en
Feedback
HOP Ministry

HOP Ministry

Open in Telegram

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
445
Subscribers
+224 hours
+237 days
+6630 days
Number of Posts

Data loading in progress...

Reactions
Comments
Telegram Stars
TOP posts by

Data loading in progress...

Publication analysis
Posts
Views dynamics
Track_05_Filegaw_Aderegegn_ፍለጋው_አደረገኝ_Aster_Abebe_Vol_2128k.m4a
270101Loading...
4_5776310973908391561.m4a
445101Loading...
አስር_ጊዜ_ባይህ_10_gize_bayih_ዮሴፍ_አስቻለው_Yosef_Aschalew128k.m4a
71000Loading...
#Being_Empty_for_More እግዚአብሔር የትናንት አምላክ ብቻ አይደለም። የዛሬም ነው፤ ዛሬም ሕያው ነው። እርሱ ለማደስ እና እንደገና ለመስራት አቅም አያንሰውም። እግዚአብሔር ዛሬ ለመስራት ኃይል አንሶት በትናንት ትዝታ አይጠመድም፤ ዛሬም ሊሰራ፣ ሊያድስ የበረታ፤ የታመነም ነው። እግዚአብሔርን እና ኃይሉን ታምነን ሌላ አዲስ ክብር፣ ኃይል፣ መነካት እንናፍቃለን። እርሱም ማለዳ ማለዳ አዲስ የሆነ፤ ለብርታቱም ወሰን የሌለው አምላክ ስለሆነ ከትናንት በበለጠ ክብር ወደ እኛ ይመጣል። እግዚአብሔር ሆይ፣ እያየሁህ ይበልጥ እንድትስበኝ፣ እንድናፍቅህ አድርገኝ። በእግርህ ስር መንበርከክን ቀላል የሚያደርግ ፍቅር፣ ናፍቆትና መንፈሳዊ ረሃብ ስጠኝ! Being Empty for More God is not only the God of yesterday. He is also the God of today, and He is still alive and at work. He never lacks the power to renew and to do a new work. He has not grown weary or powerless. He is not confined to yesterday's memories. Today, He is still mighty to work, to restore, and to transform. Trusting in God and His power, we long for fresh glory, fresh power, and a fresh touch from Him. Because His mercies are new every morning and His power knows no limits, He comes to us with greater glory than yesterday. Emptying ourselves before God for more. Being thirsty and hungry to be filled by Him abundantly. Being not satisfied with less, but to receive more of Him. To be touched by His hands like never before. ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 27, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
535401Loading...
Emptying ourselves before God for more. Being thirsty and hungry to be filled by Him abundantly. Being not satisfied with less, but to receive more of Him. To be touched by His hands like never before. t.me/hopministry10
481100Loading...
_ምድር_ላይ_ካለው_ነገር_ዘማሪ_ሳሙኤል_አዴሎ_new_ethiopian_protestant_mezmur_True.m4a
633400Loading...
ሉቃስ 12 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁶ አምስት ድንቢጦች በዐሥር ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ይሁን እንጂ ከእነርሱ አንዷ እንኳ በእግዚአብሔር ዘንድ አትዘነጋም። ⁷ የእናንተ የራሳችሁ ጠጒር ሁሉ እንኳ የተቈጠረ ነው፤ እንግዲህ አትፍሩ፤ ከብዙ ድንቢጦች የበለጠ ዋጋ አላችሁ። Luke 12: 6-7 (ESV) "Are not five sparrows sold for two pennies?And not one of them is forgotten before God. Why, even the hairs of your head are all numbered. Fear not; you are of more value than many sparrows." #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
754203Loading...
4_5834464483203877310.mp3
779201Loading...
#በእግዚአብሔር_ታመኑ! ሉቃስ 12 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁵ ለመሆኑ፣ ከእናንተ ተጨንቆ በዕድሜው ላይ አንድ ሰዓት መጨመር የሚችል ማነው? ²⁶ እንግዲህ ቀላሉን ነገር እንኳ ማድረግ የማትችሉ ከሆነ፣ ስለ ሌላው ነገር ለምን ትጨነቃላችሁ? በ July 25, 2026 የቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ የተቀዳ ስብከት። t.me/hopministry10
820204Loading...
ሉቃስ 12 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁵ ለመሆኑ፣ ከእናንተ ተጨንቆ በዕድሜው ላይ አንድ ሰዓት መጨመር የሚችል ማነው? ²⁶ እንግዲህ ቀላሉን ነገር እንኳ ማድረግ የማትችሉ ከሆነ፣ ስለ ሌላው ነገር ለምን ትጨነቃላችሁ? ²⁷ “እስቲ አበቦች እንዴት እንደሚያድጉ ተመልከቱ፤ አይለፉም፤ አይፈትሉም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ፤ ሰሎሞን እንኳ በዚያ ሁሉ ክብሩ ከእነርሱ እንደ አንዷ አልለበሰም። ²⁸ እንግዲህ እግዚአብሔር ዛሬ ታይቶ ነገ ወደ እሳት የሚጣለውን የሜዳ ሣር እንዲህ የሚያለብስ ከሆነ፣ እናንተ እምነት የጐደላችሁ፣ እናንተንማ እንዴት አብልጦ አያለብሳችሁም? ²⁹ ስለዚህ ምን እንደምትበሉና ምን እንደምትጠጡ በመሻት ልባችሁ አይጨነቅ፤ ³⁰ ይህንማ በዓለም ያለ ሕዝብ ሁሉ ይፈልጋል፤ አባታችሁ እኮ ይህ ሁሉ እንደሚያስፈልጋችሁ ያውቃል። ³¹ ይልቁንስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ በተጨማሪ ይሰጣችኋል። #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
752201Loading...
📖 Hear. Obey. Practice. t.me/hopministry10
650100Loading...
ሉቃስ 12 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁵ “በአጭር ታጥቃችሁ ተዘጋጁ፤ መብራታችሁም የበራ ይሁን፤ ³⁶ ጌታቸው ከሰርግ ግብዣ እስኪመለስ እንደሚጠባበቁና መጥቶም በር ሲያንኳኳ ወዲያው ለመክፈት ዝግጁ የሆኑ ሰዎችም ምሰሉ። Luke 12: 35-36 (ESV) “Stay dressed for action and keep your lamps burning, and be like men who are waiting for their master to come home from the wedding feast, so that they may open the door to him at once when he comes and knocks." “ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና በመጠን ኖራችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ።”   — 1ኛ ጴጥሮስ 1፥13 (አማርኛ 1954) 1 Peter 1: 13 (ESV) "Therefore, preparing your minds for action, and being sober-minded, set your hope fully on the grace that will be brought to you at the revelation of Jesus Christ." #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
791201Loading...
📖 Hear. Obey. Practice. t.me/hopministry10
677200Loading...
📖 Hear. Obey. Practice. ኢየሱስን የማውቀው በመረጃ፣ በሰሚ ሰሚ እውቀት ነው፤ ወይስ እርሱን በመጠጋት? t.me/hopministry10
828202Loading...
#ኢየሱስን_በመጠጋት_ማወቅ! አንድን ሰው ቤተኛው፣ ቤተሰቡ፣ አብሮ ኗሪውና የተጠጋጋው ሰው በሚያውቀው ልክ ሌላው፣ የውጪ ሰው፣ አብዛኛው ሰው ሊያውቀው አይችልም። በውጪ ያለው አብዛኛው ሰው፦ ሰው ሁሉ በሰሚ ሰሚ የደረሰውና ሊያውቀው የሚችለው ጠቅለል ያለ እውቀት፣ መረጃ ይኖረዋል። ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ ሰውየውን ጨርሶ የማያውቀውም ይኖራል። ኢየሱስን ለማወቅ ከአብዛኛው ሰው የተለየ ሁነኛ መጠጋት፣ ከእርሱ ጋር መቆየት፣ መጠጋጋት ይጠይቃል። ኢየሱስ ማን መሆኑን የሚገልጥልን፣ የሚያስረዳን መንፈስ ቅዱስ ቢሆንም የተከፈተ ልብ፣ ሊያውቀው የተጋ ማንነት ደግሞ ከእኛ ይጠበቃል። ስለ ኢየሱስ አብዛኛው ሰው ሊያውቀው የሚችለው እውቀት አይደለም በአማኞች ዘንድ በአንዳንድ ንቁ ኢ-አማንያን እንዲሁም በአጋንንት ዘንድም ሞልቷል፤ ነገር ግን መጠጋትና ከእርሱ ሕይወትን መካፈል ይጎድለዋል። ኢየሱስን ሊያዩት ሊሰሙት፣ ሊዳስሱት፣ በእርሱ ሊነኩ ወደው የቀረቡት ግን ከቃላት ያለፈ የተካፈሉትና የቀዱት ሕይወት አላቸው። ኢየሱስ የመረጃና የእውቀት ጉዳይ ብቻ አይሆንባቸውም። ኢየሱስን የማውቀው በመረጃ፣ በሰሚ ሰሚ እውቀት ነው፤ ወይስ እርሱን በመጠጋት? የዛሬው ቁልፍ መልዕክቴ፦ HOP (Hear. Obey. Practice.) Hear፦ ኢየሱስን ከጠቅላላ እውቀት ባለፈ እርሱን በመጠጋት፣ ከእርሱ ጋር በመቆየት፣ በመነካት ማወቅ የተሰጠ ልብ፣ የሰከነ አእምሮ፣ በእግሮቹ ስር ለመሆን የተጋ ጉልበት ይጠይቃል። Obey፦ ኢየሱስን ለማወቅ፣ እርሱን ለመጠጋት፦ ሕይወታችንን እንቃኝ፤ ሊገኝለት ያልወደደውን ማንነታችንን እንግራ፣ ለእርሱ ለመገኘት ራሳችንን እናሰልጥን፣ ጊዜያችንን ለእርሱ ለመሰዋት መርህ እናብጅ፣ ከትንሽ ጀምረን ፍለጋችንን እያሳደግን እንሂድ። Practice፦ የጀመርነውን እርሱን መጠጋት ሳናቋርጥ፣ ድግግሞሹን እናስቀጥል፤ የሕይወት ስርዓታችን፣ በውሎአችን ውስጥ ያለ አንዱ የሕይወት ክፍላችን፣ ልማዳችን እስኪሆን ድረስ እንቆይበት። ““ፊቴን ፈልጉ” ባልህ ጊዜ፤ ልቤ እግዚአብሔር ሆይ፤ ፊትህን እሻለሁ አለች።”   — መዝሙር 27፥8 (አዲሱ መ.ት) ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 24, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
783503Loading...
#መንፈሳዊ_ግለትን_መጠበቅ! በተለምዶ ቀዝቃዛ ውሃ ወደ መፍላት የሚደርሰው የሚያገኘው ሙቀት እየጨመረ በሄደበት ልክ ነው። ቀዝቃዛ የነበረው ውሃ እሳት ሲያገኝ ለብ እያለ፣ እየሞቀ፣ እየሞቀ፣....እየሞቀ፣.....እየጋለ፣ ወደ መፍላት ይደርሳል። በተቃራኒው ደግሞ የፈላው ውሃም የሚቀዘቅዘው በአንድ ጊዜ ሳይሆን በጊዜ ሂደት ውስጥ ነው፤ ትኩሳትና ሙቀቱ እየቀነሰ፣ ለብ እያለ፣ በረድ እያለ፣ ወደ መቀዝቀዝ ይደርሳል። በሁለቱም ሂደት ውስጥ የሙቀቱ መጠን መለዋወጥ ነው የውሃውን ሁኔታ የሚወስነው። ማለትም የውሃው የሙቀት መጠን መጨመር ወይም መቀነስ፣ መውጣት ወይም መውረድ ውሃው በሚያገኘው የሙቀት መጠን ላይ ይወሰናል። መንፈሳዊ ሕይወታችንም ልክ እንደዚሁ የውሃ ምሳሌ ሲዋዥቅ እናስተውላለን። በምድር እስካለን ድረስ ላይ ወጥቶ የሚቀር መንፈሳዊ ሕይወት እንደሌለ ሁሉ ታች ወርዶ የሚቀርም የለም። ነገር ግን መንፈሳዊ ግለታችንን መጠበቅ የእኛ ድርሻ ነው። መንፈሳዊ ሕይወታችን እንዲጎለብት፣ ብስለት እንዲኖረን፣ በመንፈስ የጋልን እንድንሆን ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት ካልቆየን፣ የእግዚአብሔርን ቃል ካላጠናን፣ ካልጸለይን፣ በመንፈስ ቅዱስ ካልተሞላን፣ ከቅዱሳን ጋር ሕብረት ካላደረግን፣....... በአጠቃላይ በመንፈሳዊው ነገር ላይ #አተኩረን ዕለት ተዕለት መንፈሳችንን ካልመገብን፣ የውስጥ ሰውነታችንን ካላጠነከርን እያሽቆለቆልን ሄደን ለብታ ላይ መድረሳችን፣ መንፈሳዊ ሕይወታችንም ቀዝቃዛና በራድ መሆኑ #አይቀሬ! ነው። ስለዚህ መንፈሳዊ ግለታችንን አስጠብቆ ለመንቀሳቀስ የሕይወታችን ባለአደራ እንዲሁም መጋቢ ነን ማለት ነው። እኛ ያልሰራንበት፣ ያልመገብነው ሕይወታችን ከየትም መጥቶ እንደምንናፍቀው፣ እንደሚጠበቅበት ሊያድግና ሊያፈራ አይችልምና ዘወትር ራሳችን ላይ ለመስራት እንበርታ!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 23, 2024 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
928403Loading...
Lauren_Daigle_-_Once_And_For_All__Audio_(128k).m4a
762200Loading...
Once and for All Song by Lauren Daigle ‧ 2015 "God I give You all I can today These scattered ashes that I hid away I lay them all at Your feet From the corners of my deepest shame The empty places where I've worn Your name Show me the love I say I believe Oh Help me to lay it down Oh Lord I lay it down Oh let this be where I die My lord with thee crucified Be lifted high as my Kingdom's fall Once and for all, once and for all There is victory in my Saviors loss And In the crimson flowing from the cross Pour over me, pour over me yes Oh let this be where I die My lord with thee crucified Be lifted high as my Kingdom's fall Once and for all, once and for all Oh Lord I lay it down Oh Lord I lay it down Help me to lay it down Oh Lord I lay it down Oh let this be where I die My Lord with thee crucified Be lifted high as my Kingdom's fall Once and for all Once and for all Oh once and for all Once and for all"
851500Loading...