fa
Feedback
LOGOS

LOGOS

رفتن به کانال در Telegram

🎯የቻናሉ ዓላማ:LOGOS የሚለው ቃል ከGreek የመጣ ሲሆን፦ትርጉሙም ቃል፣ ምክንያት፣ክርስቶስ (የእግዚአብሔር ቃል ዮሐ 1፥1) በዚህ ቃል እውቀታችንን አሳድገን በኑሮ እንድንተገብር ነው

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
252
مشترکین
+224 ساعت
+47 روز
+1730 روز
آرشیو پست ها
፨ #ክፍል 1 “የክርስቶስ ማንነት ” 📌ኢየሱስ፦ የግሪክ ቃል ሲሆን “መድኃኒት ፣ አዳኝ ” ማለት ነው። በዕብራይስጥ “የሹዋህ” Yeho-shuah ትርጉሙ “ያህዌ” አዳኝ ነው “እግዚአብሔር አዳኝ ነው” ማለት ነው። (ማቴ 1፡21) 👉 በዚህ ስም ነው መዳን የሆነልን 📌ክርስቶስ፦ የተቀባ ፣ የተሾመ ማለት ነው ፣ ይህም የተላከበትን ዓላማና ስራ ሁሉ ለመፈጸም ስልጣን እንዳለው የሚገልጥ ማረጋገጫ የስልጣን ስም ነው ። ክርስቶስ ከስምነት ይልቅ የኢየሱስን ማዕረግ እና ስልጣንን ይገልጣል ። (ማቴ 16፡16 ሐዋ 2፡36) 📌አማኑኤል፦ ትሥጉትን(አምላክ በስጋ መገለጡን) ወይም incarnation የሚለውን የሚያሳይ እና በሕዝቡ መካከል መኖሩን ስም ነው ። ትርጉሙም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው ( ኢሳ 7፡14 , ማቴ 1፡23) 📌የእግዚአብሔር ልጅ ዘላለማዊ የእግዚአብሔር የባህርይ ልጁ ፣ ማለትም ፍፁም አምላክ መሆኑን የሚገልጥ መጠሪያ ነው። ( ማቴ 16፡16) ዮሐ 20፡31) 📌የሰው ልጅ በስጋ መገሉጡንና ፣ በስጋና በደም ከእኛ ጋር የተካፈለበትን ፍፁም ሰውነቱን የሚገልጥበት መጠሪያ ነው ። ( ማር 10፡45, ማቴ 26፡64) 📌ጌታ፦ በግሪኩ ኩሪዮስ የሚለው ቃል የተተረጎመው ላለና ለነበረው ለአምላክ ስም ያህዌህ ለሚለው ሲሆን በግሪኩ መጽሐፍ ቅዱስ ፈጣሪና ፣ ፍጥረቱን መጋቢ ለሆነ አምላክ ለሆነ አምላክ የሚቀጸል መጠሪያ ነው 📌👑ንጉስ፦ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጥበት ፣ በያዕቆብ ቤት ሁሉ ላይ ፣ በኢየሩሳሌም በታላቁ ንጉስ ከተማ የሚነግስበት ስልጣኑን የሚያሳይ መጠሪያ ነው ( ማቴ 2፡1-11, 27፡37) 📌የዳዊት ልጅ እግዚአብሔር ለዳዊት በዙፋኑ ላይ ለዘላለም የሚቀመጥ ልጅ እንደሚያስነሳለት ተስፋ ሰጥቶታል እናም አይሁድ ሁሉ ተስፋ የሚያደርጉት ንጉሳቸው መሆኑን የሚገልጥ መጠሪያ ነው ( መዝ 89፡28-37 ማቴ 10፡48) ይቀጥላል ...

መግቢያ “የክርስቶስ ማንነት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን ለብሶ ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ሰዎች በእርሱ ማንነት ላይ የተለያየ ዓይነት ገለጻ ሲሰጡ ይስተዋላሉ፡፡ በማንነቱ ላይ በነበራቸውም አልመግባባት ብዙ የኃይማኖት ተቋማት ሊመሠረቱ ችለዋል፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ግራ መጋባት የተጀመረው ዛሬ ሳይሆን ከጥንት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋሪያቱን ሦስት ዓመት ተኩል ካስተማራቸው በኋላ አንድ ወሳኝ ጥያቄ ይጠይቃችኋል፤እንዲህ በማለት፡- ''ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል?'' አላቸው (ማቴ 16፡13)፡፡ በእርግጥ ሐዋሪያቱ የተጠየቁት ጥያቄ በጣም ከባድ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ምክንያቱም ለሦስት ዓመት ተኩል የተማሩት ትምህርና የወሰዱት ሥልጠና በዚህ ጥያቄ ልቋጭ ነውና፡፡ እነርሱም፡- ''አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት'' (ማቴ 16፡14)። ኢየሱስም መልሶ ''እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው'' (ማቴ 16፡15)። ከመካከላቸውም ጴጥሮስ ኢየሱስን እንዲህ አለው፡- ''አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለው'' (ማቴ 16፡15)። ዳሩ ግን ለጴጥሮስ ይህን መልስ የገለጠው እግዚአብሔር አብ ነበር (ማቴ 16፡17)፡፡ እግዚአብሔር አብ እስካልገለጠ ድረስ ወልድን ሊያውቅ የሚችል ከቶ የለምና (ሉቃ 10፡22)፡፡ 📚 Android Application so called ‹‹መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮ›› is developed by Fantahun Beyene.

ወገኖች (በክርስቶስ ወንድሞችና እህቶቼ ) ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ ። ሳምንቱን( በተከታታይ) የክርስቶስ ማንነት በሚል ሀሳብ እያጠነው ስለሆነ ... ሌላ እቅድ የሌላችሁ ማታ ማታ (3፥00) ከእኔ ጋር ማጥናት ትችላላችሁ (ያጣናውትን በትንሹ አካፍላችዋለሁ) reference (ማጣቃሻ መፅሐፍት የሚሆኑት )📚 📚(systematic theology.✍️“Wayne grudum” 📚የእግዚአብሔር ልጅ ✍️“ጳውሎስ ፈቃዱ” 📚የመዳን እውቀት ✍️“ተስፋኹን ነጋሽ ” 📚knowing God✍️J.I. packer 📚This Android Application so called ‹‹መሠረታዊ የክርስትና አስተምህሮ›› is developed by Fantahun Beyene. ከነዚህ መፅሐፍት ይሆናል መፅሐፍቶቹን ካገኛችሁ እንድታነቡት ነው ስማቸውን እና ደራስዎቹን mention ያረኩት! ግን እንግሊዝኛውን የት አባቱ ብዬ ገና እያሞከርኩ ነው😁

🏃‍♂የእምነት ጉዞ ​ብዙዎቻችን #ስለ እግዚአብሔር ማወቅ እና #እግዚአብሔርን በግል ሕይወት ማግኘት አንድ ይመስሉናል። ነገር ግን በሁለቱ መካከል የባሕርይ ልዩነት አለ። 👉​ስለ እግዚአብሔር ማወቅ (Knowledge)፦ ይህ ደረጃ አእምሯዊ ነው። መጻሕፍትን ማንበብ፣ ታሪኮችን ማጥናት፣ ዶክትሪኖችን በቃል መያዝ እና በሃይማኖታዊ ክርክሮች ላይ ማሸነፍ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ይህ እውቀት ወደ ልብ ካልወረደ የሃይማኖት "ሳይንስ" ወይም "ፍልስፍና" ብቻ ሆኖ ሊቀር ይችላል። 👉​እግዚአብሔርን ማግኘትና መለማመድ (Intimacy)፦ ይህ ደግሞ የልብና የሕይወት እውነተኛ ልምምድ ነው። መለኮታዊውን ፍቅር በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ በተግባር መለማመድ፣ በፈተናዎች መካከል የእርሱን እረኝነት ማየት እና ፈቃዱን በሕይወት መተርጎም ነው። ስለዚህ፤ ​የእምነት እውነተኛው ውበትና ማራኪነት የሚገለጠው መረጃዎችን በማከማቸት ብቻ ሳይሆን፣ ያንን እውቀት ወደ ሕያው ግንኙነትና የሕይወት ለውጥ ማሸጋገር ሲቻል ብቻ ነው። ጉዟችን ከመጽሐፍት ገጾችና ከጭንቅላት እውቀት አልፎ ወደ ልባችን ጥልቀት የሚዘልቅ ይሁን! ✍️https://t.me/christcentered7

ነፍስን የሚያሰፋው ምርጥ ትምህርት የተሰቀለውን #ኢየሱስን ማጥናት ነው። •••••••••••• ✍️ቻርልስ ስፐርጅን ••••••••••••

#ቅድስና የዘመን ክፋት ቀልሎልን ሳይሆን ፤ የእግዚአብሔር ፀጋ በዝቶልን የምንኖረው ሕይወት ነው ። 📚 መንፈሳዊ ብስለት ✍️ማሙሻ ፈንታ (ዶ/ር)

#መንፈስ_ቅዱስ ለብርታታችን የሚሰጥ ሽልማት አይደለም ፤ ደካማው እንድበረታ የሚሰጥ የእግዚአብሔር አብ ስጦታ ነው ። #መንፈስ_ቅዱስ ፦ ስንበረታ ከእኛ ጋር ሆኖ ፣ ስንደክም ከእኛ የማይርቅ ነው። ✍️ወንድም አሻግሬ

“እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና፦ ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።” — ሉቃስ 22፥19 “ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን
“እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና፦ ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”   — ሉቃስ 22፥19 “ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም፦ እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”   — 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥24 “እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ፦ ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”   — 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥25

📖1ጴጥሮስ 2:9📖 9 እናንተ ግን ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃኑ የጠራችሁን የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ እንድታውጁ #የተመረጠ_ትውልድ፣ #የንጉሥ_ካህናት፣ #ቅዱስ_ሕዝብ #እግዚአብሔር ለራሱ የለያችሁ ሕዝብ ናችሁ። ክርስቲያን ርኩስ ስለሆነ አይደለም የሚቀደሰው ፤ ቅዱስ ስለሆነ እንጂ ። ምክንያቱም ቃሉ እንዲህ ይላል      “ 📖 ራእይ 22:11📖 ... #ዐመፀኛው #በዐመፁ #ይቀጥል፤ #ርኩሱም #ይርከስ፤ #ጻድቁም #ይጽደቅ፤ #ቅዱሱም #ይቀደስ።” ክርስቲያኖችን እርኩሳን ካልክ በኋላ ፤ ተቀደሱ እንዳትል 😁 ምክንያቱም እርኩስ ልቀደስ አይችልምና ነው🤭😁

📖1ጴጥሮስ 2:9📖 9 እናንተ ግን ከጨለማ ወደ አስደናቂ ብርሃኑ የጠራችሁን የእግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ እንድታውጁ #የተመረጠ_ትውልድ፣ #የንጉሥ_ካህናት፣ #ቅዱስ_ሕዝብ #እግዚአብሔር ለራሱ የለያችሁ ሕዝብ ናችሁ። ክርስቲያን ርኩስ ስለሆነ አይደለም የሚቀደሰው ፤ ቅዱስ ስለሆነ እንጂ ። ምክንያቱም ቃሉ እንዲህ ይላል “ 📖 ራእይ 22:11📖 ... #ዐመፀኛው #በዐመፁ #ይቀጥል፤ #ርኩሱም #ይርከስ፤ #ጻድቁም #ይጽደቅ፤ #ቅዱሱም #ይቀደስ።” ክርስቲያኖችን እርኩሳን ካልክ በኋላ ፤ ተቀደሱ እንዳትል 😁 ምክንያቱም እርኩስ ልቀደስ አይችልምና ነው🤭😁

#የቅድስናችን መለኪያ የገዛ ባሕሪያችን ምን ያህል እንደተሻሻለ መመልከት ሳይሆን፣ በክርስቶስ ፍጹም ሥራ ላይ ያለን እምነትና መደገፍ ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ ማየት ነው። #እውነተኛ #ቅዱስ ሰዉ ወደ ራሱ ተመልክቶ በጽድቁ የሚደሰት ሳይሆን፣ ወደ #ክርስቶስ ተመልክቶ በጸጋው የሚደገፍና ራሱን ፍጹም #ዐቅመ ቢስ አድርጎ የሚቈጥር ትሑት ነፍስ ነው።  ❇️ቢ. ቢ ዋርፊልድ

📌ብዙዎች ዝሙትን የሚሸሹት እግዚአብሔርን ከማፍቀርና በርሱ ከመደሰት የተነሣ ሳይሆን፣ “ነገ ትዳሬ እንዳይበላሽ፣ ወሲባዊ ርካታዬን እንዳላጣው” በሚል #ጥቅም ተኮር ፍልስፍና (Utilitarianism) ነው። ኀጢአትን የሚሸሹት አምላክን ስለሚያሳዝን ሳይሆን፣ የኅሊና ወቀሳንና የጥፋተኝነት ሥቃይን ለመሸሽ ብቻ ነው (Hedonistic avoidance)። ወይም ደግሞ ፍቅረ ሥላሴ እና ትኲስ መለኮታዊ ኅብረት በሌለው፣ ፍርሃትና ደረቅ #ግዴታ በነገሠበት #የሕግጋት እስር ቤት ውስጥ ሆነው ቅድስናን ለመጠበቅ ይውተረተራሉ (Deontological Legalism)። ይኽ ግን #መንፈሳዊ ድንቁርና ነው። ክርስቲያናዊ ቅድስና ፦ #ጥቅመኛም፣ #ስሜት አሳዳጅም ወይም #ደረቅ የሕግ ግዴታም አይደለም። የመቀደሳችንና የወሲባዊ ንጽሕናችን ፍጹም መዳረሻ ግብ በራሱ በክርስቶስ ውበት መደሰት፣ በርሱ መለኮታዊ ክብር መርካትና ማረፍ ብቻ ነው!“እኛ ወሲባዊ ቅድስናን የምንጠብቀው በምላሹ ምድራዊ ጥቅምን ለመሸመት በሚደረግ የንግድ ስሌት አይደለም፤ ይልቁኑ ከሁሉ በላይ በሆነው በክርስቶስ ማንነት አስቀድመን በመርካታችን ምክንያት በሕይወታችን ከሚፈስስ የፍቅር ትርፍ ነው እንጂ። 📚የኅሩያን ሕይወት (ምዕራፍ ስድስት) #ኢየሱስን ወደን እንቀደ #ሙሴን ሳይሆን ኢየሱስን እያየን እንቀደስ! #ኦሪትን ሳይሆን የተሰቀለውን እያየን እንቀደስ! ይህ ካልሆነ ግን ፤ የሀገሬ ሰው እንደሚል “አድሮ ቃሪያ ፤ ከርሞ ጥጃ ” እዚያው በዚያ ሳንለወጥ መንፈሳዊ #ህፃናት ሆነን እናረጃለን ! ✍️ወንድም አሻግሬ

ለመዳን የሙሴ ህግ እንዳልጠቀመን ሁላ ፤ ለመቀደስም ከሙሴ ህግ አንዋስም ፣ ያዳነን ያ ፀጋ ደግሞ ቀዳሻችን ነው ! በፀጋ ድነናል ፤ በፀጋ እንቀደሳለን ! 📖ገላትያ 3:2-4📖(ህያው ቃል ትርጉም ) እስቲ አንድ ነገር ልጠይቃችሁ። ለመሆኑ መንፈስ ቅዱስን የተቀበላችሁት የኦሪትን ሕግ ለመፈጸም ባደረጋችሁት #ጥረት ነው ? ወይስ የተሰበከላችሁን የወንጌል ቃል #በእምነት በመቀበላችሁ ነው ? በመጀመሪያውኑ የኦሪትን ሕግ በመፈፀም መንፈሳዊ ህይወት ልታገኙ #አለመቻላችሁን አውቃችሁ በእምነት ከጀመራችሁ በኋላ ፥ ተመልሳችሁ ይህንኑ ሕግ በመጠበቅ “መንፈሳዊ ሕይወታችን ፍጹም ይሆናል” ብላችሁ እንዴት ታስባላችሁ ? ሞኞች ናችሁ ልበል ? እሲት ሕግ ሕግ የሚትሉ ሰዎች ☝️ከላይ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ላቀረበው ጥያቄ መልስ ስጡ ፤ ለእኔ ሳይሆን ለጳውሎስ 🤭 እግዚአብሔር አብ ፦ ሙሴም ፣ ኤልያስም ባሉበት እነሱን ሳይሆን ፣👂ስሙ ያለን ልጁን ኢየሱስን ነው (ማቴ 17፥5) በክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሆናችሁ #ሙሴ #ሙሴ የሚሸታችሁ ሰዎች ፤ አደብ ጊዙ ! ኢየሱስ አድኖናል ፤ መንፈስ ቅዱስ ቀደሻችን ነው! ኢየሱስ አዳኛችንም ጌታችንም ነው ! ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ ፀጋ #አድኖናል #ይቀድስናል ( ቲቶ 2፥11-12 )

ተጠንቀቁ ስልኩ ላይ ለረጅም ሰዓታት አቀርቅሮ በማሳለፉ ፓራላይዝ የሆነው የ19 ዓመት ወጣት ቻይናዊው የ19 ዓመቱ ሻዮ ዶንግ ለረጅም ሰዓታት ስልኩ ላይ አቀርቅሮ በማሳለፉ የተነሳ በከፊል ፓራላይዝ ሆ
+1
ተጠንቀቁ ስልኩ ላይ ለረጅም ሰዓታት አቀርቅሮ በማሳለፉ ፓራላይዝ የሆነው የ19 ዓመት ወጣት ቻይናዊው የ19 ዓመቱ ሻዮ ዶንግ ለረጅም ሰዓታት ስልኩ ላይ አቀርቅሮ በማሳለፉ የተነሳ በከፊል ፓራላይዝ ሆኗል። ስልኩ ላይ ማኀበራዊ ሚዲያዎችን በመከታተል ሙሉ ጊዜውን በሚባል ደረጃ ላይ የሚያሳልፈው ወጣቱ  ከጊዜ በኋላ በአንገቱ፣ በእጆቹ እና በእግሮቹ ላይ የመደንዘዝ ስሜት ይሰማው ጀመር። ነገሮችም እየተባባሱ ሄደው አንድ ቀን ጠዋት ከእንቅልፉ ሲነቃ እግሩ መንቀሳቀስ አቅቶት እንደነበር ኦዲቲ ሴንትራል ዘግቧል። ዶክተሮችም በፍጥነት ወደ ቀዶ ጥገና ወስደውት በአከርካሪው ላይ ከፍተኛ የደም መርጋት መኖሩ አረጋገጡ። ወጣቱ ያለማቋረጥ ስልኩ ላይ አቀርቅሮ ማሳለፉ በአከርካሪው ውስጥ ያለውን የደም ቧንቧ ተሰብሯል። ይህም ደም በውስጡ እንዲረጋ እና በከፊል ሽባ እንዲሆን አድርጓል ብለዋል ዶክተሮቹ። እንደ ዕድል ሆኖ ግን፣ ሻዮ ዶንግ አሁን ላይ ቀስ በቀስ እንቅስቃሴን እያደረገ ሲሆን፤ ዶክተሮች ሙሉ በሙሉ እንደሚድን ያምናሉ። አንገትን ለረጅም ጊዜ አቀርቅሮ ስልክ ላይ ማሳለፍ የደም ዝውውርን በመዝጋት ራስ ምታትን፣ ማዞርን፣ ድካምን እና መደንዘዝን እንደሚያስከትል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ። ሁኔታዎች እየከፉ ሲሄዱ ደግሞ ወደ ስትሮክ ወይም ፓራላይዝ እስከመሆን ሊዳርግም ይችላል ይላሉ @Addis_News @Addis_News

በእጆቹ መዳፍ ላይ አንዴ ቀረፀኝ እስከሞት የወደደኝ አፍቃሪ አለኝ ወረት የማያውቀው የልቤ ነው እርሱ ወድሀለሁ/ሻለሁ ያለኝ ምሎ ነው በራሱ /2* ይወደኛል ብዬ የለም ወይ አፍቅሮኛል ብዬ የለም ወይ አይተወኝ ብዬ የለም ወይ ዛሬ ደርሶ የከፋ ይመስል አይኔ ደፍሮ እንዴት ሌላ ሊያይ 😭😭😭😭😭😭😭 .... ራሴን እንኳን ከወደድኩት ከተቀበልኩት በላይ ወዶኝ ተቀብሎኝ ሳያው አልኩኝ ይወደኝ የለ ወይ 🙆‍♀️🙆‍♀️🙆‍♀️🙆‍♀️🙆‍♀️🙆‍♀️🙆‍♀️🙆‍♀️ የወደደቻውን እስከመጨረሻው እንደምወድ ከኢየሱሴ የሚለየኝ እንደሌለ በእኔ ዘንድ አውቆ የለም ወይ ይሄ ልቤ ከቶ ሀሳቤን አልቀይረው ይወደኛል ብዬ ነበር ዛሬም እርሱን ደግመዋለው

📌 የማወራቹ ስለ ##ኃይል ነው! መሬት ላይ ጥሎ እንደ ትል የሚያንፈራፍር አይደለም፣ ቪ ኤይት የሚያሳውጅ አይደለም፣ ያልተፈወሰውን ተፈወሰ የሚያስብል አይደለም። 🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋 የማወራው የክርስትናን ሕይወት እንድትኖሩ ስለሚያደርግ #ኃይል፣ በእውነተኛ ፍቅር ስለሚያራምድ ኃይል፣ ስለ ጸሎት #ኃይል፣ የወንጌል-መስካሪ ስለሚያደርግ #ኃይል ነው። ይህ ኃይል ነው የሚያስፈልገን። •••••••••• ፖል ዎሸር ••••••••••

ድነት የሚገኘው በሰው ጥረት ወይም በመልካም ሥራ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ ነው። የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱም በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ተገልጧል። እርሱ ኃጢአትህን ይቅር ብሎ፣ በመ
ድነት የሚገኘው በሰው ጥረት ወይም በመልካም ሥራ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ ነው። የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱም በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ተገልጧል። እርሱ ኃጢአትህን ይቅር ብሎ፣ በመንፈስ ቅዱስ አዲስ ሕይወት ሰጥቶሃል። ስለዚህ ያለፈው ውድቀትህ የወደፊት ተስፋህን አይወስንም፤ የእግዚአብሔር ጸጋ ከውድቀትህ ይበልጣል፣ ፍቅሩም ከኃጢአትህ ይበልጣል። ስለዚህ ዛሬ ክርስቶስ በሰራልህ ስራ ብቻ እመን። ያዳነህ ጌታ ዛሬም ህይወትህን ሙሉ ያድሰዋል።
ቲቶ 3:4-5 ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤
✍️ #tesfa

##እኔ ሁለንተናዬን ለአንተ ሰጥቼሃለሁ እያልኩ ነው ፤ ግን ምንአልባት እኔ ሳላውቅ ለአንተ እየሰጠው የቀረ ማንነት ካለም ውሰዳው ፤ ##ሙሉዬን ውሰደው የእኔ የምለው ማንነት አይኑረኝ ሁሉ የአንተ ሆኖ የአንተ የሆነው ሁሉ ደግሞ በአንተ ተዋጅቶ ተመልሶ የኔ ይሁን ! ⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐ ✍️ወንድም አሻግሬ 📆 15/10/2018 ሰኞ

አውቃለሁ አንዳንዶቻችሁ ኢየሱስን መውደድ በምትፈልጉት ልክ ባለመውደዳችሁ ታዝናላቹ። ለእርሱ ያላችሁን የእናንተን ፍቅር እርሱትና፥ እርሱ ለእናንተ ያለውን ትልቅ ፍቅር አስቡ፤ ያኔ ለእርሱ ያላችሁ ፍቅር ካሰባችሁት በላይ ከፍ ይላል። ••••••••••••••• ቻርልስ ስፐርጀን •••••••••••••••

🏆ድል ኢየሱስ በእኔ ውስጥ ስኖር ስለ እኔም ሲያሸንፍ ነው ! #እኔ እንድድን በመስቀል ላይ እንደሞተ ሁሉ ፤ ዛሬም #እኔ እንዳሸንፍ በእኔ ውስጥ ይኖራል ። 📚 ድል ነሺ ህይወት ✍️ዎችማን ኒ ገፅ 84 አሸነፍ ሆንኩኝ በአንተ ተመስገን ድሌ ነህ አከብርሃለሁ አንተ ግንዴ እኔም ቅርንጫፍህ ነኝ በአንተ ብዙ ፍሬ ማፍራት ሆነልኝ ተመስገን በክርስቶስ በፀጋ ብቻ ድነት ያገኛችሁ ሰዎች ፤ ባዳነችሁ በክርስቶስ የድል ህይወት መኖር ትችላላችሁ #እንድህ በሉ “ ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ፤ ከእንግዲህ እኔ አልኖርም፤ ነገር ግን ክርስቶስ በውስጤ ይኖራል። ” 📖፨ገላትያ 2፥19-20📖 ✍️ወንድም አሻግሬ