Jura Legal Update
前往频道在 Telegram
Official Telegram Channel of Jura Legal Update. For comments, feedback, or inquiries, reach us at juralegalupdate@gmail.com. Or DM us directly in this telegram channel.
显示更多1 981
订阅者
+1824 小时
+3197 天
+46430 天
帖子存档
1 985
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ግብይት እንዲኖር መሠረት የጣለ የሕግ ማዕቀፍ ነው።
የአዋጁ ዋና ዋና ዓላማዎች፡ ኩባንያዎችና መንግሥት ለልማትና ለንግድ ማስፋፊያ የሚሆን የረጅም ጊዜ ገንዘብ ከአክሲዮንና ከቦንድ ሽያጭ ማግኘት እንዲችሉ ማድረግ፤ ግለሰቦችና ተቋማት በቁጠባ ያስቀመጡትን ገንዘብ በካፒታል ገበያ ላይ በማዋል ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ማመቻቸት እና የኢንቨስትመንት ስጋቶችን ለብዙ ባለሀብቶች በማካፈል የፋይናንስ ሥርዓቱን ማጠናከር ናቸው።
አዋጁ ገበያው በነፃነትና በፍትሐዊነት እንዲመራ የሚያደርጉ ቁልፍ ተቋማዊ መዋቅሮችን ገንብቷል። ከነዚህም መካከል የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን (ECMA) ገበያውን የሚቆጣጠር፣ ፈቃድ የሚሰጥና የኢንቨስተሮችን ከማጭበርበር የሚጠብቅና ገበያው ግልጽና ፍትሐዊ እንዲሆን የሚያደርግ ራሱን የቻለ ተቆጣጣሪ ተቋም ሆኖ ተቋቁሟል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ (ESX) የአክሲዮኖች፣ ቦንዶችና ሌሎች የፋይናንስ ሰነዶች ግብይት የሚካሄድበት ዘመናዊ መድረክ ሆኖ የተዘረጋ ሲሆን፣ በገበያው ላይ የሚነሱ ክርክሮችንና አቤቱታዎችን ፈጣንና ልዩ በሆነ መንገድ ለመዳኘት የሚያስችል የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም ተደርጓል።
የካፒታል ገበያ ስኬታማ የሚሆነው የኢንቨስተሮች እምነት ሲጠበቅ በመሆኑ፣ አዋጁ ለክትትልና ጥበቃ የሕግ ማዕቀፍ ፈጥሯል። በተጨማሪም ሰነደ ሙዓለ ንዋይ የሚያወጡ ኩባንያዎች ትክክለኛና ወቅታዊ የፋይናንስ መረጃዎቻቸውን ለሕዝብ ይፋ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ይደነግጋል።
የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 ሙሉ የPDF ሰነድ ከዚህ በታች ተያይዞ ያገኙታል። 👇
Jura Legal Update
1 985
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ግብይት እንዲኖር መሠረት የጣለ የሕግ ማዕቀፍ ነው።
የአዋጁ ዋና ዋና ዓላማዎች፡ ኩባንያዎችና መንግሥት ለልማትና ለንግድ ማስፋፊያ የሚሆን የረጅም ጊዜ ገንዘብ ከአክሲዮንና ከቦንድ ሽያጭ ማግኘት እንዲችሉ ማድረግ፤ ግለሰቦችና ተቋማት በቁጠባ ያስቀመጡትን ገንዘብ በካፒታል ገበያ ላይ በማዋል ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ማመቻቸት እና የኢንቨስትመንት ስጋቶችን ለብዙ ባለሀብቶች በማካፈል የፋይናንስ ሥርዓቱን ማጠናከር ናቸው።
አዋጁ ገበያው በነፃነትና በፍትሐዊነት እንዲመራ የሚያደርጉ ቁልፍ ተቋማዊ መዋቅሮችን ገንብቷል። ከነዚህም መካከል የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን (ECMA) ገበያውን የሚቆጣጠር፣ ፈቃድ የሚሰጥና የኢንቨስተሮችን ከማጭበርበር የሚጠብቅና ገበያው ግልጽና ፍትሐዊ እንዲሆን የሚያደርግ ራሱን የቻለ ተቆጣጣሪ ተቋም ሆኖ ተቋቁሟል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ (ESX) የአክሲዮኖች፣ ቦንዶችና ሌሎች የፋይናንስ ሰነዶች ግብይት የሚካሄድበት ዘመናዊ መድረክ ሆኖ የተዘረጋ ሲሆን፣ በገበያው ላይ የሚነሱ ክርክሮችንና አቤቱታዎችን ፈጣንና ልዩ በሆነ መንገድ ለመዳኘት የሚያስችል የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም ተደርጓል።
የካፒታል ገበያ ስኬታማ የሚሆነው የኢንቨስተሮች እምነት ሲጠበቅ በመሆኑ፣ አዋጁ ለክትትልና ጥበቃ የሕግ ማዕቀፍ ፈጥሯል። በተጨማሪም ሰነደ ሙዓለ ንዋይ የሚያወጡ ኩባንያዎች ትክክለኛና ወቅታዊ የፋይናንስ መረጃዎቻቸውን ለሕዝብ ይፋ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ይደነግጋል።
የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 ሙሉ የPDF ሰነድ ከዚህ በታች ተያይዞ ይገኛል። 👇
1 985
በነገራችን ላይ፣
ከሁለት ወይም ሶስት ቀናት በፊት ባስነበብኳችሁ የሰበሩ ውሳኔ ላይ እንደተመለከትነው፣ በትዳር ዘመን የተገኘ የደም ካሣ የጋራ ንብረት ነው ወይስ የግል? የሚለው ጭብጥ አከራካሪ ጉዳይ ነው። ይህ ጥያቄ የሕጉን ቀጥተኛ ቃላት ብቻ ሳይሆን የሕጉን መንፈስና የሕግ አውጪውን መሠረታዊ ሀሳብ መመርመርን ይጠይቃል። አንድ እናት በቀደመ ትዳሯ የወለደችው ልጇ በአደጋ ምክንያት ቢሞትባትና የተከፈላትን የካሣ ገንዘብ ለቤት መስሪያ ብታውለው፣ በኋላ ከሁለተኛ ባሏ ጋር በሚፋቱበት ጊዜ ይህ ንብረት እንደ ማንኛውም በትዳር ዘመን እንደተገኘ ገቢ ተቆጥሮ እኩል ሊከፈል ይገባል ወይስ አይገባም? የሚለው ጭብጥ ምርመራ የሚያስፈልገው ጉዳይ ነው።
በቀደመው ልጥፍ እንደገለጽነው፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 26953 (ቅጽ 5) በሰጠው ውሳኔ፣ መልስ ሰጪ (ሚስት) ቤቱ በልጅ ሞት ምክንያት በተሰጠ የደም ካሣ የተሰራ በመሆኑ የግል ሀብቴ ሆኖ ይቀጥላል ማለቷን ጠቅሶ፣ ነገር ግን አባባሏን የሚደግፍ በቂ የሕግ ክርክር አላቀረበችም በሚል አቋም ይዟል። ችሎቱ የካሣ ክፍያው ምክንያት ምንም ይሁን ምን ክፍያ ማግኘቷንና በእርሱም ቤቱ መሰራቱን ስላልካደች፣ ክፍያው በትዳር ውስጥ እያሉ የተገኘ ገቢ በመሆኑ የጋራ ንብረት ነው በሚል ድምዳሜ ላይ ደርሷል።
ሆኖም ይህ ዓይነቱ ሜካኒካዊ የሕግ አተገባበር የቤተሰብ ሕጉን መሠረታዊ ፍልስፍና እና የካሣ ሕግን ተፈጥሮ ያገናዘበ አይደለም። በተሻሻለው የፌዴራል የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 62 ስር በትዳር ዘመን የተገኘ ንብረት ወይም ገቢ የጋራ እንደሚሆን የተደነገገ ሲሆን፣ በአንቀጽ 63 ስር ደግሞ አንደኛው ተጋቢ የግል ሀብቱ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር ማንኛውም ንብረት የጋራ እንደሆነ የሚወሰድ የሕግ ግምት ተቀምጧል። በአንቀጽ 62 ንዑስ አንቀጽ 1 ላይ ባልና ሚስት ከግል ጥረታቸውና ከንብረታቸው የሚያገኟቸው ገቢዎች ሁሉ የጋራ ሀብቶቻቸው እንደሚሆኑ ይደነግጋል።
ነገር ግን የደም ካሣ በሥራ፣ በጥረት ወይም በንግድ እንቅስቃሴ የተገኘ የኢኮኖሚ ጥቅም አይደለም። የደም ካሣ በባህሪው ለደረሰ ሀዘን፣ ጉዳትና ስብራት የሚሰጥ ማጽናኛ ነው። ክፍያው የተጎዳውን ወይም ሀዘን የደረሰበትን ወገን ለማካካስ የሚሰጥ እንጂ ከግል ወይም ከጋራ ጥረት የተገኘ ገቢ ሊሆን አይችልም። በስጦታ ወይም በውርስ የተገኘ ንብረት በቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 57 ስር የግል ሀብት እንዲሆን የተደረገበት ምክንያት ከግል ወይም የጋራ ጥረት ውጪ የተገኘ በመሆኑ ከሆነ፣ በሰው ሕይወት ማለፍ ምክንያት የሚገኝ የጉዳት ካሣና ማጽናኛማ ከስጦታና ከውርስ በበለጠ ሁኔታ ከግለሰቡ ጋር በጥብቅ የተያያዘ የግል ሀብት ሊሆን ይገባ ነበር።
ዶክተር መሐሪ ረዳኢ "የፌደራል የቤተሰብ ሕግ፡ ይዘት እና አተገባበር" (2012 ዓ.ም፣ ገጽ 88-89) በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ የሰበር ሰሚ ችሎቱን ውሳኔ ሲተቹ፣ የጉዳት ካሣ እንደ መደበኛ ገቢ ተቆጥሮ የጋራ ሀብት የሚሆንበት አሰራር አሳማኝ አለመሆኑን ይሞግታሉ። የጉዳት ካሣ የሥራና የጥረት ውጤት ተደርጎ የሚወሰድ ገቢ ሳይሆን፣ ለደረሰ መራራ ሀዘን ማካካሻ ተብሎ የሚሰጥ ማጽናኛ በመሆኑ፣ በግብር ሕግም ሆነ በአሠሪና ሠራተኛ ሕግ ስር ገቢ ተብሎ ግብር እንደማይከፈልበት ሁሉ በቤተሰብ ሕግም በተመሳሳይ ዕይታ ሊቃኝ እንደሚገባ ያመላክታሉ። እናት በሞተ ልጅ ሕመም ያገኘችውን ማጽናኛ ከተለየችው ባሏ ጋር እንድትካፈልና በእርሱ የተገዛን ንብረት እንድታጣ ማድረግ ሁለተኛ ሞትና ልጃቸውን የሚያስታውሱበትን ምልክት ማጣት እንደሆነ በመግለጽ፣ የሰበር ሰሚ ችሎቱ አቋም ከሕግ አውጪው መንፈስ ጋር የሚጣጣም እንዳልሆነ ይሞግታሉ።
በሌሎች ሀገራት የቤተሰብ ሕግ ተሞክሮም፣ ለምሳሌ በፖላንድ ሕግ፣ በአካልና በስነ-ልቦና ላይ ለሚደርስ ጉዳት የሚከፈል የሞራል ካሣ በግልጽ የተጎጂው የግል ሀብት ተደርጎ ይወሰዳል።
ሲጠቃለል፣ በትዳር ዘመን የተገኘ የደም ካሣም ሆነ በእርሱ የተገዛ ንብረት፣ ከባልና ሚስት የግል ወይም የጋራ ጥረት የተገኘባለመሆኑ እና ሙሉ በሙሉ ግላዊ ባህሪ ያለው በመሆኑ፣ የእንደዚህ ዓይነቱ ጉዳት ሰለባ የሆነው ተጋቢ የግል ሀብት እንጂ የጋራ ንብረት ሊሆን አይገባም። በመሆኑም ወደፊት ሕግ አውጪው ሕጉን ሲያሻሻል እንዲህ አይነት ልዩ ሁኔታዎች (exceptions) በግልጽ ሊደነግግ ይገባል። እስከዚያው ድረስ ግን፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የካሣን መሠረታዊ ባህሪ፣ የሕጉን መንፈስ እና የሕግ አውጪውን ዓላማ ባገናዘበ መልኩ ቀደሞ የሰጠውን የሕግ ትርጉም በድጋሚ ሊመረምረውና ሊያርመው የተገባ ነው።
መልካም አዳር!
Jura Legal Update
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
1 985
የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ | የፍትሕ ሚኒስቴር
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ለዐቃቤ ሕግ (ደረጃ 3) መደብ አዳዲስ ተመራቂዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
ትምህርት ደረጃ: የሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ (LL.B)
የተመረቁበት ዓመት: 2018 ዓ.ም
CGPA: 3.6 እና ከዚያ በላይ
Exit Exam: 85 ፐርሰንታይል እና ከዚያ በላይ
ልምድ: 0 ዓመት (አዲስ ተመራቂ)
ብዛት: 25
የምዝገባ ጊዜ: ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ30 ተከታታይ ቀናት።
የምዝገባ ሊንክ: https://forms.gle/N4UezidkwqFUrSdz9
ማስታወሻ: ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን ከተቋሙ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ማግኘት ይችላሉ።
1 985
#ጥቆማ
የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT Exam) የምዝገባ ጥሪ
የ2018 ዓ.ም የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (National Graduate Admission Test - NGAT) የምዝገባ ጊዜ ይፋ ተደርጓል።
የምዝገባ ጊዜ፡ ከሐምሌ 15 እስከ ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም ብቻ
የመመዝገቢያ ሊንክ፡ https://ngat.ethernet.edu.et
የአገልግሎት ክፍያ፡ 750 ብር (በTelebirr የሚከፈል)
ቅድመ ሁኔታ፡ የፋይዳ (Digital ID) መታወቂያ አስቀድሞ ማዘጋጀት አስፈላጊ ነው።
የፈተና ቦታ፡ በሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጥ ሲሆን፤ የተወሰነው የፈተና ጣቢያ ከምዝገባ በኋላ እንደ ተመዝጋቢዎች ቁጥር የሚገለፅ ይሆናል።
የፈተናው መስጫ ጊዜ ወደፊት የሚገለፅ ሲሆን አመልካቾች አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ ተብሏል።
1 985
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁ. 246230 መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት በሰጠው ውሳኔ ቀደም ሲል በሰ/መ/ቁ.186946 እና መሰል መዝገቦች ላይ ተሰጥቶ የነበረውን አስገዳጅ የሕግ ትርጉም በመለወጥ አዲስ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል።
በዚህም መሠረት፣ በአንድ ባለይዞታ ሊመዘገብ የሚገባው የከተማ ይዞታ ላይ ከአንድ በላይ የሆነ የይዞታ ማረጋገጫ ወይም ካርታ ለተለያዩ ሰዎች ተሰጥቶ ሲገኝ፣ ለቦታው ባለመብትነት ቅድሚያ የሚሰጠው መጀመሪያ ላስመዘገበው ሰው ነው በማለት ወስኗል።
ሙሉ ውሳኔውን ከተያያዘው ፋይል ማግኘት ይችላሉ። 👇
1 985
ሕጉን መፈለግና መተርጎም የፍርድ ቤት እንጂ የባለጉዳዩ ኃላፊነት አይደለም (Jura Novit Curia)
Written by Jura Legal Update
በሥነ-ሥርዓት ሕግ ውስጥ የክርክር ሂደቶችን ውጤታማና ፍትሐዊ የሚያደርገው ዋናው መሠረት በፍርድ ቤቱ እና በተከራካሪ ወገኖች መካከል ያለው ግልጽ የሥራ ክፍፍል ነው። አንዳንድ ጊዜ በክርክር ወቅት ተከራካሪ ወገኖች ያቀረቡትን አቤቱታ ወይም መከራከሪያ የሚደግፍ ሕግ አልጠቀሱም ወይም የተሳሳተ የሕግ ድንጋጌ አቅርበዋል በሚል ምክንያቶች የክርክሩ ይዘት በአግባቡ ሳይመረመር ውድቅ ሲደረግ ይስተዋላል።
ሆኖም ግን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው የሚሠራበትና በሕግ ሥርዓታችን ውስጥም መሠረት ያለው "ፍርድ ቤቱ ሕጉን ያውቃል" (Jura Novit Curia) የሚለው መርህ ይኸንን አሰራር በጽኑ ይሞግታል። በዚህ መርህ መሠረት፣ ባለጉዳዮች ለፍርድ ቤቱ የማቅረብ ግዴታ ያለባቸው ፍሬ-ነገር (Facts) እና ማስረጃዎችን ብቻ ሲሆን፣ አግባብነት ያለው ሕግ መኖሩን መፈለግ፣ መተርጎም እና መተግበር ግን የፍርድ ቤቱ የራሱ ኃላፊነት ነው።
የፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ቁጥር 222 (1) ከሀ እስከ ቀ ባሉት ንዑሳን አንቀጾች በክስ አቤቱታ ላይ መካተት ያለባቸውን ዝርዝር ነገሮች ይደነግጋል። ከነዚህም መካከል የፍርድ ቤቱ ሥልጣን፣ የከሳሽና የተከሳሽ ማንነትና አድራሻ፣ የክሱ ምክንያት የሆኑት ነገሮችና የተፈጠሩበት ጊዜና ቦታ (የፍሬ-ነገር ዝርዝር)፣ እንዲሁም ለክሱ ምክንያት በሆነው ነገር ውስጥ የተከሳሽ አግባብነት ይገኙበታል።
በዚህ የሕግ አንቀጽ ውስጥ ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው ነጥብ ከሳሽ ክሱን በሚያቀርብበት ጊዜ ክሱን የሚደግፍ የሕግ አንቀጽ ወይም የሕግ መከራከሪያ የማቅረብ ግዴታ እንዳልተጣለበት ነው። ሕጉ ባለጉዳዩ የክርክሩን መሠረት ወይም ፍሬ-ነገር (Facts) ብቻ እንዲያቀርብ ያስገድዳል፤ እንጂ አግባብነት ያለውን ሕግ ጠቅሶ እንዲከራከር አይጠይቅም። ይህ ድንጋጌ የJura Novit Curia (ፍርድ ቤቱ ሕጉን ያውቃል) መርህ ቀጥተኛ መገለጫ ነው። ባለጉዳዩ ፍሬ-ነገሩን የማቅረብ ኃላፊነት እንዳለበት ሁሉ፣ በቁጥር 222 መሠረት የቀረበውን ፍሬ-ነገር አይቶ አግባብነት ያለውን ሕግ ፈልጎ የማዛመድ እና የመተግበር ድርሻ የፍርድ ቤቱ ብቻ ነው።
ይህ መርህ በከሳሽ ላይ ብቻ ሳይሆን በተከሳሽ የመከላከያ መልስ ላይም በተመሳሳይ ደረጃ ይተገበራል። በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ቁጥር 234 (1) መሠረት፣ ተከሳሽ በመከላከል መልሱ ውስጥ ሊያካተታቸው የሚገቡት የክሱን ፍሬ-ነገሮች ማስተባበያ፣ የመቃወሚያ መሠረቶችን (ለምሳሌ የዕርቅ፣ የይርጋ ወይም የችሎት ማጣት መከራከሪያዎችን) እና ለመከላከያው መሠረት የሆኑትን የፍሬ-ነገር ዝርዝሮች እንጂ መከላከያውን የሚደግፉ የሕግ አንቀጾችን መጥቀስ ግዴታ አይደለም።
ተከሳሹ የቀረበበትን ክስ የሚከላከልበትን ፍሬ-ነገር እና ማስረጃ ማቅረብ እንጂ፣ የመከላከያ መከራከሪያውን የሚደግፍ የሕግ አንቀፅ የመጥቀስ ግዴታ የለበትም። ተከሳሹ የሕግ ድንጋጌዎችን ባይጠቅስ እንኳ፣ ባቀረበው የመከላከል ፍሬ-ነገር መሠረት አግባብነት ያለውና ተከሳሹን ሊታደግ የሚችል ሕግ የመፈለግ፣ የመተርጎም እና የመተግበር ኃላፊነቱ አሁንም የፍርድ ቤቱ የራሱ ነው። ተከሳሽ "መከላከያውን የሚደግፍ የሕግ አንቀጽ አልጠቀሰም" በሚል ብቻ መከላከያው ውድቅ ሊደረግበት አይገባም።
ከዚህም በላይ፣ የፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 3/1987 አንቀጽ 2 ንዑስ ቁጥር 3 በግልጽ እንደሚያስቀምጠው "ማንኛውም የፌዴራል ወይም የክልል ሕግ አውጪ፣ አስፈጻሚ እና ተርጓሚ እንዲሁም ማንኛውም የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ የወጣውን ሕግ የመቀበል ግዴታ አለበት" ይላል። የእንግሊዝኛው ትርጉም ደግሞ በግልጽ "shall take judicial notice of Laws published in the Federal Negarit Gazeta" በማለት ይገልጸዋል።
ይህ ድንጋጌ በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው የወጡ ሕጎች በሙሉ በሕግ ተርጓሚው አካል (በፍርድ ቤቱ) ዘንድ አስቀድመው እንደሚታወቁ (Judicial Notice) ይገመታል። በመሆኑም ተከራካሪ ወገኖች በነጋሪት ጋዜጣ የታወጀን ሕግ በማስረጃነት ማቅረብ ወይም "ሕጉ አለ" ብለው ማስረዳት አይጠበቅባቸውም። ፍርድ ቤቱ በራሱ ተነሳሽነት በነጋሪት ጋዜጣ የወጡትን ሕጎች አውቆና ተረድቶ በክርክሩ ላይ የመተግበር ግዴታ አለበት።
ሲጠቃለል፣ የፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ቁጥር 222 እና 234 ተከራካሪ ወገኖች ፍሬ-ነገሩን እና ማስረጃ ብቻ የማቅረብ ኃላፊነት እንዳለባቸው ሲደነግጉ፣ የአዋጅ ቁጥር 3/1987 አንቀጽ 2 (3) ደግሞ ፍርድ ቤቱ በነጋሪት ጋዜጣ የወጡ ሕጎችን በJudicial Notice ደረጃ አውቆ የመተግበር ግዴታ እንዳለበት ያረጋግጣል። እነዚህ ድንጋጌዎች ተጣጥመው ሲተገበሩ ተከራካሪ ወገኖች "የሕግ አንቀጽ አልጠቀሱም" ወይም "ክርክሩን የሚደግፍ ሕግ አላቀረበም" በሚል ምክንያት አቤቱታን ወይም ክርክርን ውድቅ ማድረግ ሕጋዊ መሠረት የሌለው እና የሕጉን ዓላማ የሚቃረን መሆኑን በግልጽ ያሳያሉ።
መልካም ምሽት!
Jura Legal Update
ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
1 985
በትዳር ዘመን የተገኘ "የደም ካሣ" የጋራ ንብረት ነው ወይስ የግል? አንድ እናት በቀደመ ትዳሯ የወለደችው ልጇ በአደጋ ምክንያት ቢሞትባትና የካሣ ገንዘብ ብታገኝ፣ በኋላ ከሁለተኛ ባሏ ጋር በሚፋቱበት ጊዜ ይህ የካሣ ገንዘብ ወይም በእርሱ የተሰራ ቤት እንደ ማንኛውም በትዳር ዘመን እንደተገኘ ገቢ ተቆጥሮ ለሁለቱም እኩል መከፈል አለበት ወይስ የለበትም?
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 26953 (ቅጽ 5) በሰጠው ውሳኔ፣ መልስ ሰጪ (ሚስት) ቤቱ በልጅ ሞት ምክንያት በተሰጠ የደም ካሣ የተሰራ በመሆኑ የግል ሀብቴ ሆኖ ይቀጥላል አለች እንጂ አባባሏን የሚደግፍ የሕግ ክርክር አላቀረበችም፤ የካሣ ክፍያው ምክንያት ምንም ይሁን ምን የካሣ ክፍያ ማግኘቷንና በእርሱም ቤቱ መሰራቱን ስላላካደች፣ የካሳ ክፍያ ደግሞ ገቢ በመሆኑና በትዳር ውስጥ እያሉ የተገኘ ገቢ በመሆኑ የጋራ ንብረት ነው ሲል ድምዳሜ ላይ ደርሷል።
ከዚህ ውሳኔ መገንዘብ የሚቻለው በትዳር ዘመን የሚገኝ ማናቸውም ገቢ ወይም ንብረት በሕጉ ግምት የጋራ እንደሚሆን ነው። የደም ካሣው የተገኘው በትዳር ዘመን እስከሆነ ድረስ እንደ ገቢ የሚቆጠር በመሆኑ፣ የጋራ አለመሆኑን የሚያስረዳ የሕግ ክርክር እስካልቀረበ ድረስ ንብረቱ የጋራ ይሆናል።
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሚሰጠው የሕግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ በሚገኙ የበታች ፍርድ ቤቶች ላይ አስገዳጅነት ያለው በመሆኑ፣ ይህ ውሳኔ ተመሳሳይ ጭብጥ ላላቸው ጉዳዮች አስገዳጅነት ያለው ነው።
Jura Legal Update
1 985
የፍርድ ቤቶች ዓመታዊ የዕረፍት ጊዜ
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 በአንቀጽ 38 ላይ እንደተደነገገው፤ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች (ጠቅላይ፣ ከፍተኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ) በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 በከፊል ዝግ ሆነው ይቆያሉ።
ይህ የዕረፍት ጊዜ እየቀረበ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ፣ ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ በሚሆኑበት ወቅት የዳኝነት አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ እንደማይቋረጥ እና የትኞቹ ጉዳዮች እንደሚስተናገዱ ማወቅ አስፈላጊ ነው።
ፍርድ ቤቶች የዜጎችን መብትና ጥቅም የሚያስክብሩ ተቋማት በመሆናቸው፣ ሙሉ በሙሉ ዝግ አይሆኑም። ይልቁንም አጣዳፊ ምላሽ የሚሹ ጉዳዮችን ለማስተናገድ በተረኛ ችሎቶች በከፊል ክፍት ሆነው አገልግሎት ይሰጣሉ።
የክልል ፍርድ ቤቶችም በየራሳቸው ሕጎች በተደነገገው መሠረት የዕረፍት ጊዜያት የሚኖራቸው ሲሆን፣ በዚህም ወቅት አጣዳፊ ጉዳዮችን በተረኛ ችሎት በማስተናገድ በከፊል ዝግ ሆነው እንደደሚቆዩ ይታወቃል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያስተላለፈው ማስታወቂያ ከዚህ ጋር ተያይዟል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከሐምሌ 21/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም ድረስ በክረምት እረፍት ምክንያት መደበኛ የመዝገብ ሥራ ዝግ ይሆናል።
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ሆነ የሌሎች ክልል ፍርድ ቤቶች በኩል የዓመቱን የዕረፍት ጊዜ ዝርዝር አፈፃፀም አስመልካቶ ይፋዊ መግለጫ በቅርቡ እንደሚያወጡ ይጠበቃል።
Jura Legal Update
1 985
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት (1923 ዓ.ም)
ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ የተጻፈ ሕገ መንግሥት ያጸደቁት በሐምሌ 9 ቀን 1923 ዓ.ም ነበር፡፡
በንጉሡ ቀጥተኛ ትእዛዝ ረቂቁ በደጃዝማች ተክለሐዋርያት ተክለማርያም ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን ከሚኒስትሮችና ከክፍለ ሀገር መኳንንቶች የተውጣጣ 11 አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቁሞ ተወያይቶበታል።
ኮሚቴው የእንግሊዝና የጃፓን ሕገ መንግሥቶች ተተርጉመው ቀርበውለት ተወያይቶበት እና በቀጥታ ወደ ንጉሡ ተልኮ ነው የጸደቀው።
ንጉሡ ከብላቴን ጌታ ሕሩይ ወልደሥላሴና ከራስ ካሳ ኃይሉ ጋር እንደመከሩበት የሚነገረውን ይህን ሕገ መንግሥት ያጸደቁ ሲሆን፣ ሰነዱ የሕግ መወሰኛ እና የሕግ መምሪያ የተባሉ ሁለት ምክር ቤቶችንም አቋቁሟል።
በሐምሌ 9 ቀን 1923 ዓ.ም ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ የጸደቀው የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዘመናዊ የተጻፈ ሕገ መንግሥት ሙሉ የPDF ሰነድ ከዚህ በታች ተያይዞ ይገኛል። 👇
1 985
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ (Rent Control and Administration Proclamation)
በአዲስ አበባ ከተማ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ ከጀመረው የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት ጋር ተያይዞ በመነሳት ላይ ያለው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ፤
ይህ አዋጅ ተፈፃሚ የሚሆነው ተጠሪነታቸው ለክልል በሆኑ ከተሞች፣ በአዲስ አበባ እና በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ላይ በሚፈፀም የመኖሪያ ቤት ኪራይ ላይ ሲሆን ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ አዋጁ በሌሎች ከተሞች ላይ ተፈፃሚ ሊሆን ስለሚችልበት ሁኔታ ክልሎች ነባራዊ ሁኔታውን እያዩ እንደሚወስኑ አዋጁ ያስቀምጣል። በተጨማሪም አዋጁ ተፈፃሚ ከሚሆንበት ሁኔታ ውጪ ተፈፃሚ የማይሆንበት ሁኔታ ተመለከቷል።
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል የኪራይ ዘመኑ ሳይጠናቀቅ በአከራዩና ተከራዩ ስምምነት፣ ተከራይ ቤቱን መልቀቅ ሲፈልግ የሁለት ወር የቅድሚያ ማስታወቂያ በመስጠት ወይም የቤት ባለቤትነት በሕጋዊ መንገድ ለሌላ ሰው ሲተላለፍ የ6 ወር ማስጠንቀቂያ በመስጠት ሊቋረጥ ይችላል። እነኚህ ውሉ በማስጠንቀቂያ የሚቋረጥባቸው ምክንያቶች ሲሆኑ ውሉ ያለማስጠንቀቂያ የሚቋረጥባቸው ሁኔታዎች ደግሞ በአንቀጽ 16 ስር ተዘርዝረው ይገኛሉ።
አዋጁ በPDF ከዚህ በታች ተያይዞ ይገኛል። 👇
1 985
ብታውቁት መልካም ነው! 👇
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 249171 (ጥቅምት 05 ቀን 2017 ዓ.ም) በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም፣ በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1179 መሠረት ባለይዞታው ሳይቃወም በይዞታው ላይ ቤት የሠራ ሰው የሕንፃው ባለቤት ቢሆንም፣ ይህ መብት የመሬቱን ባለይዞታነት ስለማያካትት የመሬቱ ባለይዞታ ለቤቱ ተገቢውን ግምት በመክፈል ቤቱን አስለቅቆ የመረከብ መብት እንዳለው ወስኗል።
በተጨማሪም ችሎቱ በዚህ ውሳኔው "ግምት" የሚለው ቃል የቤቱን የግንባታ ዋጋ እንጂ የገበያ ዋጋን እንደማያመለክት አብራርቷል። የገበያ ዋጋ ማለት ቤቱ ለሽያጭ ቢቀርብ ሊያወጣ የሚችለው ዋጋ ሲሆን፤ የግንባታ ዋጋ ግን ቤቱን ለመገንባት የወጣውን ትክክለኛ ወጪ የሚመለከት ነው።
ሙሉ ውሳኔው በPDF 👇
