Jura Legal Update
رفتن به کانال در Telegram
1 504
مشترکین
+224 ساعت
+827 روز
+15530 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئن '26
ژوئن '26
+178
در 1 کانالها
مه '26
+530
در 3 کانالها
Get PRO
آوریل '26
+247
در 1 کانالها
Get PRO
مارس '26
+650
در 2 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 22 ژوئن | +5 | |||
| 21 ژوئن | +3 | |||
| 20 ژوئن | +2 | |||
| 19 ژوئن | +8 | |||
| 18 ژوئن | +6 | |||
| 17 ژوئن | +22 | |||
| 16 ژوئن | +43 | |||
| 15 ژوئن | +5 | |||
| 14 ژوئن | +4 | |||
| 13 ژوئن | +3 | |||
| 12 ژوئن | +3 | |||
| 11 ژوئن | +3 | |||
| 10 ژوئن | +8 | |||
| 09 ژوئن | +6 | |||
| 08 ژوئن | +4 | |||
| 07 ژوئن | +4 | |||
| 06 ژوئن | +2 | |||
| 05 ژوئن | +9 | |||
| 04 ژوئن | +12 | |||
| 03 ژوئن | +9 | |||
| 02 ژوئن | +15 | |||
| 01 ژوئن | +2 |
پستهای کانال
የኮንዶሚኒየም ቤት የደረሰው ሰው ዕጣው ከደረሰው 5 ዓመት ባይሞላውም እንኳ፣ ሌላ የኮንዶሚኒየም ቤት ከደረሰው ሌላ ሰው ጋር በስምምነት ቤታቸውን ሊቀያየሩ ይችላሉ?
የኮንዶሚኒየም ቤት የደረሰው ሰው ሌላ የኮንዶሚኒየም ቤት ከደረሰው ሰው ጋር ዕጣው ከደረሰው አምስት ዓመት ባይሞላውም በልውውጥ ወይም በስምምነት ሊቀያየሩ ይችላሉ ወይስ አይችሉም የሚለው ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ ይነሳል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካላት የአስተዳደሩን ቤቶች የማስተላለፍ ኃላፊነትና አፈጻጸሙን ለመወሰን የወጣው አዋጅ ቁጥር 19/97 አንቀጽ 14 (2) ድንጋጌ ገዢው ጠቅላላው ዋጋውን ከፍሎ ቢያጠናቅቅም ቤቱን ለሦስተኛ ወገን በሽያጭ ወይም በስጦታ ማስተላለፍ የሚችለው ቤቱን ከገዛ 5 ዓመት ሲሞላው ብቻ ይሆናል በማለት ይደነግጋል።
ድንጋጌው በግልጽ ቃል የጠቀሰው ቤቱን በሽያጭ ወይም በስጦታ ማስተላለፍን በመሆኑ፣ ዕጣው ከወጣ 5 ዓመት ባልሞላው ቤት ላይ የተደረገ የኮንዶሚኒየም ቤት ልውውጥ በዚህ አዋጅ መሠረት የተከለከለ ነው ወይ? የሚለው ነጥብ መታየት ያለበት ጥያቄ ነው።
ይህን ጥያቄ በተመለከተ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቅጽ 19 በሰበር መዝገብ ቁጥር 105919 ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል። ችሎቱ በውሳኔው ላይ ድንጋጌው የከለከለው ቤትን በሽያጭ ወይም በስጦታ ማስተላለፍን እንጂ ልውውጥን ወይም ቅይይርን ባለመሆኑ፣ በዚህ አግባብ የተደረገው የልውውጥ ውል ሕገወጥ ነው ሊባል አይችልም ሲል ወስኗል።
ለዚህም እንደ ምክንያት የጠቀሰው፣ ሕግ አውጭው ይህንንም ልውውጥ መከልከል ፈልጎ ቢሆን ኖሮ "በማናቸውም አኳኋን" ማስተላለፍ አይቻልም የሚል አጠቃላይ የሆነ ቋንቋ መጠቀም ይችል እንደነበር ነው።
ከዚህም በላይ በዕጣ የደረሰው ሰው ቤቱን በሽያጭም ሆነ በስጦታ ለሦስተኛ ወገን እስከ 5 ዓመት ጊዜ ድረስ ማስተላለፍ አይችልም ተብሎ በሕግ መብቱ ሲገደብ ታሳቢ የተደረገው፣ ግለሰቡ በጊዜያዊ ችግር ምክንያት ቤቱን ሸጦ መጠለያ እንዳያጣ በማሰብ ነው።
በለውጥ ጊዜ ግን አንደኛው ቤት በሌላ ቤት የሚተካ በመሆኑና ያለቤት የሚቀር ሰው ስለሌለ፣ ልውውጥን መከልከል ከሕጉ ዓላማ አንጻር ምክንያታዊ አይሆንም።
ስለዚህም የኮንዶሚኒየም ቤት የደረሰው ሰው ሌላ የኮንዶሚኒየም ቤት ከደረሰው ሰው ጋር እጣው ከደረሰው 5 ዓመት ባይሞላውም እንኳ በልውውጥ ወይም በስምምነት የመቀያየር ሙሉ ሕጋዊ መብት አላቸው የሚል ድምዳሜ ላይ መድረስ ይቻላል።
መልካም ጊዜ!
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/
| 2 | بدون متن... | 208 |
| 3 | 44588.pdf | 299 |
| 4 | በአሰሪና ሠራተኛ ክርክር ችሎት ሠራተኛው 'ከሥራ ለማሰናበት የሚያበቃ ጥፋት አልፈጸመም' ተብሎ መወሰኑ፣ አሰሪው በሠራተኛው ጥፋት ወይም ጉድለት ምክንያት በድርጅቱ ላይ የደረሰውን የገንዘብ ወይም የንብረት ጉዳት ካሣ በፍትሐብሔር ችሎት የመጠየቅ መብቱን አያስቀርም። ክሱም ዳግም ዳኝነት (Res Judicata) ተብሎ ሊወሰድ አይችልም።
ሰ/መ/ቁ.44588
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/ | 295 |
| 5 | 134240.pdf | 390 |
| 6 | በትራፊክ አደጋ ከደረሰ የሞት አደጋ የተነሳ በራሳቸው ስም ሆነው በመተዳደሪያ ረገድ ለሚደርስባቸው ጉዳት ካሣ ለመጠየቅ የሚችሉት የተጎጂ ባል ወይም ሚስት፤ ወይም ወላጆችና ልጆች ብቻ እንጂ ወንድም ወይም እህት መጠየቅ ስላለመቻላቸው
የሰ/መ/ቁ.134240 (ቅጽ 22)
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/ | 384 |
| 7 | ለግንዛቤ ያህል...
በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 139 (2) መሠረት፣ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሥራ ክርክር ችሎት ማንኛውም የግል የሥራ ክርክር ጉዳይ በቀረበለት በ60 ቀናት ውስጥ ውሳኔ መስጠት አለበት።
በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በተሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ማንኛውም ወገን፣ ውሳኔው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ በ30 ቀናት ውስጥ ይግባኙን ለከፍተኛ ፍርድ ቤት የሥራ ክርክር ችሎት ማቅረብ እንደሚኖርበት በአዋጁ አንቀጽ 139(3) ላይ ተደንግጓል።
መልካም ምሽት!
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/ | 420 |
| 8 | 131863.pdf | 415 |
| 9 | በወንጀል ተጠርጥሮ በሕግ ከለላ ስር የሚገኝን ተጠርጣሪ
በዋስትና የመለቀቅ ጥያቄ ባነሳ ጊዜ ተጠርጣሪው በከተማው
ውስጥ ቋሚ የመኖሪያ /የመታወቂያ/ አድራሻ የለውም በማለት
የዋስትና መብቱን መከልከል ሕገ መንግስታዊ ስላለመሆኑ
ሰ/መ/ቁ.131863 (ቅጽ 20)
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/ | 420 |
| 10 | 53985.pdf | 471 |
| 11 | የሕብረት ስምምነት በሌለበት ድርጅት ሠራተኛን አግዶ ማቆየት ይቻላል? (የሰበር መ/ቁ 53985)
ጉዳዩ በአሰሪና ሠራተኛ ሕግ ላይ የተመለከተውን ሠራተኛን ከሥራ አግዶ የማቆየት ሥልጣን እና የሕብረት ስምምነት መኖር/አለመኖር ያለውን ግንኙነት የሚመለከት ነው።
የክርክሩ መነሻ ተጠሪ በድርጅቱ ውስጥ በሥራ ላይ እያሉ በጋዜጣ ላይ አስተያየት ሰጥተዋል በሚል፣ አሰሪው (አመልካች) ጉዳዩን አጣርቶ የዲስፕሊን እርምጃ እስኪወስድ ድረስ ለአንድ ወር ያህል ከሥራና ከደመወዝ ማገዱ ነበር።
ጉዳዩን መጀመሪያ የተመለከቱት የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ እና የከፍተኛው ፍርድ ቤት በአዋጁ አንቀጽ 27(4) መሠረት ሠራተኛን ከሥራ አግዶ ማቆየት የሚቻለው በሕብረት ስምምነት ላይ ከተደነገገ ብቻ ነው፤ ሕብረት ስምምነት በሌለበት ሁኔታ ማገድ ሕገ-ወጥ ነው በማለት ተጠሪ ወደ ሥራው እንዲመለስና ያልተከፈለውን ደመወዝ እንዲያገኝ ወስነው ነበር።
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎት የሕብረት ስምምነት በሌለበት ድርጅት ውስጥ አሰሪው በአሰሪና ሠራተኛ አዋጁ አንቀጽ 27 (4) መሠረት የዲስፕሊን ጥፋት የፈጸመን ሠራተኛ ጉዳዩ እስኪጣራ ድረስ ለአንድ ወር ከሥራ አግዶ የማቆየት መብት አለው ወይስ የለውም? የሚለውን ነጥብ በጭብጥነት በመያዝ መዝገቡን መርምሮታል።
ችሎቱም በአዋጁ አንቀጽ 27 (4) መሠረት ሠራተኛን ከሥራ አግዶ ማቆየት የተፈቀደበት ዋና ዓላማ፣ አሰሪው በአስተዳደራዊ ሥልጣኑ ተጠቅሞ ሠራተኛው ፈጽሞታል የተባለውን የዲስፕሊን ወይም የስነ-ምግባር ግድፈት በተገቢው መንገድ ለማጣራትና ለመመርመር እንዲችል ዕድል ለመስጠት መሆኑን አስገንዝቧል።
ሕጉ “በሕብረት ስምምነት ሊወሰን ይችላል” ሲል የእገዳውን አፈጻጸምና ዝርዝር ሁኔታዎች አሰሪና ሠራተኛ ማኅበሩ በስምምነት ሊያሻሽሉት ወይም ሊወስኑት ይችላሉ ለማለት እንጂ፣ እገዳ ለመጣል የግድ የሕብረት ስምምነት መኖር አለበት ማለት እንዳልሆነ ችሎቱ አብራርቷል። በመሆኑም ድንጋጌው በይዘቱ ፈቃጅ እንጂ እገዳን የሚከለክል አይደለም።
የሕጉ ትርጓሜ ሁልጊዜም ቢሆን የሕጉን ዋና ዓላማ በሚያሳካ መልኩ መሆን እንዳለበት የገለጸው የሰበር ችሎቱ፣ የሕብረት ስምምነት የሌለው ድርጅት ጥፋት የፈጸመን ሠራተኛ መርምሮ ጥፋቱን ለማረጋገጥ እንዳይችል ማድረግ የሕጉን ዓላማ ማለትም እውነትን ማውጣት፣ ምርታማነትን ማሳደግና የኢንዱስትሪ ሰላምን ማስፈንን የሚቃረን ነው ብሏል።
ስለሆነም የሕብረት ስምምነት የሌለው አሰሪ ሠራተኛውን ማገድ አይችልም ለማለት የሚያስችል ሕጋዊ ምክንያት የለም በማለት የስር ፍርድ ቤቶችን ውሳኔ የሻረው ሲሆን፣ የሕብረት ስምምነት ባይኖርም አሰሪው ሠራተኛውን አግዶ የማቆየት ሕጋዊ ሥልጣን እንዳለው የሚያረጋግጥ አስገዳጅ የሕግ መርህ አስቀምጧል።
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/ | 473 |
| 12 | ትዕዛዝ አለማክበር (ሰበር).pdf | 485 |
| 13 | የአሰሪን ትዕዛዝ አለማክበር፡ የሥራ ውልን ሕጋዊ በሆነ መንገድ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነውን?
====================
By Jura Legal Update
ታህሳስ 04 ቀን 2018 ዓ.ም የተጻፈ (አሁን በድጋሚ የቀረበ)
አዲስ አበባ፥ ኢትዮጵያ
====================
የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 13 (2) ማንኛውም ሠራተኛ በሥራ ውሉና በሥራ ደንቡ መሰረት በአሰሪው የሚሰጠውን ሕጋዊ ትዕዛዝ የመፈፀም መሰረታዊ ግዴታ እንዳለበት በግልጽ ይደነግጋል። ሆኖም ይህንን መሰረታዊ ግዴታ ያለመወጣት ውጤቱ ምን እንደሆነ አዋጁ በግልጽ ያስቀመጠው ነገር የለም።
እንደሚታወቀው አዋጁ አሰሪው የሥራ ውልን ያለ ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሊያቋርጥባቸው የሚችሉ ምክንያቶችን በዝርዝር አስቀምጧል። የአዋጁ አንቀጽ 27 (1) መግቢያ ክፍል እንዲህ ይላል፦
"በህብረት ስምምነት በሌላ አኳኋን ካልተወሰነ በስተቀር የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ማቋረጥ የሚቻለው በሚከተሉት ምክንያቶች ብቻ ነው ..."።
ይህ የሚያሳየው በአንቀጽ 27 (1) አሰሪው የሥራ ውልን ያለ ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሊያቋርጥባቸው የሚችሉ ምክንያቶች ተዘርዝረው የተቀመጡ (exhaustive list) መሆኑን ነው።
በሕብረት ስምምነት ተጨማሪ የውል ማቋረጫ ምክንያት ካልተወሰነ በስተቀር ጥፋትን መሰረት በማድረግ በሌላ ምክንያት ሠራተኛን ማሰናበት አይቻልም።
በአዋጁ በአንቀጽ 27 የተገደበ ዝርዝር ውስጥ "ሕጋዊ ትዕዛዝን አለመቀበል" ወይም "ትዕዛዝን ለመፈጸም ፈቃደኛ አለመሆን" የሚል ምክንያት በግልጽ አልተካተተም።
ይህ ማለት በሕብረት ስምምነት የሥራ ውል ማቋረጫ ምክንያት ተደርጎ ካልተወሰነ በስተቀር፣ ትዕዛዝን አለመቀበልን መሰረት ያደረገ ስንብት ሕጋዊነት በሕጉ አጻጻፍ መሰረት አጠያያቂ ይሆናል እንደማለት ነው።
ለነገሩ ያ ግልጽ ሆኖ ተዘርዝሮ ባይቀርብም፣ አንዳንድ የትዕዛዝ አለመቀበል ሁኔታዎች በአንቀጽ 27 (1) ውስጥ ባሉ ተዛማጅ ግን የተለዩ ንዑስ አንቀጾች ሥር በትርጉም ሊሸፈኑ ይችላሉ ሊባል ይችላል።
ለምሳሌ ንዕስ አንቀጽ (ረ) ላይ "እንደጥፋቱ ክብደት በሥራው ቦታ አምባጓሮ ወይም ጠብ አጫሪነት ተጠያቂ መሆን" ለሥራ ውል ማቋረጫ ምክንያት ሆኖ ተቀምጧል። አለመታዘዙ ከአምባጓሮ ወይም ጠብ ጋር ከተያያዘ ስንብቱ በዚህ ንዑስ አንቀጽ ሥር ሊወድቅ ይችላል።
በንዑስ አንቀጽ (ሸ) ላይ "በሆነ ዓይነት ጥፋት ወይም በከፍተኛ ቸልተኝነት ወይም ሆን ብሎ በአሰሪው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ" ለሥራ ውል ማቋረጫ ምክንያት ሆኖ ተቀምጧል። አለመታዘዙ የኢኮኖሚ ኪሣራ ወይም ጉዳት ካስከተለ፣ ይህን እንደ "በአሰሪው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ" ለጥጦ በመውሰድ፣ በዚህ ንዑስ አንቀጽ መሰረት ውሉ ሊቋረጥ ይችላል።
ሆኖም ግን አለመታዘዙ ከጉዳት/ኪሣራ ወይም ከጠብ በፀዳ መልኩ የተፈጸመ ከሆነ (ማለትም ንዑስ አንቀጽ (ረ) ወይም (ሸ) ተፈጻሚ ሊሆን በማይችልበት ሁኔታ)፣ አለመታዘዝን ብቻ መሰረት በማድረግ ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሥራ ውል ማቋረጥ ይቻላል ወይ? የሚለው አጠያያቂ ይሆናል።
አለመታዘዙ በአንቀጽ 27 (1) ውስጥ ባሉ ተዛማጅ ግን የተለዩ ንዑስ አንቀጾች ሥር በትርጉም ሊሸፈን የማይችል ከሆነ የአሰሪው የሥራ ውል ማቋረጡ እርምጃ ሕገ-ወጥ ተብሎ የመፈረጅ አደጋም ሊያጋጥመው ይችላል።
ሕጉ መታዘዝን በአንቀጽ 13 (2) ላይ እንደ መሰረታዊ ግዴታ አስቀምጦ፣ ነገር ግን ለዚህ ግዴታ ጥሰት ግልጽ የሆነ ሕጋዊ መፍትሄ (ውጤት) አለማስቀመጡ አጠያያቂ ነው።
ሕግ አውጪው መታዘዝን እንደ መሰረታዊ ግዴታ አስቀምጦ፣ ነገር ግን አለመታዘዝን እንደ አንድ የተለየ ራሱን የቻለ የውል ማቋረጫ ምክንያት አለማስቀመጡ ያስገርማል። ይህንን ለውል ማቋረጫ ምክንያት አድርጎ በአንቀጽ 27 ላይ ያላስቀመጠው ለምን ይሆን? የሚል ጥያቄም ያስነሳል።
ሕግ አውጪው ይህንን ለውል ማቋረጫ ምክንያት አድርጎ በአንቀጽ 27 ላይ ያላስቀመጠው ይህንን ዓይነቱ ባህሪ ውል ማቋረጥን በሚያስከትልበት ደረጃ ላይ ካልደረሰ በስተቀር እንደ ማስጠንቀቂያ ወይም እገዳ ባሉ ተግሣጻዊ እርምጃዎች እንዲታለፍ አስቦ ይሆን?
ወይስ ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ባህሪ በሌሎቹ ድንጋጌዎች ለመሸፈን በቂ ነው፣ ወይንም በህብረት ስምምነት መፍታት አለበት የሚል አመለካከት ኖሮት?
ወይስ በሌላ ምክንያት?
ወይስ በአጻጻፍ ስህተት ተዘሎ ቀርቶ?
በአጠቃላይ፣ ይህ ጉዳይ ለወደፊቱ አዋጁ በሚከለስበት እና በሚሻሻልበት ጊዜ ውይይት ሊደረግበትና መፍትሔ ሊበጅለት የሚገባ ነው። እስከዚያው ድረስ ግን፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የአሰሪን ትዕዛዝ ካለማክበር ጋር በተያያዘ የሰጣቸውን ሁለት ውሳኔዎች (በቅጽ 18 ላይ እንደታተሙት) ከዚህ በታች አያይዤ አቅርቤያለሁ።
መልካም ንባብ! | 521 |
| 14 | የአሰሪን ትዕዛዝ አለማክበር፡ የሥራ ውልን ሕጋዊ በሆነ መንገድ ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ነውን?
====================
By Jura Legal Update
ታህሳስ 04 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፥ ኢትዮጵያ
====================
የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 13 (2) ማንኛውም ሠራተኛ በሥራ ውሉና በሥራ ደንቡ መሰረት በአሰሪው የሚሰጠውን ሕጋዊ ትዕዛዝ የመፈፀም መሰረታዊ ግዴታ እንዳለበት በግልጽ ይደነግጋል። ሆኖም ይህንን መሰረታዊ ግዴታ ያለመወጣት ውጤቱ ምን እንደሆነ አዋጁ በግልጽ ያስቀመጠው ነገር የለም።
እንደሚታወቀው አዋጁ አሰሪው የሥራ ውልን ያለ ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሊያቋርጥባቸው የሚችሉ ምክንያቶችን በዝርዝር አስቀምጧል። የአዋጁ አንቀጽ 27 (1) መግቢያ ክፍል እንዲህ ይላል፦
"በህብረት ስምምነት በሌላ አኳኋን ካልተወሰነ በስተቀር የሥራ ውልን ያለማስጠንቀቂያ ማቋረጥ የሚቻለው በሚከተሉት ምክንያቶች ብቻ ነው ..."።
ይህ የሚያሳየው በአንቀጽ 27 (1) አሰሪው የሥራ ውልን ያለ ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሊያቋርጥባቸው የሚችሉ ምክንያቶች ተዘርዝረው የተቀመጡ (exhaustive list) መሆኑን ነው።
በሕብረት ስምምነት ተጨማሪ የውል ማቋረጫ ምክንያት ካልተወሰነ በስተቀር ጥፋትን መሰረት በማድረግ በሌላ ምክንያት ሠራተኛን ማሰናበት አይቻልም።
በአዋጁ በአንቀጽ 27 የተገደበ ዝርዝር ውስጥ "ሕጋዊ ትዕዛዝን አለመቀበል" ወይም "ትዕዛዝን ለመፈጸም ፈቃደኛ አለመሆን" የሚል ምክንያት በግልጽ አልተካተተም።
ይህ ማለት በሕብረት ስምምነት የሥራ ውል ማቋረጫ ምክንያት ተደርጎ ካልተወሰነ በስተቀር፣ ትዕዛዝን አለመቀበልን መሰረት ያደረገ ስንብት ሕጋዊነት በሕጉ አጻጻፍ መሰረት አጠያያቂ ይሆናል እንደማለት ነው።
ለነገሩ ያ ግልጽ ሆኖ ተዘርዝሮ ባይቀርብም፣ አንዳንድ የትዕዛዝ አለመቀበል ሁኔታዎች በአንቀጽ 27 (1) ውስጥ ባሉ ተዛማጅ ግን የተለዩ ንዑስ አንቀጾች ሥር በትርጉም ሊሸፈኑ ይችላሉ ሊባል ይችላል።
ለምሳሌ ንዕስ አንቀጽ (ረ) ላይ "እንደጥፋቱ ክብደት በሥራው ቦታ አምባጓሮ ወይም ጠብ አጫሪነት ተጠያቂ መሆን" ለሥራ ውል ማቋረጫ ምክንያት ሆኖ ተቀምጧል። አለመታዘዙ ከአምባጓሮ ወይም ጠብ ጋር ከተያያዘ ስንብቱ በዚህ ንዑስ አንቀጽ ሥር ሊወድቅ ይችላል።
በንዑስ አንቀጽ (ሸ) ላይ "በሆነ ዓይነት ጥፋት ወይም በከፍተኛ ቸልተኝነት ወይም ሆን ብሎ በአሰሪው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ" ለሥራ ውል ማቋረጫ ምክንያት ሆኖ ተቀምጧል። አለመታዘዙ የኢኮኖሚ ኪሣራ ወይም ጉዳት ካስከተለ፣ ይህን እንደ "በአሰሪው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ" ለጥጦ በመውሰድ፣ በዚህ ንዑስ አንቀጽ መሰረት ውሉ ሊቋረጥ ይችላል።
ሆኖም ግን አለመታዘዙ ከጉዳት/ኪሣራ ወይም ከጠብ በፀዳ መልኩ የተፈጸመ ከሆነ (ማለትም ንዑስ አንቀጽ (ረ) ወይም (ሸ) ተፈጻሚ ሊሆን በማይችልበት ሁኔታ)፣ አለመታዘዝን ብቻ መሰረት በማድረግ ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሥራ ውል ማቋረጥ ይቻላል ወይ? የሚለው አጠያያቂ ይሆናል።
አለመታዘዙ በአንቀጽ 27 (1) ውስጥ ባሉ ተዛማጅ ግን የተለዩ ንዑስ አንቀጾች ሥር በትርጉም ሊሸፈን የማይችል ከሆነ የአሰሪው የሥራ ውል ማቋረጡ እርምጃ ሕገ-ወጥ ተብሎ የመፈረጅ አደጋም ሊያጋጥመው ይችላል።
ሕጉ መታዘዝን በአንቀጽ 13 (2) ላይ እንደ መሰረታዊ ግዴታ አስቀምጦ፣ ነገር ግን ለዚህ ግዴታ ጥሰት ግልጽ የሆነ ሕጋዊ መፍትሄ (ውጤት) አለማስቀመጡ አጠያያቂ ነው።
ሕግ አውጪው መታዘዝን እንደ መሰረታዊ ግዴታ አስቀምጦ፣ ነገር ግን አለመታዘዝን እንደ አንድ የተለየ ራሱን የቻለ የውል ማቋረጫ ምክንያት አለማስቀመጡ ያስገርማል። ይህንን ለውል ማቋረጫ ምክንያት አድርጎ በአንቀጽ 27 ላይ ያላስቀመጠው ለምን ይሆን? የሚል ጥያቄም ያስነሳል።
ሕግ አውጪው ይህንን ለውል ማቋረጫ ምክንያት አድርጎ በአንቀጽ 27 ላይ ያላስቀመጠው ይህንን ዓይነቱ ባህሪ ውል ማቋረጥን በሚያስከትልበት ደረጃ ላይ ካልደረሰ በስተቀር እንደ ማስጠንቀቂያ ወይም እገዳ ባሉ ተግሣጻዊ እርምጃዎች እንዲታለፍ አስቦ ይሆን?
ወይስ ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ባህሪ በሌሎቹ ድንጋጌዎች ለመሸፈን በቂ ነው፣ ወይንም በህብረት ስምምነት መፍታት አለበት የሚል አመለካከት ኖሮት?
ወይስ በሌላ ምክንያት?
ወይስ በአጻጻፍ ስህተት ተዘሎ ቀርቶ?
በአጠቃላይ፣ ይህ ጉዳይ ለወደፊቱ አዋጁ በሚከለስበት እና በሚሻሻልበት ጊዜ ውይይት ሊደረግበትና መፍትሔ ሊበጅለት የሚገባ ነው። እስከዚያው ድረስ ግን፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የአሰሪን ትዕዛዝ ካለማክበር ጋር በተያያዘ የሰጣቸውን ሁለት ውሳኔዎች (በቅጽ 18 ላይ እንደታተሙት) ከዚህ በታች አያይዤ አቅርቤያለሁ።
መልካም ንባብ! | 1 |
| 15 | 239903.pdf | 547 |
| 16 | በአንድ የወንጀል ድርጊት የተጣሰው የሕግ ድንጋጌ አንድ ሆኖ፣ ድርጊቱ በተለያዩ ሰዎች መብት ላይ ጉዳት ካደረሰ፣ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 60(ሐ) መሠረት ወንጀል አድራጊው በተደራራቢ ወንጀል ሊቀጣ እንደሚገባ ተደንግጓል።
ይሁንና ተከሳሹ በተደራራቢ ወንጀል ሊጠየቅ የሚገባው የወሰዳቸው ከብቶች የሁለትና ከዚያ በላይ ሰዎች ስለሆኑ ብቻ አይደለም። ይልቁንም፣ ተከሳሹ ከብቶቹ የተለያየ ሰዎች መሆናቸውን እያወቀ መውሰዱ ሲረጋገጥ ነው። ይህ ካልተረጋገጠ በቀር በተደራራቢ ወንጀል ሊቀጣ አይገባም። (በውንብድና ወንጀል የተሰጠ ውሳኔ)
ሰ/መ/ቁ. 239903 (ሐምሌ 27 ቀን 2014 ዓ.ም)
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/ | 559 |
| 17 | 249367.pdf | 697 |
| 18 | አውራሹ በሕይወት እያለ በስጦታ ንብረት የተቀበለ ወራሽ አውራሹ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ የዉርስ ሀብት ክፍፍል ላይ ለመሳተፍ የሚፈልግ ከሆነ አስቀድሞ በስጦታ የተቀበላቸዉን ንብረቶች መመለስ አለበት።
ነገር ግን ወራሹ አስቀድሞ በስጦታ የወሰደውን ንብረት ወደ ውርሱ ለመመለስ ፍቃደኛ ካልሆነ ከቀሪዉ የዉርስ ሀብት ክፍፍል ዉጭ ነው የሚሆነው።
የሰ/መ/ቁ.249367 (ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም)
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/ | 721 |
| 19 | ሰላም የቻናላችን ቤተሰቦች! ይህ ቻናል ጠቃሚ ሆኖ ካገኙት ለስራ ባልደረቦችዎ፣ ለወዳጅ ዘመድ እና ለጓደኞችዎ Copy Share Link በማድረግ ተደራሽነታችንን እንዲያሳድጉልን በአክብሮት እንጠይቃለን። ለድጋፍዎ እናመሰግናለን!
Jura Legal Update
ቴሌግራም ሊንክ: https://t.me/JuraLegalUpdate | 710 |
| 20 | 96548.pdf | 780 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
