የቀጠናው ተመልካች
Open in Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
4 330
Subscribers
-924 hours
-407 days
-8130 days
Posts Archive
4 333
🇺🇦🇺🇸 ፕሬዚዳንት ትራምፕ በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ሰላም ስለሚወርድበት ሁኔታ ለመወያየት እንደ ፈረንጆች July 28 በዋይት ሃውስ ከዘሌንስኪ ጋር ይገናኛሉ — የWH ባለሥልጣን ለCNN
'ጦርነቱን ለማቆም ጊዜው አሁን ነው።'
*-*-*-*
ዘለንስኪ ባልከው ቦታ ይገኛል፣ አያካብድም፣ flixable ነው፣ አይከብድምም።
ዘለንስኪ ከሩስያ በሁሉም ነገሯ ቁጫጭ የሆነች ሀገር እየመራ፣ በጠሩት ቦታ ስለሚገኝ፣ ለመወያየት ዝግጁ ስለሆነ እና ያሉትን የሚሰማ እና የሚታዘዝ ስለሚመስል፣ ይኸው፣ ሩሲያን የምታክል ሀገር ገጥሞ ከያዘ 4 ዓመት ሞላው።
ከምዕራቡ ዓለም ጋር ሩሲያ ያላት ግንኙነት የሆነው ቢሆን፣ ፑቲን እንደ ዘለንስኪ ወርዶ ለመነጋገር ይፈቅዳል? በአሜሪካን ታሪክ እንደ ትራምፕ ያለ ለሩሲያ የተመቸ መሪ የለም ይላሉ፣ እውነት ነው። ትራምፕ ከሩሲያ ጎን ነህ ተብሎ እስኪባል ድረስ ለፑቲን ፍራሽ ሆኖለታል። አንዳንዴም እራሱን እስከማሳነስ ደርሶ በሩን በመክፈት፣ በንግድ እና በዲፕሎማሲ ትስስር ለመፍጠር እጅግ ከፍተኛ የሚባል ጥረት አድርጓል። ፑቲን ግን ተለጠጠ። አያወራም፣ አይነጋገርም። ቢባል ቢሰራ፣ አልገናኝም፣ አልወያይም እያለ ከክሬምሊን ለመውጣት አልፈቀደም። ሲያስፈልግ የበታቾቹን ባለስልጣናት ይልካል፣ ከዚያ ውጭ አለቀ፣ ምንም የለም።
እና በጣም ከባድ ነገር ነው።
በሌላ በኩል ዘለንስኪን እንደምታዩት ነው፣ ጦርነት ያለበት ሀገር የሚመራ አይመስልም ከቦታ ቦታ ሲንጦለጦል።
4 333
🇮🇶/🇺🇦 የኢራቅ ብሔራዊ የደህንነት አማካሪ፣ ቃሲም አል-አቡዲ፣ የዩክሬን ሴሎች በመላው ኢራቅ ንቁ መሆናቸውን፣ በውሸት ባንዲራ ሥር (False flag) ጥቃቶችን በመፈጸም ላይ እንደሚሳተፉ ተናግሯል።
'የዩክሬን የስለላ ሴሎች በኢራቅ ውስጥ ጥቃቶችን ያካሂዳሉ እና የጥቃቶቹን ሃላፊነት ለተለያዩ አንጃዎች በሐሰት ይሰጣሉ።'
የዩክሬን ሴሎች በሉዓላዊ የኢራቅ ተቋማት ላይ ጥቃቶችን እንደፈፀሙ የተናገረው ቃሲም አል አቡዲ፣ በዚህ ወንጀል የተሳተፉ የዩክሬን ግለሰቦችን እና አካላትን አስረናል፣ ብሏል።
4 333
🇺🇦🇬🇧 የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር አንዲ በርናም፦
የዩክሬን ድሮኖችን ለመጠበቅ አዲስ የሀገር ውስጥ የጃሚንግ ቴክኖሎጂን እያቀረብን ነው።
ዒላማዎቻቸውን እንዲመቱ እና የዩክሬን ሰዎችን ሕይወት ለማዳን ይረዳቸዋል።
እንዲሁም ኢንዱስትሪዎቻችን በጋራ ሊያቀርቡት የሚችሉትን የፈጠራ ዓይነት ያሳያል።
*-*-*
የዩክሬን ፕሬዝዳንት አቶ ዘላለም (ዘለንስኪ)፣ እንደ ኔታንያንሁ፣ እጅግ በጣም ተፈላጊ ሰው ከመሆኗ የተነሳ፣ ትላልቅ የአውሮፓ ንጉሦችና መኳንንቶች እጇን ለመጨበጥ የሚፈልጓት ሰው ሆናለች።
እቺ ሰው ባሁኑ ሰዓት፣ በአውሮፓ ውስጥ አንዲት ተረስታ የቆየች፣ ጥግ ላይ በተራሮች መሃል፣ በሸለቆ ውስጥ ያለችን ሀገር፣ በመሪነት እየመራች እና ሩሲያ የምትባል፣ ባለ ብዙ ዝና እና ሀብት ያላት ሀገርን በሽፍታነት ለንጉሦቹ እየወጋችላቸው ትገኛለች፣ እነሱም ወደዋታል።
ሰውዬይቱ፣ ሩሲያን አርዳ በሰሃን ታቀርብላቸዋለች?
4 333
+5
— 🇸🇦 ባለፉት 48 ሰዓታት በሳውዲ ዓረቢያ ውስጥ በተሳካ ሁኔታ ዒላማ የተደረጉ የነዳጅ ተቋማት እና ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ኢንዱስትሪዎች፦
– ሳውዲ አራምኮ፣ የጀዛን ማጣሪያ ኢንዱስትሪ (16.8841879, 42.5803417)
– ሳውዲ አራምኮ፣ በጀዛን ከተማ የነዳጅ ማከማቻ ማጠራቀሚያዎች (16.8742617, 42.5605715)
– ሳውዲ አራምኮ፣ የአብቃይቅ ማጣሪያ ኢንዱስትሪ (25.9282786, 49.6842320) ናቸው።
የሳዑዲ አረቢያ ዜጎች፣ "በአየር መቃወሚያ መትቶ ለመጣል ችግሩ ምንድነው?" እያሉ በሶሻል ሚዲያዎች ሲጠይቁ ታይተዋል።
አሜሪካ በገጠማት የዩክሬን እና አሁን ደግሞ የኢራን ጦርነቶች ምክኒያት፣ አብዛኛውን ውድ ውድ የአየር መቃወሚያ ሚሳዬሎቿን በመጠቀሟ የተነሳ ብዛቱ ስለተመናመነ፣ በጥበቃዋ ላይ አሥርተ ዓመታትን ተማምና የኖረችው ሳዑዲ ዓረቢያ ተጋላጭ ልትሆን ችላለች።
አሜሪካ ቀድማ በገልፍ ሀገሮች ላይ የጨረሰችውን ሚሳዬሎች ለማካካስም፣ ሰሞኑን ሳዑዲ ዓረቢያ የግሪክን አየር መቃወሚያ ገዝታ ጥቅም ላይ እያዋለች ትገኛለች።
*-*-*-
ሳዑዲ ግሪክ ከመሄድ ይልቅ ሜቴክ ብትመጣ፣ በርካሽ እንሸጥላት ነበር፣ የኢትዮጵያን አየር መቃወሚያ። የኛ ሮኬቶች ችግራቸው ለምሳሌ ሪያድ ሰማይ ላይ ስትተኩሰው ወደ መካ ሄዶ ያልሆነ ቦታ ሊመታብህ ይችላል።
*-*-*-*-
4 333
🇸🇦⚡️ ከሪያድ በስተምስራቅ የሚገኝን ግዙፍ የነዳጅ ኢንዱስትሪ ሊመቱ ከኢራቅ ተተኩሰው የነበሩ ድሮኖች፣ ዒላማቸውን ሳይመቱ በሪያድ ሰማይ ላይ በአየር መቃወሚያ መውደቃቸውን ሳዑዲ ገለፀች።
ሳዑዲ ዓረቢያ ለኢራቅ ሚሊሺያዎች ጥቃት ኢራንን በቀጥታ ተጠያቂ ያደረገች ሲሆን፣ እራሷን የመከላከል ብሎም አስፈላጊ መስሎ ሲታያት የማጥቃት ሙሉ መብት እንዳላት አስረግጣ ተናግራለች።
4 333
🇷🇺🇺🇦❗️"ከጥቂት ጊዜ በኋላ ዩክሬን ከስታሊን የተሰጣትን የምዕራብ ግዛቶቿን እንደምታጣ እርግጠኛ ነኝ – እና ሁሉም ነገር ወደ ቀድሞ ባለቤቶቹ፣ ወደ ሃንጋሪ፣ ሮማኒያ እና ፖላንድ ይመለሳል፣" - የሩሲያ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን።
ፑቲን በተጨማሪም፣ "ሩሲያ የዩክሬንን ግዛታዊ አንድነት ብቸኛ ዋስትና ሰጪ ሀገር ነበረች፣ እስከ አሁን ድረስ። ነገር ግን ዛሬ፣ ኪየቭ ሞስኮን ጠላት አድርጋ አውጃለች።
4 333
🇮🇷🇺🇦⚡️የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ፣ ዘለንስኪን፤ 'በነፃ አግበስባሽ' (freeloader) ብሎ ጠርቶታል።
በኢራን የጭነት መርከብ ላይ ላደረስከው ጥቃትም፣ "ሳንመልስልህ አንቀርም" ብሎታልም።
4 333
🇮🇷🇺🇸⚡- "አሜሪካ እና ኢራን ውይይቶችን ለመቀጠል ለፓኪስታን-ኳታር ሓሳብ ምላሻቸውን ሰጥተዋል" - አል-አረቢያ።
ኢራን፡ "አሜሪካ ትንኮሳ እስካልፈጸመችብኝ ድረስ አላጠቃትም፣ የአሜሪካ እና የጽዮናዊያን አጋር አረቦችንም እንቅልፍ፣ አልረብሽም "- ሮይተርስ
4 333
🇺🇸⚡️— የዋይት ሃውስ ኦፊሴላዊ የX አካውንት ሳይንስ ፊክሽን ዘይቤ ያለው ቪዲዮ በሚከተለው መግለጫ አውጥቷል፣ "ውስጥ ይግቡ... እስካሁን የተጋለጠውን ሥራ ይመልከቱ።"
4 333
⚡️🇮🇱🇮🇷 Ynet ፦ በእስራኤል የዓለም የአይሁድ ኮንግረስ ፕሬዝዳንት የሆኑት ሲልቫን አዳምስ፣ በፓሪስ ውስጥ ከኢራን የዘውድ ወራሽ ረዛ ፓህላቪ ጋር ተገናኝተዋል፣
እሱም፣ ፕሬዝዳንድ ትራምፕን በስም ሳይጠቅስ ኮንኖታል፣ በኢራን ውስጥ የተካሄዱትን የተቃውሞ ሰልፎች በኃይል ስለመቋጨቱም በምሬት አንስቷል።
"በቅርቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢራናውያን ተገድለዋል። የባሕር መተላለፊያ እንዲዘጋላቸው ወይም ክፍት ሆኖ እንዲቆይ ወይም ለኒውክሊየር ስምምነት አልሞቱም። ለነፃነት ሞተዋል፣"
4 333
🇮🇷⚡️🚢 አልጃዚራ እንደዘገበው፣ ከኢራን ባለስልጣናት ጋር እንቅስቃሴውን ማስተባበር ያልቻለ ታንከር መርከብ በሆርሙዝ ወንዝ ላይ ፈንድቷል።
ፍንዳታው የተከሰተው መርከቡ በኢራን ጦር ኃይሎች ከተደነገገው መንገድ ከወጣ በኋላ የባሕር ፈንጂ በመምታቱ ነው።
ሕትመቱ፣ ታንከሩ የሚጓዝበትን ባንዲራ ጨምሮ ተጨማሪ ዝርዝሮችን አላቀረበም።
4 333
🇸🇦🇾🇪⚡️በሳውዲ የሚደገፉት የአል-ጁወይድ ጎሣች እና ሚሊሺያዎች፣ ሁቲዎችን ፊት ለፊት ለመግጠም ወታደራዊ ኃይሎቻቸውን ወደ ማዕሪብ እና አል-ጀውፍ እንዲሁም ወደ ሁደይዳ እና ሰነዓ አቅራቢያ እያጓጓዙ ናቸው።
ምሽቱን፣ በሁቲ ኃይሎች ላይ ጥቃት ከፍተው የነበረ ሲሆን፣ አራት ኬላ ጠባቂዎችን የገደሉበትን ቪዲዮ አሰራጭተዋል። በተጨማሪም በርካታ የሁቲ ወታደራዊ መኪናዎችን አቃጥለው ታይተዋል።
ይህ ዓይነት አካሄድ በተለምዶ፣ ለሳውዲ አረቢያ እና ለምትደግፋቸው ጎሣዎች መጥፎ ሆኖ ተገኝቷል።
4 333
🇷🇺🇺🇦⚡️— ዘለንስኪ እና የዩክሬን ባለስልጣናት አለን ባሉት የደህንነት መረጃ መሠረት፣ በጸደይ ወቅት በሩሲያ 500 ሺህ ወታደሮች ክተት እንደሚቀሰቀሱ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ዘለንስኪ ዛሬ፣ ከሰሜን ኮሪያ 30 ሺህ ወታደሮች ከሩሲያውያን ጋር እንደሚቀላቀሉ ተናግሯል።
*-*-*-
ውነት ነው? ውኀት ይመስላል።
የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ፣ ሩሲያ ከሞላ ጎደል ጦርነቱን በበላይነት በምትመራበት ወቅት፣ ከ12-15ሺ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ከሩሲያ ጎን ተሰልፈው ተዋግተዋል።
የሩሲያ ጦር በደህና ደረጃ በነበረበት ወቅት።
ዛሬ ግን፣ ያ ጦር እንደ ትናንቱ አይደለም፣ እናም 30ሺ የሰሜን ኮርያ ወታደራዊ አባላት ሊቀላቀሉ ነው የሚለው የዘለንስኪ ንግግር ውነት ሊሆን ይችላል።
በሌላ በኩል ደግም፣ በታሪክ፣ የሩሲያ ጦር በውጊያ በቆየ ቁጥር፣ እየጠነከረ እና እየሰላ የሚሄድ ጦር ነው። የሶቪየት ጦር በታሪኩ፣ ሌሎች ሲቆዩ እንደሚዳከሙት፣ የሚዳከም ተፈጥሮ የለውም። ሲቆይ ይጠነክራል። ስለዚህ በዚያ ስሌት መሠረት፣ የዘለንስኪ 30ሺ የሚለው ንግግር፣ ከፕሮፓጋንዳ የዘለለ ላይሆን ይችላል።
አንድ ነገር ግን ግልጽ ነው፣ ጦርነቱ ከምንግዜውም በላይ ከፍቷል።
4 333
🇷🇺🇺🇦⚡️— ዘለንስኪ እና የዩክሬን ባለስልጣናት፣ አለን ባሉት የደህንነት መረጃ መሠረት፣ በጸደይ ወቅት በሩሲያ 500 ሺህ ወታደሮች ክተት እንደሚቀሰቀሱ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ዘለንስኪ ዛሬ፣ ከሰሜን ኮሪያ 30 ሺህ ወታደሮች ከሩሲያውያን ጋር እንደሚቀላቀሉ ተናግሯል።
*-*-*-
ውነት ነው? ይመስላል። የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ፣ ሩሲያ ከሞላ ጎደል ጦርነቱን በበላይነት በምትመራበት ወቅት፣ ከ12-15ሺ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ከሩሲያ ጎን ተሰልፈው ተዋግተዋል።
የሩሲያ ጦር በደህና ደረጃ በነበረበት ወቅት።
ዛሬ፣ ጦሩ እንደትናንቱ አይደለም፣ እናም 30ሺ የሰሜን ኮር ጦር አባላት ሊቀላቀሉ ነው የሚለው ሊያስኬድ ይችላል።
በሌላ በኩል ደግም፣ በታሪክ፣ የሩሲያ በውጊያ በቆየ ቁጥር፣ እየጠነከረ እየሰላ የሚሄድ ጦር ነው። ሌሎች ሲቆዩ እንደሚዳከሙት፣ የሚዳከም ተፈጥሮ ጦሩ የለው። ስለዚያ በዚያ ስሌት መሠረት የዘለንስኪ 30ሺ ፕሮፓጋንዳ ሊሆን ይችላል።
አንድ ነገር ግልጽ ነው። ጦርነቱ ከምንግዜውም በላይ ከፍቷል።
4 333
🇮🇷🇺🇦⚡️የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለዩክሬን መንግሥት ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።
ኢራን እራሷን እና ብሔራዊ ጥቅሞቿን ለመከላከል በፍጹም ወደ ኋላ አትልም። ማንም ይህን ሊጠራጠር አይገባም። በዩክሬን፣ የአገዛዙ መሪ [ዜሌንስኪ] በወሰደው የእብሪት እርምጃ ተከትሎ ለሚመጣው መዘዝ፣ ሃላፊነቱ ሙሉ በሙሉ በዚያ አገዛዝ እና በደጋፊዎቹ እና በአመራሮቹ ላይ ይሆናል።
4 333
🇩🇪 የጀርመን መንግስት፣ ከሳምንታት በፊት የሆርሙዝ ወሽመጥ መከፈትን ተከትሎ፣ በቀጠናው የደህንነት ተልዕኮን ለመደገፍ ልኳቸው የነበሩ ሁለት የባሕር ኃይል መርከቦቹን፣ እየመለሰ ነው፣
📌 ይህ ውሳኔ የተወሰደበት ምክንያት፣ በበርሊን ውስጥ በኢራን ያለው ግጭት በቅርቡ ያበቃል የሚል ተስፋ እየጠፋ በመሆኑ እና የአሜሪካ ወታደሮች መሞት (እና ከ400 በላይ የቆሰሉ) በመመልከት፣ በራሳቸው ወታደራዊ አባላት ላይ ተመሳሳይ ነገር እንዲደርስ ባለመፈለጋቸው ነው።
4 333
🇺🇸🇮🇷 ትራምፕ ስለ ኢራን፦ ከኢራን የምንፈልገውን 100% ካላገኘን፣ ሙሉ ስፋት ያለውን ጦርነት እንደገና ለመጀመር በእርግጠኝነት እናስባለን።
🎙️ ለአውሮፓውያን አጋሮችዎ መልእክት አለዎት? ትራምፕ፦ እኔን እንደ ጓደኛ በማግኘታቸው እድለኞች ናቸው።
4 333
🇮🇷‼️🇺🇦 የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ዩክሬን በካስፒያን ባሕር ውስጥ በኢራን የንግድ መርከብ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች፣ አንድ መርከበኛ ገድላለች እና ሌላውን ደግሞ አቁስላለች፣ ብሏል።
ጥቃቱን፣ የዓለም አቀፍ ሕግ ጥሰት እና የጥቃት ድርጊት፣ ብሎ አውግዞታል።
*-*-*-
ዩክሬን ኢራን እንደ ሩሲያ መስላት ይሆን?
