የቀጠናው ተመልካች
Open in Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
4 330
Subscribers
-924 hours
-407 days
-8130 days
Posts Archive
4 331
🇷🇺🇺🇦⚡️— ዘለንስኪ እና የዩክሬን ባለስልጣናት አለን ባሉት የደህንነት መረጃ መሠረት፣ በጸደይ ወቅት በሩሲያ 500 ሺህ ወታደሮች ክተት እንደሚቀሰቀሱ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ዘለንስኪ ዛሬ፣ ከሰሜን ኮሪያ 30 ሺህ ወታደሮች ከሩሲያውያን ጋር እንደሚቀላቀሉ ተናግሯል።
*-*-*-
ውነት ነው? ውኀት ይመስላል።
የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ፣ ሩሲያ ከሞላ ጎደል ጦርነቱን በበላይነት በምትመራበት ወቅት፣ ከ12-15ሺ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ከሩሲያ ጎን ተሰልፈው ተዋግተዋል።
የሩሲያ ጦር በደህና ደረጃ በነበረበት ወቅት።
ዛሬ ግን፣ ያ ጦር እንደ ትናንቱ አይደለም፣ እናም 30ሺ የሰሜን ኮርያ ወታደራዊ አባላት ሊቀላቀሉ ነው የሚለው የዘለንስኪ ንግግር ውነት ሊሆን ይችላል።
በሌላ በኩል ደግም፣ በታሪክ፣ የሩሲያ ጦር በውጊያ በቆየ ቁጥር፣ እየጠነከረ እና እየሰላ የሚሄድ ጦር ነው። የሶቪየት ጦር በታሪኩ፣ ሌሎች ሲቆዩ እንደሚዳከሙት፣ የሚዳከም ተፈጥሮ የለውም። ሲቆይ ይጠነክራል። ስለዚህ በዚያ ስሌት መሠረት፣ የዘለንስኪ 30ሺ የሚለው ንግግር፣ ከፕሮፓጋንዳ የዘለለ ላይሆን ይችላል።
አንድ ነገር ግን ግልጽ ነው፣ ጦርነቱ ከምንግዜውም በላይ ከፍቷል።
4 331
🇷🇺🇺🇦⚡️— ዘለንስኪ እና የዩክሬን ባለስልጣናት፣ አለን ባሉት የደህንነት መረጃ መሠረት፣ በጸደይ ወቅት በሩሲያ 500 ሺህ ወታደሮች ክተት እንደሚቀሰቀሱ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ዘለንስኪ ዛሬ፣ ከሰሜን ኮሪያ 30 ሺህ ወታደሮች ከሩሲያውያን ጋር እንደሚቀላቀሉ ተናግሯል።
*-*-*-
ውነት ነው? ይመስላል። የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ፣ ሩሲያ ከሞላ ጎደል ጦርነቱን በበላይነት በምትመራበት ወቅት፣ ከ12-15ሺ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ከሩሲያ ጎን ተሰልፈው ተዋግተዋል።
የሩሲያ ጦር በደህና ደረጃ በነበረበት ወቅት።
ዛሬ፣ ጦሩ እንደትናንቱ አይደለም፣ እናም 30ሺ የሰሜን ኮር ጦር አባላት ሊቀላቀሉ ነው የሚለው ሊያስኬድ ይችላል።
በሌላ በኩል ደግም፣ በታሪክ፣ የሩሲያ በውጊያ በቆየ ቁጥር፣ እየጠነከረ እየሰላ የሚሄድ ጦር ነው። ሌሎች ሲቆዩ እንደሚዳከሙት፣ የሚዳከም ተፈጥሮ ጦሩ የለው። ስለዚያ በዚያ ስሌት መሠረት የዘለንስኪ 30ሺ ፕሮፓጋንዳ ሊሆን ይችላል።
አንድ ነገር ግልጽ ነው። ጦርነቱ ከምንግዜውም በላይ ከፍቷል።
4 331
🇮🇷🇺🇦⚡️የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለዩክሬን መንግሥት ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።
ኢራን እራሷን እና ብሔራዊ ጥቅሞቿን ለመከላከል በፍጹም ወደ ኋላ አትልም። ማንም ይህን ሊጠራጠር አይገባም። በዩክሬን፣ የአገዛዙ መሪ [ዜሌንስኪ] በወሰደው የእብሪት እርምጃ ተከትሎ ለሚመጣው መዘዝ፣ ሃላፊነቱ ሙሉ በሙሉ በዚያ አገዛዝ እና በደጋፊዎቹ እና በአመራሮቹ ላይ ይሆናል።
4 331
🇩🇪 የጀርመን መንግስት፣ ከሳምንታት በፊት የሆርሙዝ ወሽመጥ መከፈትን ተከትሎ፣ በቀጠናው የደህንነት ተልዕኮን ለመደገፍ ልኳቸው የነበሩ ሁለት የባሕር ኃይል መርከቦቹን፣ እየመለሰ ነው፣
📌 ይህ ውሳኔ የተወሰደበት ምክንያት፣ በበርሊን ውስጥ በኢራን ያለው ግጭት በቅርቡ ያበቃል የሚል ተስፋ እየጠፋ በመሆኑ እና የአሜሪካ ወታደሮች መሞት (እና ከ400 በላይ የቆሰሉ) በመመልከት፣ በራሳቸው ወታደራዊ አባላት ላይ ተመሳሳይ ነገር እንዲደርስ ባለመፈለጋቸው ነው።
4 331
🇺🇸🇮🇷 ትራምፕ ስለ ኢራን፦ ከኢራን የምንፈልገውን 100% ካላገኘን፣ ሙሉ ስፋት ያለውን ጦርነት እንደገና ለመጀመር በእርግጠኝነት እናስባለን።
🎙️ ለአውሮፓውያን አጋሮችዎ መልእክት አለዎት? ትራምፕ፦ እኔን እንደ ጓደኛ በማግኘታቸው እድለኞች ናቸው።
4 331
🇮🇷‼️🇺🇦 የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ዩክሬን በካስፒያን ባሕር ውስጥ በኢራን የንግድ መርከብ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች፣ አንድ መርከበኛ ገድላለች እና ሌላውን ደግሞ አቁስላለች፣ ብሏል።
ጥቃቱን፣ የዓለም አቀፍ ሕግ ጥሰት እና የጥቃት ድርጊት፣ ብሎ አውግዞታል።
*-*-*-
ዩክሬን ኢራን እንደ ሩሲያ መስላት ይሆን?
4 331
🇮🇷‼️🇺🇦 የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ዩክሬን በካስፒያን ባሕር ውስጥ በኢራን የንግድ መርከብ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች፣ አንድ መርከበኛ ገድላለች እና ሌላውን ደግሞ አቁስላለች፣ ብሏል።
ጥቃቱን፣ የዓለም አቀፍ ሕግ ጥሰት እና የጥቃት ድርጊት፣ ብሎ አውግዞታል።
*-*-*-
ዩክሬን ኢራን እንደ ሩሲያ መስላት ይሆን?
4 331
🇮🇷🇺🇦⚡️የኢራን ቻናሎች፣ ዘለንስኪን እና ዩክሬንን እያስጠነቀቁ ናቸው። ይህን እያሉ ያሉት፣ ዘለንስኪ በካዝቢያን ባሕር ወደ ኢራን ይጓዙ የነበሩ የሩሲያ መርከቦችን ዩክሬን አጥቅታለች ማለቱን ተከትሎ ነው።
ከዚህ በፊትም፣ ጦርነቱ የተጀመረ ሰሞን፣ ዘለንስኪ ኢራንን ያልተገባ ነገር ተናግሮ ከመንግሥት ባለስልጣናት ማስጠንቀቂያዎች ደርሰውት ነበር።
ቀኝ ዘመም የኢራን የመንግሥት ባለስልጣናትም፣ በጊዜው ዩክሬን መመታት እንዳለባት ተናግረው ነበር።
ኢራኖች፣ አብዛኞቹ ሚሳዬሎቻቸው ሙሉ ዩክሬንን የሚሸፍኑ መሆናቸውንም ለዩክሬናዊያን እያስታወሷቸው ነው።
ለአቶ ዘለንስኪ በአክብሮት ማሳሰቢያ፦ መላው ዩክሬን እጅግ ከባድ የሆነውን Khorramshahr-4ን ጨምሮ በኢራን ባሊስቲክ ሚሳይሎች ተደራሽ ነው። ምንም እንኳን ጥሩ ሚሳይሎችን ማባከን ቢሆንም።
4 331
—❗️🇮🇷/🇷🇺/🇺🇦 የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎደሚር ዘለንስኪ፣ የዩክሬን ጦር ኃይሎች ወደ ኢራን የሚጓዝ የሩሲያ ወታደራዊ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት እንደፈፀሙ አስታውቋል።
4 331
—❗️🇾🇪/🇸🇦 የየመን ጦር ኃይሎች፣ በጃዛን የሚገኘውን የአራምኮ ነዳጅ ማጣሪያ እና በሳውዲ አረቢያ ያንቡ ውስጥ የሚገኘውን የአራምኮ ምስራቅ-ምዕራብ መተላለፊያ ትቦ፣ በበርካታ ባሊስቲክ ሚሳይሎች፣ ክሩዝ ሚሳይሎች እና ድሮኖች ዒላማ አድርጎ የመታ መሆኑን አስታውቋል።
የመን በተጨማሪ፣ እገዳ በእገዳ እና ጥቃት በጥቃት እንደሚመለስ አስታውቃለች።
4 331
+1
🇸🇦 የሳዑዲ ልዑል በለንደን ሆቴል በመጠጥ እና በአደንዛዥ ዕፅ ሞቶ ተገኘ።
ልዑል አብዱላህ ቢን ፋሐድ ቢን አብዱላህ ቢን አብዱል አዚዝ ቢን ጃላዊ አል ሳዑድ፣ በለንደን ማርዮት ሆቴል ባኞ ቤት በሠራተኛው ሞቶ ተገኝቷል።
ቀደም ብሎ ብዙ የአልኮል መጠጦች እና የፌሽታ አደንዛዥ ዕፆችን ወደ ክፍሉ እንዳዘዘ፣ በሰውነቱም ውስጥ ከተገቢው መጠን ከሦስት እጥፍ በላይ እንደተገኘ ፖሊስ በምርመራው አረጋግጧል።
በሳዑዲ፣ የንጉሣዊያን ቤተሰብ አባላት፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና ባለ ሃብቶች፣ በምዕራቡ ዓለም ባሉ ሆቴሎች እና መዝናኛዎች፣ ልቅ በሆነ መንገድ፣ ከሴተኛ አዳሪዎች፣ ከአደንዛዥ ዕፅ እና መጠጥ ጋር ሲዝናኑ ማየት የተለመደ ነው። በአንዳንድ አጋጣሚዎችም እንደዚሁ፣ ሞተው የተገኙ አሉ።
4 331
+2
🇸🇦🇾🇪⚡️በቃሽ የመን፣ በጣም አበዛሽው፣ በሳዑዲ ቀልድ የለም፣ አርፈሽ ተቀመጪ!
እረ ምናገባኝ፣ አርፌ ብቀመጥ። እኔንም መጥተው እንዳይመቱኝ ደግሞ። "ዘጋቢው እንዳይዘግብ በራሱ ላይ ዘገባ ሠሩበት" እንዳልባል።
ጀዛን ያላችሁ ሀበሾች፣ ገጠማችሁ። ዛሬ ሥራ የለም፣ መሥሪያ ቤታችሁ በየመን ሚሳዬል ተዘግቶላችኋል፣ እረፍታችሁን በቤታችሁ አጣጥሙ።
4 331
🇸🇦⚡️🇾🇪 በሳዑዲ ዓረቢያ ጀዛን ክፍለ ሀገር የሚገኘው የሀገሪቱ ግዙፍ የነዳጅ ኩባንያ፣ አርማኮ፣ በአሁኑ ሰዓት በከፍተኛ ሁኔታ እየነደደ ነው።
በተደጋጋሚ በደረሰበት የየመን ሚሳዬሎች ድብደባ፣ ከኩባንያው ማምረቻ ግቢ የሚወጣው ጭስም፣ ከተማዋን ሸፍኗት ይገኛል፣ እየወጡ እንዳሉ ዘገባዎች።
4 331
🇸🇦⚡️🇾🇪 የተረጋገጠ! የጅዳ እና የሪያድ አየር ማረፊያዎች፣በየመን ጥቃት ምክኒያት፣ በአሁኑ ሰዓት ለማንኛውም ዓይነት በረራዎች ዝግ መሆናቸው ታውቋል።
4 331
🇾🇪❌🇸🇦 | የየመን የሚሳይል ጥቃት በሳውዲ አረቢያ በአብዱላህ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ የሚገኘውን የአውሮፕላን ማረፊያ ዲስትሪክት አካባቢን ዒላማ አድርጓል።
የመበቀል የመጀመሪያ ደረጃዎች ላይ የምትገኘው የመን፣ አራምኮን እና ሌሎች የኃይል ተቋማትን ጨምሮ በሳውዲ አገዛዝ ሥር ያሉ ወሳኝ ዒላማዎችን ዒላማ አድርጋለች እና ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም ላይ ለማነጣጠር እንዳልተወላወለች ቀደም ሲል አረጋግጣለች።
4 331
🇸🇦⚡️🇾🇪 | ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት፣ ኃይለኛ ፍንዳታዎች በሳዑዲ አረቢያ እንደገና እንደተከሰቱ ይጠቁማሉ፣ ፍንዳታዎቹ በበርካታ ቦታዎች ላይ እንደተከሰቱ ሪፖርት ተደርጓል።
በሳዑዲ አረቢያ ጂዛን (ጃዛን) ፍንዳታዎች እንደተከሰቱ ሪፖርት ተደርጓል፣ በከተማዋ ላይ የጭስ ደመናዎች እየወጡ ነበር። በሳዑዲ አረቢያ ካሚስ ሙሻይት ተጨማሪ ፍንዳታዎች ሪፖርት ተደርገዋል። ዘገባዎች በተጨማሪ፣ የየመን ሚሳይሎች በሳዑዲ አረቢያ ወደምትገኘው ያንቡ እንደደረሱ ያመለክታሉ፣ በዚህም ምክንያት በመላው የያንቡ ግዛት የማንቂያ ደውሎች እና ያልተቋረጡ ሳይረኖች ተሰምተዋል።
የጂዳ አውሮፕላን ማረፊያም እንደተጎዳ ሪፖርት ተደርጓል፣ የማንቂያ ድምጽ ሲሰማ እና ወደ ሪያድ የሚጓዙ አውሮፕላኖች ወደ ኋላ እንደተመለሱ ወይም የመጠባበቂያ መንገዶች ውስጥ እንደገቡ ሪፖርት ተደርጓል።
4 331
🇮🇷 ኢራን፣ "አጭሬ" የተባለ ሰርጓጅ መርከብን በዋና ዋና አደባባዮች ላይ ለሕዝብ ማስተዋወቅ ጀምራለች።
ከ120-150 ቶን ያህል የሚመዝነው "አጭሬ"፣ ትላልቅ የአሜሪካ የባሕር ኃይል ሰርጓጅ መርከቦች ሊሰሩ በማይችሉባቸው ጥልቀት በሌላቸው የፋርስ እና የኦማን ውሃዎች ውስጥ፣ መሥራት የሚችል ሰርጓጅ ነው ተብሏል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ ዝቅተኛ ድምፅ ያለው፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ፈንጂ የሚሸከም፣ ፈንጂዎችንም በባሕር ውስጥ መቅበር የሚችል፣ በጥልቀት ሰርጎ የሚገባ እና በምዕራባዊያን መርከቦች ራዳሮች አሻራው በቀላሉ የማይሸተት መርከብ ነው፣ ተብሏል።
4 331
🇮🇷🇧🇭🇺🇸⚡- በባሕሬን ሳይረኖችና ፍንዳታዎችይሰማሉ። የአየር መቃወሚያዎችም እየተተኮሱ ናቸው።
አሜሪካ በበኩሏ፣ ኢራንን በመደብደብ ላይ ናት።
4 331
ሰበር ዜና | 🇧🇭 🇰🇼 🇦🇪 🇸🇦 🇮🇷 — በዎል ስትሪት ጆርናል ሪፖርት መሠረት፣ ባህሬን እና ኩዌት በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ በኢራን ላይ ሚስጥራዊ የአየር ጥቃቶችን አካሂደዋል — ይህም በቴህራን ላይ የመጀመሪያ ቀጥተኛ ወታደራዊ የበቀል እርምጃቸው ነው።
ጥቃቶቹ፣ የድሮን እና የሚሳይል ማከማቻ መጋዘኖችን እና ሌሎች ወታደራዊ ቦታዎችን ዒላማ አድርገው ነበር።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የስለላ እና የመከላከያ የአየር ሽፋን ሰጥታለች። ሳዑዲ አረቢያም በጦርነቱ ቀጣይ እርምጃዎቿን እየገመገመች ትገኛለች።
የባሕረ ሰላጤው መንግሥታት፣ የኢራን አገዛዝ ቀጣይ መኖር የረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ስጋታቸው እንደሆነ እያዩት ነው።
