LOGOS
Open in Telegram
🎯የቻናሉ ዓላማ:LOGOS የሚለው ቃል ከGreek የመጣ ሲሆን፦ትርጉሙም ቃል፣ ምክንያት፣ክርስቶስ (የእግዚአብሔር ቃል ዮሐ 1፥1) በዚህ ቃል እውቀታችንን አሳድገን በኑሮ እንድንተገብር ነው
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
262
Subscribers
+124 hours
+127 days
+2530 days
Posts Archive
262
#ከፍል_3 የኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን (incarnation )
ለ.##የሰውነት_ባህሪያት_(የሰው ድክመትና_ውስንነት)...
1.ኢየሱስ እንደ እኛ ያለ አካል እንደነበረው መፅሐፍ ቅዱሳችን ብዙ ቦታ ይናገራል
📌ማንኛውም ህፃን እንደሚወለድ ተወለደ( ሉቃ 2፡52) እንደልጆች በጥበብ ፣በዕውቀት ፣ በቁመት ያድግ ነበረ (ሉቃ 2:40,52)
📌↖️ ይደክመው ነበረ (ዮሐ 4:6)
ልክ እኛን እንደሚደክመን እርሱንም ይደክመው ነበረ ፤
↖️ ይርበው ነበረ(ማቴ 4:2)
↖️ይጠማው ነበረ( ዮሐ 19:28)
↖️መላእክት ያገለግሉት ነበረ( ማቴ 4:11)
↖️ነፍሱን በእግዚአብሔር አጅ አደረ ሰጠ (ሉቃ 23:46)
📌ከሞትም ሲነሳ ሰብዓዊ አካሉ በሙሉ በትንሣኤ አካል ተነስቷል ። ስለሆነም ስጋና አጥንት ያለው አካል እንጂ መንፈስ አልነበረም ( ሉቃ 24:39)
በፊታቸውም ምግብ በልቷል (ሉቃ 24:42, ዮሐ 20:17,20,27 ዮሐ 21:9,13)
↗️ኢየሱስ በዚው አካል ሰማይም ይኖራል ።
2.ኢየሱስ ሰብዓዊ አዕምሮ ነበረው ፦
“ኢየሱስ በጥበብ.. አደገ”(ሉቃ 2:52) ኢየሱስ እንደ እኛው በመማር ህዳት እንዳሳለፈ ይህ ክፍል ይናገራል ።
እንዴት እንደሚበላ ፣ እንዴት እንደሚናገር ፣ እንዴት እንደሚያነብ ፣ ለወላጆቹ እንዴት እንደምታዘዝ (ዕብ 5:8)
3.ኢየሱስ ሰብዓዊ ነፍስና ፤ ሰብዓዊ ጥልቅ ስሜት ነበረው፦
ኢየሱስ ሰብዓዊ ነፍስ እንደነበረው የሚያመላክቱ ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አሉ ።
↗️ነፍሱ ትታወክ ነበረ (ዮሐ 12:27),
↗️በመንፈሱ ይታወክ ነበረ ( ዮሐ 13:21)
↗️ነፍሱ ታዝን ነበረ (ማቴ 26:38)
↗️ይደነቅ ነበረ (ማቴ 8:10)
↗️ያዝንና ያለቅስ ነበረ (ዮሐ 11:35)
↗️በመራራ ጩኸትና እንባ ይፀልይ ነበረ (ዕብ 5:7)
📌ነፍስ 3 ክፍሎች አሏት 1.ስሜት
2.ፈቃድ
3.ዕውቀት
ክፍል 4 ይቀጥላል ... ✍️ወንድም አሻግሬ
262
እግዚአብሔርን #በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ብቻ ማወቅ ሳይሆን ፣ ራሳችንንም የምናውቀው #በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ብቻ ነው ፤ ህይወትና ሞትንም የምናውቀው #በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው ።#በኢየሱስ በኩል ካልሆነ በቀር የሕይወታችንንም ሆነ የሞታችንን ምስጥር ፤ የራሳችንንም ሆነ የእግዚአብሔርን ማንነት ለማወቅ አንችልም ። ”
(✍️ብሌይዝ ፓስካል )
“እግዚአብሔርን ማን እንደሆነ ለማወቅ ከፈለጋችሁ ኢየሱስን ተመልከቱ። ሰው መሆን ምን ማለት እንደሆነ ለማወቅ ከፈለጋችሁ #ኢየሱስን ተመልከቱ ። ፍቅር ምን እንደሆነ ለማወቅ ከፈለጋችሁ #ኢየሱስን ተመልከቱ። ሐዘን ምን እንደሆነ ለማወቅ ከፈለጋችሁ #ኢየሱስን ተመልከቱ።
( ✍️ ኤን ቲ ራይት )
ይሄን ጣፋጭ የሆነውን ኢየሱስን ማጥናት(እርሱን ማወቅ) ነፍስን ያሳርፋል ፤ ነፍስን ማሳረፍ ብቻ ሳይሆን ነፍስን ያሰፋል
#ኢየሱስ_ጣፋጭ_ነህ_እለት_እለት_ልብለህ🤲 ትላንት ##ክፍል_2 "የኢየሱስ ሰው መሆን"(incarnation ) የሚለውን ርዕስ ጀምረን ነበር ዛሬም እንቀጥላለን ...
262
#ክፍል 2 የኢየሱስ ክርስቶስ ሰብዓዊነት ( incarnation) ወይም “ሰው መሆን”
📌ሀ.ከድንግልና መወለዱ ፦ ስለ ክርስቶስ “ሰው” ወይም “incarnation” ስንናገር #ከድንግል መወለዱን ከግንዛቤ በማስገባት ብንጀምር በጣም ይጠቅማል ።
#ኢየሱስ ያለ ምንም ሰብዓዊ አባት አባት በመንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ተዓምራዊ ስራ በእናቱ በማርያም ማሕፀን እንደ ተፀነሰ መፅሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያረጋግጣል ። (...እናቱ ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ሳይገናኙ፣ በመንፈስ ቅዱስ #ፀንሳ ተገኘች።ማቴዎስ 1:18)
👉ይገርማል! ግን በሰው አዕምሮ የማይተሰብ ነገር ሆነ ፣ ኢየሱስ #ከድንግል ተወለደ፤ #ድንግል እንዴት ትወልዳለች !
ይሄንን ስላለመኑ ነው የአለም ጠቢባን ሞኞች ሆነው የቀሩት ፤ እኛ ለአለም ሞኞች ሆነን ፤ በእግዚአብሔር ጥበብ ስላመንን (ድንግል መውለዷን ስላመንን) ጠብባን ሆንን !
📌 ኢየሱስ ##ከድንግል መወለዱ ለትምህርታችንም ለሕይወታችንም ትልቅ ጠቀሜታ አለው ( ሶስት ዋና ዋና ነገሮች)
1.#ደህንነት ከቶ ፣ በፍጹም በሰው ጥረት እንደማይመጣ ፤ የእግዚአብሔር ስራ ብቻ እንደሆነ እንረዳለን ! እግዚአብሔር፦ የሴቲቱ “ዘር” (ዘፍ 3፡15) በመጨረሻ የእባቡን ዘር እንደሚያጠፋ ቃል በገባው መሠረት ፣ በሰው ጥረት ሳይሆን በገዛ ኃይሉ እውን አደረገው።
የክርስቶስ ከድንግል መወለድ ፣ #ድነት #የእግዚአብሔር የራሱ ስራና ፣ የእኛ እጅ ያልታከለበት ፣ ከቶ በሰው ጥረት እንዳልሆነ የሚያሳስብ ብርት ትምህት ነው።
🚨ድነታችን በእግዚአብሔር መለኮታዊ ስራ ብቻ የሚፈፀም ነው ። ( ...ነገር ግን የተወሰነው ዘመን በደረሰ ጊዜ፣ እግዚአብሔር #ከ“ሴት” የተወለደውን፣ ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤
5 ይህም የሆነው #የልጅነትን መብት እናገኝ ዘንድ ከሕግ በታች ያሉትን ለመዋጀት ነው።ገላትያ 4:4-5)
2. ኢየሱስ ከድንግል መወለዱ #ፍፁም #አምላክነትና #ፍፁም #ሰውነት በአንድ አካል እንዲዋሐዱ አደረገ። እግዚአብሔር ልጁን ወደ አለም ለመላክ የተጠቀመበት ዘዴ ይህ ነበር ( ዮሐ 3፡16 ገላ 4፡4)
#ኢየሱስ ያለ ምድራዊ ወላጅ(ያለ ማርያም)ከሰማይ ስጋ እንደለበሰ ሙሉ ሰው ሆኖ ቢገለጥ እንደኛ ያለ ፍፁም ሰው መሆኑን #ማረጋገጥ አይቻልም ።
#ኢየሱስ ከእናትና ከስጋ አባት እንደኛ የተወለደ ቢሆን ፍፁም አምላክ መሆኑን ፈጽሞ #ማረጋገጥ አይቻልም ።
3.የክርስቶስ ከድንግል መወለዱም "የውርስ ኃጢአት" ሳይኖርበት እውነተኛ ሰው እንዲሆን ያስችለዋል ።
+ ኢየሱስም ሌሎች ሰዎች ከአዳም እንደተገኙ በተመሳሳይ ከአዳም አልተገኘም ፣ የስጋ አባት የለውም። ይህም የሰው ሁሉ ሕጋዊ በደልና ብልሹ ግብረገብ ክርስቶስ እንዳልወረሰ ያስረዳል ።
+ በተጨማሪ በማርያም ማህፀን ውስጥ መንፈስ ቅዱስ የሰራውን ስራ ማየትም ጠቃሚ ነው (ሉቃ 1፡35)።
ለ.የሰውነት ባህሪያት ( የሰው ድክመትና ውስንነት)...
ይቀጥላል ...
262
#ክፍል 2 የኢየሱስ ክርስቶስ ሰብዓዊነት ( incarnation) ወይም “ሰው መሆን”
📌ሀ.ከድንግልና መወለዱ ፦ ስለ ክርስቶስ “ሰው” ወይም “incarnation” ስንናገር #ከድንግል መወለዱን ከግንዛቤ በማስገባት ብንጀምር በጣም ይጠቅማል ።
#ኢየሱስ ያለ ምንም ሰብዓዊ አባት አባት በመንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ተዓምራዊ ስራ በእናቱ በማርያም ማሕፀን እንደ ተፀነሰ መፅሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያረጋግጣል ። (...እናቱ ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ሳይገናኙ፣ በመንፈስ ቅዱስ #ፀንሳ ተገኘች።ማቴዎስ 1:18)
👉ይገርማል! ግን በሰው አዕምሮ የማይተሰብ ነገር ሆነ ፣ ኢየሱስ #ከድንግል ተወለደ፤ #ድንግል እንዴት ትወልዳለች !
ይሄንን ስላለመኑ ነው የአለም ጠቢባን ሞኞች ሆነው የቀሩት ፤ እኛ ለአለም ሞኞች ሆነን ፤ በእግዚአብሔር ጥበብ ስላመንን (ድንግል መውለዷን ስላመንን) ጠብባን ሆንን !
📌 ኢየሱስ ##ከድንግል መወለዱ ለትምህርታችንም ለሕይወታችንም ትልቅ ጠቀሜታ አለው ( ሶስት ዋና ዋና ነገሮች)
1.#ደህንነት ከቶ ፣ በፍጹም በሰው ጥረት እንደማይመጣ ፤ የእግዚአብሔር ስራ ብቻ እንደሆነ እንረዳለን ! እግዚአብሔር፦ የሴቲቱ “ዘር” (ዘፍ 3፡15) በመጨረሻ የእባቡን ዘር እንደሚያጠፋ ቃል በገባው መሠረት ፣ በሰው ጥረት ሳይሆን በገዛ ኃይሉ እውን አደረገው።
የክርስቶስ ከድንግል መወለድ ፣ #ድነት #የእግዚአብሔር የራሱ ስራና ፣ የእኛ እጅ ያልታከለበት ፣ ከቶ በሰው ጥረት እንዳልሆነ የሚያሳስብ ብርት ትምህት ነው።
🚨ድነታችን በእግዚአብሔር መለኮታዊ ስራ ብቻ የሚፈፀም ነው ። ( ...ነገር ግን የተወሰነው ዘመን በደረሰ ጊዜ፣ እግዚአብሔር #ከ“ሴት” የተወለደውን፣ ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤
5 ይህም የሆነው #የልጅነትን መብት እናገኝ ዘንድ ከሕግ በታች ያሉትን ለመዋጀት ነው።ገላትያ 4:4-5)
2. ኢየሱስ ከድንግል መወለዱ #ፍፁም #አምላክነትና #ፍፁም #ሰውነት በአንድ አካል እንዲዋሐዱ አደረገ። እግዚአብሔር ልጁን ወደ አለም ለመላክ የተጠቀመበት ዘዴ ይህ ነበር ( ዮሐ 3፡16 ገላ 4፡4)
#ኢየሱስ ያለ ምድራዊ ወላጅ(ያለ ማርያም)ከሰማይ ስጋ እንደለበሰ ሙሉ ሰው ሆኖ ቢገለጥ እንደኛ ያለ ፍፁም ሰው መሆኑን #ማረጋገጥ አይቻልም ።
#ኢየሱስ ከእናትና ከስጋ አባት እንደኛ የተወለደ ቢሆን ፍፁም አምላክ መሆኑን ፈጽሞ #ማረጋገጥ አይቻልም ።
3.የክርስቶስ ከድንግል መወለዱም "የውርስ ኃጢአት" ሳይኖርበት እውነተኛ ሰው እንዲሆን ያስችለዋል ።
+ ኢየሱስም ሌሎች ሰዎች ከአዳም እንደተገኙ በተመሳሳይ ከአዳም አልተገኘም ፣ የስጋ አባት የለውም። ይህም የሰው ሁሉ ሕጋዊ በደልና ብልሹ ግብረገብ ክርስቶስ እንዳልወረሰ ያስረዳል ።
+ በተጨማሪ በማርያም ማህፀን ውስጥ መንፈስ ቅዱስ የሰራውን ስራ ማየትም ጠቃሚ ነው (ሉቃ 1፡35)።
ለ.የሰውነት ባህሪያት ( የሰው ድክመትና ውስንነት)...
ይቀጥላል ...
262
እስቲ አንዴ አፍቅራችሁ የሚታውቁና የፍቅር ደብዳቤ የደረሳችው ሰዎች እጃችሁን አንሱ😁 ምን አይነት ስሜት አንዳለው ያው በደምብ ታውቃላችሁ 😁 ...
አሁን ደግሞ ሳታፈቅሩ ያፈቀራችሁን ፣ ሳትወዱት የወደዳችሁን ፤ የኢየሱስ ክርስቶስን እናጥና። አስቡ እስቲ ያፈቀራችሁ ሰው የሰጠውን ደብዳቤ ሳታነቡ ማስቀመጥ ትችላላችሁ ?🤔
የትላንቱ ክፍል ሁለት ዛሬ እንቀጥላለን 🫡
262
፨ #ክፍል 1 “የክርስቶስ ማንነት ”
📌ኢየሱስ፦ የግሪክ ቃል ሲሆን “መድኃኒት ፣ አዳኝ ” ማለት ነው።
በዕብራይስጥ “የሹዋህ” Yeho-shuah ትርጉሙ “ያህዌ” አዳኝ ነው “እግዚአብሔር አዳኝ ነው” ማለት ነው። (ማቴ 1፡21)
👉 በዚህ ስም ነው መዳን የሆነልን
📌ክርስቶስ፦ የተቀባ ፣ የተሾመ ማለት ነው ፣ ይህም የተላከበትን ዓላማና ስራ ሁሉ ለመፈጸም ስልጣን እንዳለው የሚገልጥ ማረጋገጫ የስልጣን ስም ነው ።
ክርስቶስ ከስምነት ይልቅ የኢየሱስን ማዕረግ እና ስልጣንን ይገልጣል ። (ማቴ 16፡16 ሐዋ 2፡36)
📌አማኑኤል፦ ትሥጉትን(አምላክ በስጋ መገለጡን) ወይም incarnation የሚለውን የሚያሳይ እና በሕዝቡ መካከል መኖሩን ስም ነው ። ትርጉሙም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው ( ኢሳ 7፡14 , ማቴ 1፡23)
📌የእግዚአብሔር ልጅ፦ ዘላለማዊ የእግዚአብሔር የባህርይ ልጁ ፣ ማለትም ፍፁም አምላክ መሆኑን የሚገልጥ መጠሪያ ነው። ( ማቴ 16፡16) ዮሐ 20፡31)
📌የሰው ልጅ፦ በስጋ መገሉጡንና ፣ በስጋና በደም ከእኛ ጋር የተካፈለበትን ፍፁም ሰውነቱን የሚገልጥበት መጠሪያ ነው ። ( ማር 10፡45, ማቴ 26፡64)
📌ጌታ፦ በግሪኩ ኩሪዮስ የሚለው ቃል የተተረጎመው ላለና ለነበረው ለአምላክ ስም ያህዌህ ለሚለው ሲሆን በግሪኩ መጽሐፍ ቅዱስ ፈጣሪና ፣ ፍጥረቱን መጋቢ ለሆነ አምላክ ለሆነ አምላክ የሚቀጸል መጠሪያ ነው
📌👑ንጉስ፦ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጥበት ፣ በያዕቆብ ቤት ሁሉ ላይ ፣ በኢየሩሳሌም በታላቁ ንጉስ ከተማ የሚነግስበት ስልጣኑን የሚያሳይ መጠሪያ ነው ( ማቴ 2፡1-11, 27፡37)
📌የዳዊት ልጅ፦ እግዚአብሔር ለዳዊት በዙፋኑ ላይ ለዘላለም የሚቀመጥ ልጅ እንደሚያስነሳለት ተስፋ ሰጥቶታል እናም አይሁድ ሁሉ ተስፋ የሚያደርጉት ንጉሳቸው መሆኑን የሚገልጥ መጠሪያ ነው ( መዝ 89፡28-37 ማቴ 10፡48)
ይቀጥላል ...
262
መግቢያ
“የክርስቶስ ማንነት ”
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን ለብሶ ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ሰዎች በእርሱ ማንነት ላይ የተለያየ ዓይነት ገለጻ ሲሰጡ ይስተዋላሉ፡፡ በማንነቱ ላይ በነበራቸውም አልመግባባት ብዙ የኃይማኖት ተቋማት ሊመሠረቱ ችለዋል፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ግራ መጋባት የተጀመረው ዛሬ ሳይሆን ከጥንት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋሪያቱን ሦስት ዓመት ተኩል ካስተማራቸው በኋላ አንድ ወሳኝ ጥያቄ ይጠይቃችኋል፤እንዲህ በማለት፡- ''ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል?'' አላቸው (ማቴ 16፡13)፡፡ በእርግጥ ሐዋሪያቱ የተጠየቁት ጥያቄ በጣም ከባድ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ምክንያቱም ለሦስት ዓመት ተኩል የተማሩት ትምህርና የወሰዱት ሥልጠና በዚህ ጥያቄ ልቋጭ ነውና፡፡ እነርሱም፡- ''አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት'' (ማቴ 16፡14)። ኢየሱስም መልሶ ''እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው'' (ማቴ 16፡15)። ከመካከላቸውም ጴጥሮስ ኢየሱስን እንዲህ አለው፡- ''አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለው'' (ማቴ 16፡15)። ዳሩ ግን ለጴጥሮስ ይህን መልስ የገለጠው እግዚአብሔር አብ ነበር (ማቴ 16፡17)፡፡ እግዚአብሔር አብ እስካልገለጠ ድረስ ወልድን ሊያውቅ የሚችል ከቶ የለምና (ሉቃ 10፡22)፡፡
📚 Android Application so called ‹‹መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮ›› is developed by Fantahun Beyene.
262
ወገኖች (በክርስቶስ ወንድሞችና እህቶቼ ) ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ ።
ሳምንቱን( በተከታታይ) የክርስቶስ ማንነት በሚል ሀሳብ እያጠነው ስለሆነ ...
ሌላ እቅድ የሌላችሁ ማታ ማታ (3፥00) ከእኔ ጋር ማጥናት ትችላላችሁ (ያጣናውትን በትንሹ አካፍላችዋለሁ)
reference (ማጣቃሻ መፅሐፍት የሚሆኑት )📚
📚(systematic theology.✍️“Wayne grudum”
📚የእግዚአብሔር ልጅ ✍️“ጳውሎስ ፈቃዱ”
📚የመዳን እውቀት ✍️“ተስፋኹን ነጋሽ ”
📚knowing God✍️J.I. packer
📚This Android Application so called ‹‹መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮ›› is developed by Fantahun Beyene.
ከነዚህ መፅሐፍት ይሆናል መፅሐፍቶቹን ካገኛችሁ እንድታነቡት ነው ስማቸውን እና ደራስዎቹን mention ያረኩት!
ግን እንግሊዝኛውን የት አባቱ ብዬ ገና እያሞከርኩ ነው😁
262
🏃♂የእምነት ጉዞ
ብዙዎቻችን #ስለ እግዚአብሔር ማወቅ እና #እግዚአብሔርን በግል ሕይወት ማግኘት አንድ ይመስሉናል። ነገር ግን በሁለቱ መካከል የባሕርይ ልዩነት አለ።
👉ስለ እግዚአብሔር ማወቅ (Knowledge)፦ ይህ ደረጃ አእምሯዊ ነው። መጻሕፍትን ማንበብ፣ ታሪኮችን ማጥናት፣ ዶክትሪኖችን በቃል መያዝ እና በሃይማኖታዊ ክርክሮች ላይ ማሸነፍ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ይህ እውቀት ወደ ልብ ካልወረደ የሃይማኖት "ሳይንስ" ወይም "ፍልስፍና" ብቻ ሆኖ ሊቀር ይችላል።
👉እግዚአብሔርን ማግኘትና መለማመድ (Intimacy)፦ ይህ ደግሞ የልብና የሕይወት እውነተኛ ልምምድ ነው። መለኮታዊውን ፍቅር በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ በተግባር መለማመድ፣ በፈተናዎች መካከል የእርሱን እረኝነት ማየት እና ፈቃዱን በሕይወት መተርጎም ነው።
ስለዚህ፤ የእምነት እውነተኛው ውበትና ማራኪነት የሚገለጠው መረጃዎችን በማከማቸት ብቻ ሳይሆን፣ ያንን እውቀት ወደ ሕያው ግንኙነትና የሕይወት ለውጥ ማሸጋገር ሲቻል ብቻ ነው። ጉዟችን ከመጽሐፍት ገጾችና ከጭንቅላት እውቀት አልፎ ወደ ልባችን ጥልቀት የሚዘልቅ ይሁን!
✍️https://t.me/christcentered7
262
#መንፈስ_ቅዱስ ለብርታታችን የሚሰጥ ሽልማት አይደለም ፤ ደካማው እንድበረታ የሚሰጥ የእግዚአብሔር አብ ስጦታ ነው ።
#መንፈስ_ቅዱስ ፦ ስንበረታ ከእኛ ጋር ሆኖ ፣ ስንደክም ከእኛ የማይርቅ ነው።
✍️ወንድም አሻግሬ
262
“እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና፦ ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”
— ሉቃስ 22፥19
“ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም፦ እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥24
“እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ፦ ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥25
262
📖1ጴጥሮስ 2:9📖
9 እናንተ ግን ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃኑ የጠራችሁን የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ እንድታውጁ
#የተመረጠ_ትውልድ፣
#የንጉሥ_ካህናት፣
#ቅዱስ_ሕዝብ፣
#እግዚአብሔር ለራሱ የለያችሁ ሕዝብ ናችሁ።
ክርስቲያን ርኩስ ስለሆነ አይደለም የሚቀደሰው ፤ ቅዱስ ስለሆነ እንጂ ።
ምክንያቱም ቃሉ እንዲህ ይላል
“ 📖 ራእይ 22:11📖
... #ዐመፀኛው #በዐመፁ #ይቀጥል፤ #ርኩሱም #ይርከስ፤ #ጻድቁም #ይጽደቅ፤ #ቅዱሱም #ይቀደስ።”
ክርስቲያኖችን እርኩሳን ካልክ በኋላ ፤ ተቀደሱ እንዳትል 😁 ምክንያቱም እርኩስ ልቀደስ አይችልምና ነው🤭😁
262
📖1ጴጥሮስ 2:9📖
9 እናንተ ግን ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃኑ የጠራችሁን የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ እንድታውጁ
#የተመረጠ_ትውልድ፣
#የንጉሥ_ካህናት፣
#ቅዱስ_ሕዝብ፣
#እግዚአብሔር ለራሱ የለያችሁ ሕዝብ ናችሁ።
ክርስቲያን ርኩስ ስለሆነ አይደለም የሚቀደሰው ፤ ቅዱስ ስለሆነ እንጂ ።
ምክንያቱም ቃሉ እንዲህ ይላል
“ 📖 ራእይ 22:11📖
... #ዐመፀኛው #በዐመፁ #ይቀጥል፤ #ርኩሱም #ይርከስ፤ #ጻድቁም #ይጽደቅ፤ #ቅዱሱም #ይቀደስ።”
ክርስቲያኖችን እርኩሳን ካልክ በኋላ ፤ ተቀደሱ እንዳትል 😁 ምክንያቱም እርኩስ ልቀደስ አይችልምና ነው🤭😁
262
#የቅድስናችን መለኪያ የገዛ ባሕሪያችን ምን ያህል እንደተሻሻለ መመልከት ሳይሆን፣ በክርስቶስ ፍጹም ሥራ ላይ ያለን እምነትና መደገፍ ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ ማየት ነው።
#እውነተኛ #ቅዱስ ሰዉ ወደ ራሱ ተመልክቶ በጽድቁ የሚደሰት ሳይሆን፣ ወደ #ክርስቶስ ተመልክቶ በጸጋው የሚደገፍና ራሱን ፍጹም #ዐቅመ ቢስ አድርጎ የሚቈጥር ትሑት ነፍስ ነው።
❇️ቢ. ቢ ዋርፊልድ
262
📌ብዙዎች ዝሙትን የሚሸሹት እግዚአብሔርን ከማፍቀርና በርሱ ከመደሰት የተነሣ ሳይሆን፣ “ነገ ትዳሬ እንዳይበላሽ፣ ወሲባዊ ርካታዬን እንዳላጣው” በሚል #ጥቅም ተኮር ፍልስፍና (Utilitarianism) ነው።
ኀጢአትን የሚሸሹት አምላክን ስለሚያሳዝን ሳይሆን፣ የኅሊና ወቀሳንና የጥፋተኝነት ሥቃይን ለመሸሽ ብቻ ነው (Hedonistic avoidance)። ወይም ደግሞ ፍቅረ ሥላሴ እና ትኲስ መለኮታዊ ኅብረት በሌለው፣ ፍርሃትና ደረቅ #ግዴታ በነገሠበት #የሕግጋት እስር ቤት ውስጥ ሆነው ቅድስናን ለመጠበቅ ይውተረተራሉ (Deontological Legalism)። ይኽ ግን #መንፈሳዊ ድንቁርና ነው። ክርስቲያናዊ ቅድስና ፦
#ጥቅመኛም፣
#ስሜት አሳዳጅም
ወይም
#ደረቅ የሕግ ግዴታም አይደለም።
የመቀደሳችንና የወሲባዊ ንጽሕናችን ፍጹም መዳረሻ ግብ በራሱ በክርስቶስ ውበት መደሰት፣ በርሱ መለኮታዊ ክብር መርካትና ማረፍ ብቻ ነው!“እኛ ወሲባዊ ቅድስናን የምንጠብቀው በምላሹ ምድራዊ ጥቅምን ለመሸመት በሚደረግ የንግድ ስሌት አይደለም፤ ይልቁኑ ከሁሉ በላይ በሆነው በክርስቶስ ማንነት አስቀድመን በመርካታችን ምክንያት በሕይወታችን ከሚፈስስ የፍቅር ትርፍ ነው እንጂ።
📚የኅሩያን ሕይወት (ምዕራፍ ስድስት)
#ኢየሱስን ወደን እንቀደ
#ሙሴን ሳይሆን ኢየሱስን እያየን እንቀደስ! #ኦሪትን ሳይሆን የተሰቀለውን እያየን እንቀደስ!
ይህ ካልሆነ ግን ፤ የሀገሬ ሰው እንደሚል “አድሮ ቃሪያ ፤ ከርሞ ጥጃ ” እዚያው በዚያ ሳንለወጥ መንፈሳዊ #ህፃናት ሆነን እናረጃለን !
✍️ወንድም አሻግሬ
262
ለመዳን የሙሴ ህግ እንዳልጠቀመን ሁላ ፤ ለመቀደስም ከሙሴ ህግ አንዋስም ፣ ያዳነን ያ ፀጋ ደግሞ ቀዳሻችን ነው !
በፀጋ ድነናል ፤ በፀጋ እንቀደሳለን !
📖ገላትያ 3:2-4📖(ህያው ቃል ትርጉም )
እስቲ አንድ ነገር ልጠይቃችሁ። ለመሆኑ መንፈስ ቅዱስን የተቀበላችሁት የኦሪትን ሕግ ለመፈጸም ባደረጋችሁት #ጥረት ነው ? ወይስ የተሰበከላችሁን የወንጌል ቃል #በእምነት በመቀበላችሁ ነው ?
በመጀመሪያውኑ የኦሪትን ሕግ በመፈፀም መንፈሳዊ ህይወት ልታገኙ #አለመቻላችሁን አውቃችሁ በእምነት ከጀመራችሁ በኋላ ፥ ተመልሳችሁ ይህንኑ ሕግ በመጠበቅ “መንፈሳዊ ሕይወታችን ፍጹም ይሆናል” ብላችሁ እንዴት ታስባላችሁ ? ሞኞች ናችሁ ልበል ?
እሲት ሕግ ሕግ የሚትሉ ሰዎች ☝️ከላይ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ላቀረበው ጥያቄ መልስ ስጡ ፤ ለእኔ ሳይሆን ለጳውሎስ 🤭
እግዚአብሔር አብ ፦ ሙሴም ፣ ኤልያስም ባሉበት እነሱን ሳይሆን ፣👂ስሙ ያለን ልጁን ኢየሱስን ነው (ማቴ 17፥5)
በክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሆናችሁ #ሙሴ #ሙሴ የሚሸታችሁ ሰዎች ፤ አደብ ጊዙ !
ኢየሱስ አድኖናል ፤ መንፈስ ቅዱስ ቀደሻችን ነው! ኢየሱስ አዳኛችንም ጌታችንም ነው !
ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ
#አድኖናል
#ይቀድስናል
( ቲቶ 2፥11-12 )
262
Repost from አዲስ ነገር መረጃ
+1
ተጠንቀቁ
ስልኩ ላይ ለረጅም ሰዓታት አቀርቅሮ በማሳለፉ ፓራላይዝ የሆነው የ19 ዓመት ወጣት
ቻይናዊው የ19 ዓመቱ ሻዮ ዶንግ ለረጅም ሰዓታት ስልኩ ላይ አቀርቅሮ በማሳለፉ የተነሳ በከፊል ፓራላይዝ ሆኗል።
ስልኩ ላይ ማኀበራዊ ሚዲያዎችን በመከታተል ሙሉ ጊዜውን በሚባል ደረጃ ላይ የሚያሳልፈው ወጣቱ ከጊዜ በኋላ በአንገቱ፣ በእጆቹ እና በእግሮቹ ላይ የመደንዘዝ ስሜት ይሰማው ጀመር።
ነገሮችም እየተባባሱ ሄደው አንድ ቀን ጠዋት ከእንቅልፉ ሲነቃ እግሩ መንቀሳቀስ አቅቶት እንደነበር ኦዲቲ ሴንትራል ዘግቧል።
ዶክተሮችም በፍጥነት ወደ ቀዶ ጥገና ወስደውት በአከርካሪው ላይ ከፍተኛ የደም መርጋት መኖሩ አረጋገጡ።
ወጣቱ ያለማቋረጥ ስልኩ ላይ አቀርቅሮ ማሳለፉ በአከርካሪው ውስጥ ያለውን የደም ቧንቧ ተሰብሯል። ይህም ደም በውስጡ እንዲረጋ እና በከፊል ሽባ እንዲሆን አድርጓል ብለዋል ዶክተሮቹ።
እንደ ዕድል ሆኖ ግን፣ ሻዮ ዶንግ አሁን ላይ ቀስ በቀስ እንቅስቃሴን እያደረገ ሲሆን፤ ዶክተሮች ሙሉ በሙሉ እንደሚድን ያምናሉ።
አንገትን ለረጅም ጊዜ አቀርቅሮ ስልክ ላይ ማሳለፍ የደም ዝውውርን በመዝጋት ራስ ምታትን፣ ማዞርን፣ ድካምን እና መደንዘዝን እንደሚያስከትል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ።
ሁኔታዎች እየከፉ ሲሄዱ ደግሞ ወደ ስትሮክ ወይም ፓራላይዝ እስከመሆን ሊዳርግም ይችላል ይላሉ
@Addis_News
@Addis_News
262
በእጆቹ መዳፍ ላይ አንዴ ቀረፀኝ
እስከሞት የወደደኝ አፍቃሪ አለኝ
ወረት የማያውቀው የልቤ ነው እርሱ
ወድሀለሁ/ሻለሁ ያለኝ ምሎ ነው በራሱ /2*
ይወደኛል ብዬ የለም ወይ
አፍቅሮኛል ብዬ የለም ወይ
አይተወኝ ብዬ የለም ወይ
ዛሬ ደርሶ የከፋ ይመስል
አይኔ ደፍሮ እንዴት ሌላ ሊያይ
😭😭😭😭😭😭😭
....
ራሴን እንኳን ከወደድኩት ከተቀበልኩት በላይ
ወዶኝ ተቀብሎኝ ሳያው አልኩኝ ይወደኝ የለ ወይ
🙆♀️🙆♀️🙆♀️🙆♀️🙆♀️🙆♀️🙆♀️🙆♀️
የወደደቻውን እስከመጨረሻው እንደምወድ
ከኢየሱሴ የሚለየኝ እንደሌለ በእኔ ዘንድ
አውቆ የለም ወይ ይሄ ልቤ ከቶ ሀሳቤን አልቀይረው
ይወደኛል ብዬ ነበር ዛሬም እርሱን ደግመዋለው
