ch
Feedback
Jura Legal Update

Jura Legal Update

前往频道在 Telegram

Official Telegram Channel of Jura Legal Update. For comments, feedback, or inquiries, reach us at juralegalupdate@gmail.com. Or DM us directly in this telegram channel.

显示更多
3 789
订阅者
+15724 小时
+2547 天
+1 61630 天

数据加载中...

相似频道
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+288
在1个频道中
八月 '26
+1 503
在2个频道中
Get PRO
七月 '26
+563
在2个频道中
Get PRO
六月 '26
+210
在1个频道中
Get PRO
五月 '26
+530
在3个频道中
Get PRO
四月 '26
+247
在2个频道中
Get PRO
三月 '26
+650
在2个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
05 九月+54
04 九月+157
03 九月+42
02 九月+27
01 九月+8
频道帖子
የዲፕሎማቲክ አገልግሎት የሥራ ተዋረድ (Diplomatic Service Career Ladder) በኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 790/2005 መሠረት፣ የዲፕሎማቲክ አገልግሎት የሥራ
የዲፕሎማቲክ አገልግሎት የሥራ ተዋረድ (Diplomatic Service Career Ladder) በኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 790/2005 መሠረት፣ የዲፕሎማቲክ አገልግሎት የሥራ ደረጃዎች (career ladder/ranks) እንዲህ ተደንግገዋል። N.B.፦ እነዚህን የሥራ ደረጃዎች ከዲፕሎማቲክ ሹመት (diplomatic appointment) ጋር መደባለቅ አይገባም። አምባሳደር (Ambassador) የተለየ የዲፕሎማቲክ የፖለቲካ ሹመትና የሚሲዮን ኃላፊነት (ambassadorial appointment/mission responsibility) እንጂ በእነዚህ career-rank ደረጃዎች ውስጥ የሚመደብ የሥራ ደረጃ አይደለም። Jura Legal Update

2
አዋጅ-ቁጥር-1353-2017-1 (4).pdf
820
3
የወሊድ ፈቃድ በፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ የወሊድ ፈቃድ ሴት ሠራተኛ በእርግዝናና በወሊድ ወቅት ከሥራ ለጊዜው በመለየት ጤናዋን እንድትጠብቅ፣ ከወሊድ በኋላም ለማገገምና ለሕፃኗ እንክብካቤ በቂ ጊዜ እንድታገኝ የሚያስችል ሕጋዊ መብት ነው። ስለሆነም የወሊድ ፈቃድ እንደ ተራ የዕረፍት ፈቃድ የሚታይ ሳይሆን የእናትን ጤና፣ የሕፃኑን ደህንነት እና የሴቷን ከሥራ ጋር ያላትን መብት በአንድ ላይ ማስጠበቅ ዓላማ ያደረገ ነው። የኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 35(5)(ሀ) ሴቶች ከሙሉ የደመወዝ ክፍያ ጋር የወሊድ ፈቃድ የማግኘት መብት እንዳላቸው ይደነግጋል፤ የፈቃዱ ርዝመትም የሥራውን ሁኔታ፣ የሴቷን ጤና እና የሕፃኑንና የቤተሰቡን ደህንነት ታሳቢ በማድረግ በሕግ እንዲወሰን ያዛል። አንቀጽ 35(5)(ለ) ደግሞ የወሊድ ፈቃድ ከሙሉ ክፍያ ጋር የቅድመ ወሊድ ፈቃድን ሊያካትት እንደሚችል ይደነግጋል። ይህንን ሕገ-መንግሥታዊ መርህ በፌዴራል የመንግሥት ሠራተኞች ዘርፍ ተግባራዊ የሚያደርገው የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 አንቀጽ 65 ነው። አዋጁ እርጉዝ የሆነች የመንግሥት ሠራተኛ ከእርግዝና ጋር በተያያዘ የሕክምና ምርመራና በሐኪም ምክር የሚሰጥ የቅድመ ወሊድ ዕረፍት ከክፍያ ጋር እንድታገኝ ይደነግጋል፤ እነዚህም ፈቃዶች እንደ ሕመም ፈቃድ እንደማይቆጠሩ በግልጽ ያስቀምጣል። በአዋጁ እርጉዝ የሆነች የመንግሥት ሠራተኛ ከምትወልድበት ተገምቶ ከተወሰነው ቀን በፊት 30 ተከታታይ ቀናት እና ከወሊድ በኋላ 90 ተከታታይ ቀናት፣ በአጠቃላይ 120 ቀናት ከደመወዝ ጋር የወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል። የቅድመ ወሊድ ፈቃዱ ሳያልቅ ከወለደች ያልተጠቀመችበት ቀሪ ጊዜ ወደ ድህረ-ወሊድ ፈቃድ ይተላለፋል። በተግባር ጠቃሚ የሆነው ሌላው ጉዳይ የተገመተው የወሊድ ቀን ሳይደርስ ወይም ካለፈ የሚፈጠረው ሁኔታ ነው። ሠራተኛዋ ከተገመተው ቀን በኋላ ካልወለደች፣ እስከምትወልድበት ድረስ የሚቆየው ጊዜ በአዋጁ አግባብ ከዓመት ፈቃዷ የሚተካ ነው። ይህ ድንጋጌ የ120 ቀናት መብት በቀጥታ ከዓመት ፈቃድ ጋር እንዳይደባለቅ የተደረገውን ልዩነት ያሳያል። አዋጁ ከመደበኛው የወሊድ ፈቃድ በተጨማሪ የጽንስ መቋረጥ በሚከሰትበት ጊዜ ለሠራተኛዋ የሚሰጠውን ፈቃድም በሁኔታው መሠረት ይደነግጋል። ከስድስት ወር ያላነሰ እርግዝና ከቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከመጀመሩ በፊት ከተቋረጠና ይህም በሕክምና ማስረጃ ከተረጋገጠ፣ 60 ቀናት የድህረ-ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል። በሌላ በኩል፣ ሠራተኛዋ በቅድመ ወሊድ ፈቃድ ላይ እያለች ጽንሱ ከተቋረጠ፣ የቅድመ ወሊድ ፈቃዷ ይቋረጥና 90 ቀናት የድህረ-ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል። ከሦስት እስከ ስድስት ወር ባለው የእርግዝና ጊዜ ጽንስ ከተቋረጠ ደግሞ፣ መቋረጡ በሕክምና ማስረጃ ከተረጋገጠ ከክፍያ ጋር ፈቃድ እንዲሰጣት አዋጁ ይደነግጋል። የሕጉ ጥበቃ በእናትና በሕፃን ብቻ አይወሰንም። አዋጁ የአባትንም ሚና በማገናዘብ፣ ባለቤቱ በምትወልድበት ጊዜ ለማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ከክፍያ ጋር የ10 የሥራ ቀናት የአባትነት ፈቃድ መብት ይሰጣል። ይህም የወሊድ ፈቃድ የእናትን ጤናና የሕፃኑን ደህንነት ከመጠበቅ ባሻገር፣ አባትየው በወሊድ ወቅት ከቤተሰቡ ጋር እንዲሆንና የቤተሰብ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የሚያስችል ሕጋዊ ጥበቃ መሆኑን ያሳያል። በአጠቃላይ፣ የአዋጁ አንቀጽ 65 የወሊድ ፈቃድን እንደ ተራ የዕረፍት ጊዜ ሳይሆን እናትና ሕፃንን ለመጠበቅ የሚያስፈልግ ሕጋዊ መብት አድርጎ ያዋቅረዋል። የፈቃዱ ጊዜ ከክፍያ ጋር መሆኑ፣ ከወሊድ በፊትና በኋላ የተለያዩ የፈቃድ ጊዜያትን መደንገጉ፣ እንዲሁም እርግዝና በሚቋረጥበት ጊዜ ልዩ ጥበቃ መስጠቱ የድንጋጌውን ዓላማ በግልጽ ያሳያል። ስለዚህ በአንቀጽ 65 መሠረት የተደነገገው የወሊድ ፈቃድ አሠሪው በፈቃዱ የሚሰጠው ጥቅም ሳይሆን፣ በሕግ የተረጋገጠ የሠራተኛዋ መብት ነው። ማስታወሻ፦ የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 ሙሉ ይዘትን ማንበብ የምትፈልጉ ሕጉ ከዚህ በታች ተያይዞ ይገኛል። መልካም አዳር! Jura Legal Update
817
4
+1
Ethiopia_Vehicle_Insurance_Against_Third_Party_Risks_Proclamation.pdf
1 121
5
በተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን፦ የሽፋኑ ወሰን እና የካሣ መጠን በኢትዮጵያ የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ሥርዓት ዋና ዓላማ በተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት ለሚደርሱ የሰው ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ጉዳት እና የአስቸኳይ ሕክምና ወጪዎች ተጎጂዎች በተወሰነው የሕግ ማዕቀፍ መሠረት ካሣ እንዲያገኙ ማድረግ ነው። የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አዋጅ ቁጥር 799/2005 ይህንን መድን አስገዳጅ በማድረግ ደንግጓል። በዚህ ሥርዓት “ሦስተኛ ወገን” ማለት ከመድን ገቢው፣ ከቤተሰቡ፣ ከአሽከርካሪው እና ከመድን ገቢው ተቀጣሪ ሠራተኛ ውጭ ያለ ሌላ ሰው ነው። በመሆኑም የሦስተኛ ወገን መድን ተጠቃሚ የሚሆነው የተሽከርካሪው ባለቤት ራሱ ሳይሆን፣ በተሽከርካሪው ምክንያት ጉዳት የደረሰበት በሕጉ የተገለጸው ሦስተኛ ወገን ነው። የካሣ መጠንን በተመለከተ፣ የሦስተኛ ወገን የተሽከርካሪ አደጋ የመድን ፖሊሲ የአረቦን ተመን እና የካሳ መጠን ክፍያ ደንብ ቁጥር 554/2016 የካሣ ገደቦችን በሰንጠረዥ “ለ” አስቀምጧል። በዚህ መሠረት ለአንድ ሰው የአካል ጉዳት እስከ 250,000 ብር፣ ለሞት አደጋ ከ30,000 እስከ 250,000 ብር፣ ለንብረት ጉዳት እስከ 200,000 ብር እና ለአስቸኳይ ሕክምና ወጪ እስከ 15,000 ብር የካሣ መጠን ተወስኗል። እነዚህ መጠኖች የሕጉ የካሣ ገደቦች እንጂ በእያንዳንዱ ጉዳይ ተጎጂው የሚያገኘው ተመሳሳይ ቋሚ መጠን እንደሆኑ መውሰድ አይገባም። ከዚህ ገደብ በላይ ጉዳት ከደረሰ ደግሞ፣ አግባብነት ባለው ሌላ የሕግ አግባብ መሠረት ቀሪውን ካሣ ከጉዳት አድራሹ እና/ወይም ከንብረቱ ባለቤት መጠየቅ ይቻላል። በሌላ በኩል፣ ሕጉ ከሦስተኛ ወገን መድን ሽፋን ውጭ የሆኑ ሁኔታዎችንም ይዘረዝራል። ለምሳሌ፣ በመድን ገቢው ወይም በቤተሰቡ ላይ የሚደርስ ጉዳት፣ በመድን ገቢው ተቀጣሪ ሠራተኛ በሥራ ላይ እያለ የሚደርስበት ጉዳት፣ በመድን የተሸፈነው ተሽከርካሪ ራሱ ላይ የሚደርስ ጉዳት እና ከኢትዮጵያ ግዛት ውጭ የሚደርስ አደጋ ከዚህ የመድን ሽፋን ውጭ ናቸው። ይህ ግን በሌላ የሕግ አግባብ መሠረት ተጎጂው ሊኖረው የሚችለውን ካሣ መጠየቅ መብት በራሱ የሚያስቀር ነው ማለት አይደለም። በመጨረሻም፣ ማን እንደሦስተኛ ወገን እንደሚቆጠር፣ ምን ዓይነት ጉዳት በመድን ሽፋኑ እንደሚካተት፣ ምን ዓይነት ጉዳት ከሽፋኑ ውጭ እንደሆነ እና የካሣ ገደቦች ምን እንደሆኑ ማወቅ ተገቢ ነው። የሦስተኛ ወገን መድን ሥርዓትም በዋናነት አደጋ ከደረሰ በኋላ ተጎጂዎች የሚያገኙትን ሕጋዊ ጥበቃ ለማረጋገጥ የተዘረጋ ሥርዓት በመሆኑ፣ የሽፋኑን ወሰንና የካሣ ገደቦችን መረዳት ለተሽከርካሪ ባለቤቶች፣ ለአሽከርካሪዎች እና በአደጋ ለሚጎዱ ሰዎች አስፈላጊ ነው። ማስታወሻ፦ የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አዋጅ ቁጥር 799/2005 እና የሦስተኛ ወገን የተሽከርካሪ አደጋ የመድን ፖሊሲ የአረቦን ተመን እና የካሣ መጠን ክፍያ ደንብ ቁጥር 554/2016 ሙሉ ይዘትን ማንበብ የምትፈልጉ ሕጎቹ ከዚህ በታች ተያይዘው ይገኛሉ። መልካም ምሽት! Jura Legal Update
1 133
6
+1
አዋጅ-ቁጥር-790-2005.pdf
1 229
7
አታሼ (Attaché) ምንድነው? ማነው? አታሼ (Attaché) በኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ የዲፕሎማቲክ አገልግሎት የመግቢያ ደረጃ ሲሆን፣ በውጭ አገር በሚገኝ የኢትዮጵያ ሚሲዮን ወይም በሚኒስቴሩ የሚሰጠውን የዲፕሎማቲክ ተልዕኮ ለመፈጸም የዲፕሎማቲክ ሙያን ለመጀመር የሚያስችል የመነሻ ደረጃ ነው። ይህንን ለመረዳት በመጀመሪያ የውጭ ግንኙነት አገልግሎቱን አጠቃላይ መዋቅር ማየት ያስፈልጋል። የውጭ ግንኙነት አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 790/2005 የውጭ ግንኙነት አገልግሎትን የሚመለከተው የሕግ ማዕቀፍ ሲሆን፣ አገልግሎቱ የሚኒስቴሩንና በውጭ አገር የሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖችን የሚያጠቃልል ነው። በዚህ ማዕቀፍ የውጭ ግንኙነት አገልግሎቱ በዲፕሎማቲክ አገልግሎት፣ በአስተዳደርና ቴክኒክ አገልግሎት እና በድጋፍ አገልግሎት ዘርፎች የተደራጀ ሲሆን፣ አታሼ የሚመደበው በዲፕሎማቲክ አገልግሎት ዘርፍ ውስጥ ነው። በዲፕሎማቲክ አገልግሎት ውስጥ የሙያ ዕድገት የሚከናወንባቸው የሙያ መስመሮች እና ደረጃዎች በሕጉ ተደንግገዋል። አታሼ በዚህ የሙያ መስመር የመነሻ ደረጃ ሲሆን፣ ከአታሼ በኋላ የሚመጡት የሙያ ደረጃዎች ሦስተኛ ጸሐፊ፣ ሁለተኛ ጸሐፊ፣ አንደኛ ጸሐፊ፣ አማካሪ እና ከዚያ በላይ ያሉ የሙያ ደረጃዎችን ያካትታሉ። የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ሠራተኞች አስተዳደር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብም የ“career ladder” ትርጉምን በአዋጁ በተደነገጉት የዲፕሎማቲክ አገልግሎት ምድቦች ጋር ያያይዛል። ወደ አታሼ ደረጃ ለመግባትም ሕጉ የተወሰኑ መስፈርቶችን ያስቀምጣል። አመልካቹ ኢትዮጵያዊ ዜጋ መሆን፣ ለሕገ መንግሥቱ ታማኝ መሆን፣ ቢያንስ 21 ዓመት ዕድሜ መሙላት እና እውቅና ከተሰጠው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ቢያንስ የመጀመሪያ ዲግሪ መያዝ ከመሠረታዊ መስፈርቶቹ መካከል ይገኛሉ። በተጨማሪም ከወንጀል ነፃ መሆንን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ፣ የሕክምና ምርመራን ማለፍ እና ሚኒስቴሩ የሚያዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና ማለፍ ይጠየቃል። የውጭ አገር ዜግነት ያለው የትዳር ጓደኛ ያለው አመልካችም ይህንን ለሚኒስቴሩ ማሳወቅ ይጠበቅበታል። ሕጉ ቅጥሩ በግልጽነት፣ በብቃትና በተገቢነት መርሆች መሠረት እንዲከናወን ያስቀምጣል። ከእነዚህ መስፈርቶች ጋር ተያይዞ የ“ተስማሚነት” (suitability) ማጣራት በሕጉ ተደንግጓል። አዋጁ እንደሚያስቀምጠው፣ ሌሎችን የቅጥር መስፈርቶች ያሟላ እጩ ተስማሚ መሆኑን ለማረጋገጥ የእጩው የኋላ ታሪክ ይመረመራል። ይህም የተደበቀ ማንነት አለመኖሩን፣ ከተለያዩ የውስጥና የውጭ ኃይሎች ተፅዕኖ ነፃ መሆኑን፣ ለተለያዩ ጎጂ ንጥረ ነገሮችና ባህሪያት ሱስ የሌለበት መሆኑን፣ ከወንጀል ነፃ መሆኑን፣ ሚስጥራዊ መረጃን የመጠበቅ ብቃት መኖሩን እና በአጠቃላይ ብሔራዊ ተልዕኮውን በታማኝነት ለመፈጸም ብቁ መሆኑን ያካትታል። ይህ ማጣራት የሚያሳየው አታሼነት የሚጀምረው በትምህርት ብቃት እና በፈተና ውጤት ብቻ እንዳልሆነ ነው። የዲፕሎማቲክ አገልግሎት ሠራተኛ በሥራው ምክንያት ሊያገኛቸው የሚችላቸውን ሚስጥራዊ መረጃዎች መጠበቅ እና የአገራዊ ጥቅምን በታማኝነት ማስጠበቅ የሚጠይቅ በመሆኑ፣ suitability የቅጥር ሂደቱ ውስጥ መስፈርት ሆኖ ተደንግጓል። የቅጥር ሂደቱ ከተጠናቀቀ በኋላም እጩው ወዲያውኑ ቋሚ የዲፕሎማቲክ አገልግሎት ሠራተኛ አይሆንም። የመግቢያ ፈተናውን ያለፈና በሕጉ የተደነገጉትን መስፈርቶች ያሟላ አመልካች እንደ ሙከራ ጊዜ ሠራተኛ (probationer) ይቀጠራል። የሙከራ ጊዜው ሁለት ዓመት ከስድስት ወር ሲሆን፣ አንድ ዓመት የንድፈ ሀሳብ ሥልጠና እና አንድ ዓመት ከስድስት ወር የሥራ ላይ ሥልጠና ያካትታል። በሙከራ ጊዜው የእጩው ሙያዊ ብቃት፣ ክህሎት እና የሙያዊ ሥነ-ምግባር ግዴታዎችን መከተሉ ይመዘናል። የሙከራ ጊዜው በተገቢ ውጤት መጠናቀቁም ለቋሚ ቅጥሩ ወሳኝ ነው። ሕጉ እያንዳንዱ የምዘና ውጤት አጥጋቢ እንዲሆን ያስቀምጣል፤ ውጤቱ ዝቅተኛ ከሆነ የሙከራ ጊዜው ለተጨማሪ ስድስት ወር ሊራዘም ይችላል። በተራዘመው ጊዜም አጥጋቢ ውጤት ካላመጣ የሥራ ውሉ ያለካሣ ሊቋረጥ ይችላል። ሁለት ዓመት ከስድስት ወሩን የሙከራ ጊዜ በአጥጋቢ ውጤት ያጠናቀቀ ሰው ቋሚ የዲፕሎማቲክ አገልግሎት ሠራተኛ ሆኖ ይቀጠራል። አታሼ መሆን የሙያ መስመሩ መጨረሻ ሳይሆን የሙያ ዕድገት መነሻ ነው። ቋሚ የዲፕሎማቲክ ሠራተኛ ከአንድ የሙያ ደረጃ ወደ ቀጣዩ ደረጃ ለማለፍ የምዘና ውጤት፣ ተገቢ ሥልጠና፣ የአገልግሎት ዘመን፣ የብቃት ማረጋገጫ ፈተና እና የsuitability ማረጋገጫ የሚያካትቱ መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅበታል። ከአታሼ ወደ ሦስተኛ ጸሐፊ ለማለፍ የተደነገገው የአገልግሎት ጊዜም ሁለት ዓመት ከስድስት ወር ነው። ከዚህ ሁሉ ሂደት መረዳት የሚቻለው የዲፕሎማቲክ አገልግሎት ሙያዊ ብቃትን፣ ታማኝነትን፣ ተገቢነትን እና ተጠያቂነትን መሠረት ያደረገ የሙያ መስክ መሆኑን ነው። በዚህ የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ “አታሼ” የሚለው ማዕረግ የዲፕሎማቲክ ሙያ የመነሻ ደረጃን የሚያመለክት ሲሆን፣ ከመግቢያ መስፈርቶችና የተስማሚነት ማጣራት ጀምሮ እስከ ሥልጠና፣ ሙከራ፣ ምዘና እና የሙያ ዕድገት ድረስ ያለው ሂደት በሕግ የተደነገገ ነው። የውጭ ግንኙነት አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 790/2005 ዓ.ም እና የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ሠራተኞች አስተዳደር ደንብ ሙሉ ይዘትን ማንበብ የምትፈልጉ አንባቢዎች፣ ሕጎቹ ከዚህ በታች ተያይዘው ይገኛሉ። የዲፕሎማቲክ ሙያን ለመቀላቀል ፍላጎት ያላችሁም የሥራ ማስታወቂያውን በጥንቃቄ በማንበብ የተደነገጉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ከሆነ ማመልከት እና ዕድላችሁን መሞከር ትችላላችሁ። መልካም ዕድል! Jura Legal Update ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
1 310
8
没有文字...
1 148
9
239267.pdf
1 144
10
የሰበር ውሳኔ | መ/ቁ. 239267 | 04/02/2018 ዓ.ም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሰባት (7) ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተሰጠው ይህ የሰበር ውሳኔ፣ ሀሰተኛ ሰነድን በመጠቀም የማታለል ወንጀል ሲፈጸም የሚተገበሩ የወንጀል ሕግ ድንጋጌዎችን በተመለከተ ቀደም ሲል የነበረውን የሰበር የሕግ ትርጉም ቀይሯል። ቀደም ሲል በሰበር መዝገብ ቁጥር 232750፣ 234082፣ 104637 እና 107195 እንዲሁም በመሳሰሉ መዝገቦች ላይ የተያዘው የሕግ ትርጉም፣ ሀሰተኛ ሰነድን በመጠቀም የማታለል ወንጀል ሲፈጸም፣ አድራጊው በማታለል ወንጀል እንጂ ሀሰተኛ ሰነድን በመጠቀም በተደራቢነት ሊቀጣ አይገባም የሚል ነበር። አሁን በመዝገብ ቁጥር 239267 የሰበር ችሎቱ ይህንን ቀደም ሲል የተያዘውን የሕግ ትርጉም በመቀየር፣ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 61(3) ስር የተደነገገው ቢኖርም፣ ሀሰተኛ ሰነድን በመጠቀም የማታለል ወንጀል ሲፈጸም፣ በአንቀጽ 699 መሠረት አግባብነት ያላቸው ድንጋጌዎች በተደራቢነት ተፈጻሚ ይሆናሉ ብሎ ተርጉሟል። በመሆኑም፣ ይህ ውሳኔ በዚህ ጉዳይ ላይ ከቀደመው የሰበር አቋም የተለየ አዲስ የሕግ ትርጉም ያስቀመጠ ነው። ሙሉ የሰበር ውሳኔው ከታች ተያይዟል። Jura Legal Update
1 122
11
Job Vacancy Announcement Wolkite University — School of Law Wolkite University invites qualified applicants for academic posi+5
Job Vacancy Announcement Wolkite University — School of Law Wolkite University invites qualified applicants for academic positions in the School of Law (as well as various other fields across medicine, technology, CS, social sciences, and business). * Position: Assistant Lecturer / Lecturer * Qualification: LL.B / LL.M * ​Salary: 21,238 / 25,285 ETB * Field of Specialization: Public International Law / Tax Law / Human Rights Law / Construction Law & Related Fields * Vacancies: 02 Applicants should refer to the official vacancy announcement for application procedures and deadlines. Jura Legal Update
1 215
12
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ - የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ - የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን
1 314
13
#Some Important Legal Tips (Basic) 8 መሠረታዊ ነጥቦች: 1. አንድ ሰው ተከሰሰ ማለት ጥፋተኛ ነው ወይም ተጠያቂነቱ ተረጋግጧል ማለት አይደለም። ጥፋተኛነት ወይም ተጠያቂነት በሕግ አግባብ ተመስርቶ በሂደት የሚወሰን ጉዳይ ነው። 2. ሕግ ሁሉም ውሎች በጽሑፍ እንዲደረጉ አያስገድድም። ተዋዋዮች ውላቸውን በቃል ወይም በጽሑፍ መልክ ለማድረግ በመርህ ደረጃ ነፃነት አላቸው። ውል በጽሑፍ መደረግ የግድ የሚሆነው ተፈጻሚው ሕግ ይህንን እንደ ግዴታ ሲያስቀምጥ ነው። 3. ክስ መመስረት በራሱ ባለመብትነትን አያረጋግጥም። ክስ መመስረት አንድ ጥያቄን በሕግ አግባብ ለተገቢው አካል ለማቅረብ የሚያስችል ሂደት ነው። የተጠየቀው መብት መኖሩና የሚገባው ሕጋዊ መፍትሔ ግን በቀረበው ማስረጃና ተፈጻሚ በሚሆነው ሕግ መሠረት በዳኝነት አካሉ ይወሰናል። 4. ሕጋዊነትና ሞራላዊነት አንድ አይደሉም። አንድ ድርጊት ሕጋዊ መሆኑ በራሱ በሞራል ትክክል ነው ማለት አይደለም። በተመሳሳይም ሞራላዊ ተቀባይነት የሌለው ድርጊት ሁልጊዜ ሕገወጥ ነው ማለት አይቻልም። ሕጋዊነት በሕግ የሚወሰን ሲሆን፣ ሞራላዊነት ደግሞ ከሥነ-ምግባርና ከማኅበራዊ እሴቶች ጋር ይያያዛል። 5. አንድ ሰው ለጥያቄ ወይም ለምርመራ በፖሊስ መጠራቱ በራሱ ተከሷል ወይም ጥፋተኛ ነው ማለት አይደለም። የፖሊስ ጥሪ፣ የምርመራ ሂደት፣ ክስ መቅረብ እና ጥፋተኛነት የተለያዩ ነገሮች ናቸው። 6. የምስክር መኖር ብቻ ጉዳዩን አያረጋግጥም። የምስክሩ ተዓማኒነት፣ የሰጠው ምስክርነት፣ ተገቢነቱ እና ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር ያለው ተያያዥነት በሕግ አግባብ ይመዘናል። በመሆኑም “ምስክር አለ” የሚለው ብቻ የጉዳዩን ውጤት አይወስንም። 7. አንድ ውል በሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ጽ/ቤት መደረጉ ወይም መረጋገጡ ብቻ ውሉ በሁሉም መልኩ ሕጋዊና ተፈጻሚ ነው ማለት አይደለም። የሰነድ ማረጋገጥ ከውሉ ይዘት፣ ከተዋዋዮች ሕጋዊ አቅም እና ከሌሎች የሕግ መስፈርቶች ጋር የሚመረመር የተለየ ጉዳይ ነው። ስለዚህ ውሉ በሰነዶች ጽ/ቤት መረጋገጡ በሌላ የሕግ ምክንያት እንዳይፈርስ ወይም እንዳይሰረዝ ፍጹም ዋስትና አይሰጥም። 8. አንድ ሰው ባለዕዳ በመሆኑ ብቻ አበዳሪው በራስ ፈቃድ የባለዕዳውን ንብረት ወይም ገንዘብ መውሰድ ይችላል ማለት አይደለም። አበዳሪው ያለውን መብት ለማስፈጸም ሕጉ የደነገገውን ሥርዓት መከተል ይገባዋል። Jura Legal Update
1 375
14
没有文字...
1 099
15
+3
Proclamation No 1338-2016.pdf
1 349
16
ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጋር በተያያዙ የአገልግሎት፣ የሥልጣንና የክፍያ ጉዳዮችን የሚመለከቱ አግባብነት ያላቸው የሕግ ሰነዶች ከአባሪዎቻቸው ጋር፦ 1. የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አዋጅ ቁጥር 1338/2016 (Immigration and Citizenship Service Proclamation No. 1338/2024) አዋጁ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትን እንደገና ለማቋቋም የወጣ ሲሆን፣ ከፓስፖርትና ቪዛ፣ ዜግነት፣ የመኖሪያ ፈቃድ፣ የውጭ ዜጎች ምዝገባ እና የሲቪል ምዝገባ ጋር የተያያዙ የአገልግሎቱን ሥልጣንና ተግባራት ይደነግጋል። 2. የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የአገልግሎት ክፍያ አፈጻጸም ደንብ (Immigration and Citizenship Service Fee Regulation No. 587/2026) ደንቡ ለተለያዩ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎቶች የሚከፈሉ ክፍያዎችን አፈጻጸም ይደነግጋል። 3. የደንቡ የክፍያ አባሪዎች (Schedules 1–14)(Amharic & English Fee Annexes) አባሪዎቹ የተለያዩ የኢሚግሬሽን፣ የዜግነትና የሲቪል ምዝገባ አገልግሎቶችን የክፍያ ዝርዝር ይይዛሉ። ሙሉ የሕግ ሰነዶቹ ከታች ተያይዘዋል። Jura Legal Update
1 267
17
LEGAL VACANCY | LECTURER – LAW Madda Walabu University is inviting applications for the following Law Lecturer positions: Sch+2
LEGAL VACANCY | LECTURER – LAW Madda Walabu University is inviting applications for the following Law Lecturer positions: School of Law LL.M in Public International Law — 2 positions LL.M — 4 positions Shashemene Campus LL.M — 4 positions Academic Rank: Lecturer Salary: ETB 25,285 Experience: 0 years and above Total Law Lecturer positions: 10 Applicants should refer to the official vacancy announcement for application procedures and deadlines. Jura Legal Update
1 203
18
1333_2024_የፌደራል_መንግሥት_ግዥ_እና_ንብረት_አስተዳደር_አዋጅ.pdf
1 331
19
የፌዴራል የመንግሥት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1333/2016 የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደርን ሥርዓት ለማዘመን፣ ግልጽነትን፣ ፍትሐዊነትን፣ ውጤታማነትንና ተጠያቂነትን ለማጎልበት የወጣ የሕግ ማዕቀፍ ነው። አዋጁ ይዞ ከመጣቸው ዋና አዳዲስ ጉዳዮች መካከል የተፈጻሚነት ወሰኑን ወደ መንግሥት የልማት ድርጅቶች ማስፋት፣ ከዓለም አቀፍ እና ከሌሎች መንግሥታት ጋር በሚደረጉ ስምምነቶች የሚመጡ ግዴታዎችን ታሳቢ ማድረግ፣ የግዥና የንብረት አስተዳደር መርሆችን ማስፋት፣ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነትን ማበረታታት፣ የፌዴራል መንግሥት የግዥና ንብረት ባለሥልጣንን ማቋቋም፣ የግዥ ሰነዶችን በሥርዓት መያዝ፣ ከተወዳዳሪዎችና አቅራቢዎች ጋር ያለውን ግንኙነት በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ማከናወን እና ዘመናዊ የግዥና ንብረት አስተዳደር ሥርዓትን ማስፋት ይገኙበታል። የአዋጁን ሙሉ ሰነድ ከዚህ በታች ያገኛሉ። Jura Legal Update
1 294
20
አንድርያስ እሸቴ ሲታወሱ! ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ ታዋቂ ፈላስፋ፣ የህግ እና የፖለቲካ ምሁር፣ እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መሪ ነበሩ። ዶ/ር አንድርያስ እሸቴ ከፍተኛ ትምህርታቸውን በአሜሪ+2
አንድርያስ እሸቴ ሲታወሱ! ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ ታዋቂ ፈላስፋ፣ የህግ እና የፖለቲካ ምሁር፣ እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መሪ ነበሩ። ዶ/ር አንድርያስ እሸቴ ከፍተኛ ትምህርታቸውን በአሜሪካ ታዋቂ ከሆኑት ዊሊያምስ ኮሌጅ (Williams College) እና ያሌ ዩኒቨርሲቲ (Yale University) የተከታተሉ ሲሆን፣ በፈላስፋነት ዶክተሬት (PhD) አግኝተዋል። በበርካታ የታወቁ የዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ያስተማሩ ሲሆን በምዕራብ ሀገራት የታወቁ ፍልስፍናዎችን ከኢትዮጵያ የፖለቲካ እና የማህበራዊ ሁኔታዎች ጋር በማገናኘት ይታወቃሉ። ከ1995 እስከ 2003 ዓ.ም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል። በቆይታቸውም የዩኒቨርሲቲውን የምርምር እና የትምህርት ጥራት ለማሳደግ፣ እንዲሁም ድህረ-ምረቃ ፕሮግራሞችን ለማስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። በ1987 ዓ.ም የፀደቀውን የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት በማዘጋጀት ሂደት ውስጥ በዋና አማካሪነት እና ተሳታፊነት ጎልቶ የሚታይ ሚና ተጫውተዋል። በተጨማሪም በሰብአዊ መብቶች፣ በዲሞክራሲ፣ በብሄር እና የፌደራሊዝም አስተሳሰቦች ላይ በርካታ ፅሁፎችን እና ትንተናዎችን አቅርበዋል። በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል በነበረው የድንበር ውዝግብ እና ጦርነት ወቅት በሰላም ንግግሮች እና በአልጀርሱ ስምምነት ሂደት ውስጥ በህግና ዲፕሎማሲ አማካሪነት ተሳታፊ ነበሩ። በኢትዮጵያ የዘመናዊ የፖለቲካ አስተሳሰብ እና የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስም ካላቸው ምሁራን መካከል አንዱ ነበሩ። Jemal Abdulaziz
1 342