ አግባብ ውጭ እንዳይሆኑ ለማድረግ የሚከተሉት ውሳኔዎች ተላልፈዋል፦ * የመግቢያ ሰዓትና ቅድመ-ዝግጅት፦ ስራው ለጸጥታ አካላትና ለአስተባባሪዎች አመቺ ይሆን ዘንድ አስተባባሪዎች ከሕዝቡ ቀድመው በጠዋት በቦታው መገኘት አለባቸው። * የፍተሻና የአስተናገጃ አቅጣጫ፦ የፍተሻ ስራውን ለማቀላጠፍና ስርዓትን ለመጠበቅ ሴቶች በአንድ አቅጣጫ፣ ወንዶች ደግሞ በሌላ አቅጣጫ በተለየ መስመር እንዲስተናገዱ ይደረጋል። * የሴቶች ፍተሻ እና ቦርሳዎች፦ ሴቶች በቦርሳቸው ውስጥ በርካታ ቁሳቁሶችን ስለሚይዙ ፍተሻውን አዳጋች እንዳያደርገው የያዙትን ዕቃ መጠን እንዲቀንሱ ወይም አነስተኛ እንዲያደርጉ ተጠይቋል። ፍተሻው በሴትና በወንድ ፈታሾች በጋራ የሚከናወን ሲሆን፣ የሴት አስተባባሪዎች እገዛ ከፍተኛ እንደሆነ ተገልጿል። * የኮስሞቲክስ ዕቃዎች፦ ሴቶች የሚይዟቸውን የኮስሞቲክስ ዕቃዎች ከመቀማት ይልቅ እራሳቸው ላይ ሞክረው (ፈትሸው) እንዲያልፉ ይደረጋል። * የካኪ መያዣ ክልከላ፦ ከተማዋን ሊያቆሽሽ የሚችል ማንኛውንም ነገር መያዝ አይቻልም። ካኪን ለዕቃና ለጫት መተቅለያነት የሚጠቀሙበት ወገኖች በመኖራቸው ወደ መስገጃ ቦታ ይዞ መግባት ፍጹም የተከለከለ ሲሆን፣ ምዕመናን የራሳቸውን ንፁህ መስገጃ ብቻ መያዝ ይችላሉ። * የስታዲየም አጠቃቀም፦ በዓሉ በሚከበርበት ስታዲየም ውስጥ ያለው ቦታ ሙሉ በሙሉ ሳይሞላ፣ ወደ ውጭ ሰው እንዳይቀመጥ አስተባባሪዎች ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርጉ ታዟል። ### ከጸጥታ አመራሮች የተሰጠ ምላሽና ማረጋገጫ የጸጥታ አካላትና ከፍተኛ አመራሮች ከአስተባባሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ዋና ዋና ማረጋገጫዎች ሰጥተዋል፦ 1. የሚዲያ ሽፋን፦ ሁሉም ሰው መረጃው አስቀድሞ እንዲደርሰውና ግንዛቤ እንዲኖረው ሰፊ የሚዲያ ሽፋን እንዲኖር ይደረጋል። 2. ክፍተቶችን ማረም፦ ከዚህ በፊት የነበሩትን ክፍተቶች በአሁኑ በዓል ለማስተካከል ከፍተኛ ጥረት ይደረጋል። ይህ ኦረንቴሽን ለአስተባባሪዎች ብቻ ሳይሆን ለሚሰማሩት የፖሊስ አባላትም በተመሳሳይ መልኩ የሚሰጥ በመሆኑ የተቀናጀ አሰራር ይፈጠራል። 3. ከአመራሮች ጋር ያለው ቅርበት፦ ከአመራሮች ጋር በጣም ልዩ የሆነ የሥራ ቅርበትና ግንኙነት ስላለ፣ ማንኛቸውም በመስክ ላይ የሚፈጠሩ ችግሮችን ወዲያውኑ እየተነጋገሩ ለመፍታት ዝግጁነት ተፈጥሯል። 4. ሕጋዊነት፦ "የምንሰራው በሕግና በአሰራር ላይ ተመስርተን ስለሆነ፣ ሕግን አንጥስም" በማለት ስራው በሙሉ ስነ-ስርዓት እንደሚመራ አስገንዝበዋል። ### ከፌደራል ፖሊስ የተሰጠ ምስጋና ከፌደራል ፖሊስ የተገኙት ኮማንደር ጌትነት በአስተባባሪዎች ላይ እስካሁን ምንም አይነት ችግር እንዳላዩ ጠቅሰው፣ ወጣቶቹ ከፖሊስ ባልተናነሰ መልኩ እየሰሩ መሆኑን መስክረዋል። ኮማንደሩ አክለውም፦ *"የናንተ ፕሮግራም በሰዓት የተገደበ በመሆኑ ለኛ ምቹ ነው፣ ከባድ ሁኔታ አይፈጥርም። አስተባባሪዎች ከፖሊስ እክል ባልተናነሰ መልኩ እገዛችሁን እንፈልጋለን። የተከለከሉ ነገሮችን አስቀድማችሁ በመናገር ምዕመናን ከማድረግ እንዲቆጠቡ ማድረግ ይኖርባችኋል፤ አታድርጉ የተባለውን ነገር 'አያስፈልግም' በማለት አርሟቸው፣ ተባበሩን። በአግባቡ እናስተናግዳለን፤ የጎደለ ነገር ካለ እናንተና ፈጣሪ ይሙላበት"* ብለዋል። ### የተግባራዊ ስራዎች ማጠቃለያ (Action Items) በኦረንቴሽኑ ማጠቃለያ ላይ አስተባባሪዎች በአስቸኳይ ወደ ስራ ሊገቡባቸው የሚገቡ ዋና ዋና ተግባራት ተለይተዋል፦ * የጠፉ ልጆችን ወደ ሜክሲኮ ተባረክ መስጂድ፣ ስታዲየም እና ፍልውሃ መስጂድ መውሰድ። * ካኪ መያዝ እንደማይቻል ለሕዝቡ አስቀድሞ ማሳወቅ። * ባነር፣ ቲሸርት፣ የፍልስጤም እና የኢራን ባንዲራዎችን ይዞ መግባት ክልክል መሆኑን መቆጣጠር። * ከምዕመናን የሚጠበቀው ኢዳችንን ሰግደው በሰላም መመለስ ብቻ መሆኑን ግንዛቤ መፍጠር። * የሴቶች ኮስሞቲክስ ዕቃዎች ላይ እራሳቸው ላይ አስሞክሮ ማሳለፍ። * ወንዶችንና ሴቶችን በተለያዩ መግቢያ አቅጣጫዎች መምራት።

በአረፋ በዓል አከባበርና ጸጥታ ዙሪያ ከአስተባባሪዎች ጋር የኦረንቴሽን መድረክ ተካሄደ አዲስ አበባ — የ1447ኛው ዓ.ሂ የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የራሳቸውን የ
+7
በአረፋ በዓል አከባበርና ጸጥታ ዙሪያ ከአስተባባሪዎች ጋር የኦረንቴሽን መድረክ ተካሄደ አዲስ አበባ — የ1447ኛው ዓ.ሂ የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የራሳቸውን የበኩclean አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና ከፌደራል ፖሊስ የተወከሉ ከፍተኛ የጸጥታ መኮንኖች ለአዘጋጅና አስተባባሪ ወጣቶች የኦረንቴሽን ስልጠና ሰጥተዋል። በበዓሉ ስነ-ስርዓት ላይ ስምሪት የተሰጣቸው አስተባባሪዎች ከቦሌ ክፍለ ከተማ፣ ከአራዳ ክፍለ ከተማ እና ከኮልፌ ክፍለ ከተማ የተወጣጡ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ሲሆኑ፣ በዓሉን ከማንኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ ነፃ በሆነ መልኩ በሃይማኖታዊ ስርዓቱ ብቻ አክብሮ ማጠናቀቅ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ እንዲሁም ፍተሻን፣ አስተናገድንና ልዩ ጥንቃቄዎችን በተመለከተ ጥብቅ መመሪያዎችና የተግባር አቅጣጫዎች ተላልፈዋል። ### የጠፉ ልጆችን በተመለከተ የተላለፈ ልዩ መመሪያ በበዓሉ ዕለት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ማህበራዊ እክሎችን አስቀድሞ ለመከላከል የተለየ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን፣ አስተባባሪዎችና ምዕመናን በስነ-ስርዓቱ ወቅት የጠፉ ልጆች ካሉ ወዲያውኑ ሰብስበው ወደሚከተሉት አስተማማኝ የእርዳታ ማዕከላት እንዲወስዷቸው በጥብቅ ታዟል፦

ነገ እሁድ ግንቦት 16/2018 ከአሱር ሶላት በኋላ አስኮ በድር መስጂድ የአንድነቱ ሜዳ በሚል ርዕስ ሰፋ ያለ የዳዕዋ ፕሮግራም በተወዳጁ ዳኢ ኡስታዝ ካሚል ጣሀ በአካባቢው እና በዙሪያው የምትገኙ ወ
ነገ እሁድ ግንቦት 16/2018 ከአሱር ሶላት በኋላ አስኮ በድር መስጂድ የአንድነቱ ሜዳ በሚል ርዕስ ሰፋ ያለ የዳዕዋ ፕሮግራም በተወዳጁ ዳኢ ኡስታዝ ካሚል ጣሀ በአካባቢው እና በዙሪያው የምትገኙ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ተጋብዛችኋል ።

የሐጅ አደራረግ ስልጠና በሸይኽ ኢልያስ አህመድ የቀጥታ ስርጭት ከመካ አያ ሆቴል!! https://www.facebook.com/share/v/17o5TGcPjr/

📌 ዙልሂጃ 5፡ ዱዓ እና ልመናን ማብዛት የልብ ፍላጎቶች የሚመለሱበት ወርቃማ ሰዓታት! 🤲🔥 እነዚህ ቀናት አላህ ዱዓን የሚቀበልባቸው፣ ባሮቹን ከእሳት ነፃ የሚያወጣባቸው ቀናት ናቸው። ፍላጎትህን
📌 ዙልሂጃ 5፡ ዱዓ እና ልመናን ማብዛት የልብ ፍላጎቶች የሚመለሱበት ወርቃማ ሰዓታት! 🤲🔥 እነዚህ ቀናት አላህ ዱዓን የሚቀበልባቸው፣ ባሮቹን ከእሳት ነፃ የሚያወጣባቸው ቀናት ናቸው። ፍላጎትህንና የዱንያ የአኺራ ጭንቀትህን ለአላህ የምታቀርብበት ወቅት አሁን ነው። 📖 ከቁርዓን፡ "ጌታችሁም አለ፦ ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና..." (ሱረቱ ጋፊር፡ 60) 💬 ከሐዲስ፡ ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ "በላጩ ዱዓ የአረፋ ቀን የሚደረግ ዱዓ ነው። እኔና ከእኔ በፊት የነበሩት ነቢያት ካልናቸው ቃላት ሁሉ በላጩ፦ 'ላ ኢላሀ ኢለላሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፣ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁዋ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር' የሚለው ነው።" (ቲርሚዚ) 📣 ትግበራ፦ ለራስህ፣ ለወላጆችህ፣ ለቤተሰብህ እንዲሁም ለኡማው ዱዓ ማድረግን እንዳትረሳ!