Jura Legal Update
الذهاب إلى القناة على Telegram
Official Telegram Channel of Jura Legal Update. For comments, feedback, or inquiries, reach us at juralegalupdate@gmail.com. Or DM us directly in this telegram channel.
إظهار المزيد2 051
المشتركون
+2524 ساعات
+1667 أيام
+50930 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يوليو '26
يوليو '26
+560
في 2 قنوات
يونيو '26
+210
في 1 قنوات
Get PRO
مايو '26
+530
في 3 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+247
في 2 قنوات
Get PRO
مارس '26
+650
في 2 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 31 يوليو | +19 | |||
| 30 يوليو | +26 | |||
| 29 يوليو | +14 | |||
| 28 يوليو | +4 | |||
| 27 يوليو | +16 | |||
| 26 يوليو | +21 | |||
| 25 يوليو | +53 | |||
| 24 يوليو | +40 | |||
| 23 يوليو | +21 | |||
| 22 يوليو | +121 | |||
| 21 يوليو | +39 | |||
| 20 يوليو | +30 | |||
| 19 يوليو | +34 | |||
| 18 يوليو | +5 | |||
| 17 يوليو | +3 | |||
| 16 يوليو | +6 | |||
| 15 يوليو | +10 | |||
| 14 يوليو | +2 | |||
| 13 يوليو | +7 | |||
| 12 يوليو | +8 | |||
| 11 يوليو | +3 | |||
| 10 يوليو | +9 | |||
| 09 يوليو | +7 | |||
| 08 يوليو | +14 | |||
| 07 يوليو | +3 | |||
| 06 يوليو | +7 | |||
| 05 يوليو | +12 | |||
| 04 يوليو | +10 | |||
| 03 يوليو | +13 | |||
| 02 يوليو | +1 | |||
| 01 يوليو | +2 |
منشورات القناة
| 2 | የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሕገ መንግሥት የመተርጎም ሥልጣን
ሕገ መንግሥት መተርጎም ማለት የሕገ መንግሥቱ ድንጋጌዎች አሻሚ ሲሆኑ፣ ወይም ሌሎች ሕጎች፣ አሠራሮችና የመንግሥት ውሳኔዎች ከሕገ መንግሥቱ ጋር ሲቃረኑ የሕገ መንግሥቱን መሠረታዊ ዓላማ፣ መንፈስና መርሆዎች መሠረት በማድረግ ሕጋዊ ፍቺ መስጠትና መወሰን ማለት እንደሆነ መግለጽ ይቻላል።
በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 62 ንዑስ አንቀጽ 1 ድንጋጌ መሠረት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሕገ መንግሥቱን የመተርጎም ሥልጣን ተሰጥቶታል። በተጨማሪም በአንቀጽ 62 ንዑስ አንቀጽ 2 መሠረት የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤን የማደራጀት ኃላፊነት ተጥሎበታል፤ በዛው አግባብ ተደራጅቷል።
ሕገ መንግሥቱን የመተርጎም ሥልጣን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት መሰጠቱ በሕግ ባለሙያዎችና ከሌሎችም ዘንድ ሰፊ ክርክር የሚነሳበት ጉዳይ ነው። አብዛኞቹ የዓለም ሀገራት ይህን ሥልጣን ለነፃ የዳኝነት አካል (ለሕገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ወይም ለጠቅላይ ፍርድ ቤት) የሚሰጡ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ግን የብሔር ብሔረሰቦች ውክልና ያለው የፖለቲካ አካል እንዲተርጉመው መደረጉ የዳኝነት ነፃነትን እና የሕግ የበላይነትን ይጎዳል በሚል ትችትና ክርክር ይነሳበታል።
በሌላ በኩል ስልጣኑ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት መሰጠቱን የሚደግፉ ወገኖች እንደሚሉት፤ የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት "የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የውል ስምምነት (Political Covenant)" ውጤት ነው። የሕገ መንግሥቱ ባለቤቶችና የሉዓላዊ ሥልጣን ባለቤቶች ደግሞ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በመሆናቸው፣ የእነርሱ ውክልና ያለበት አካል (የፌዴሬሽን ምክር ቤት) የውላቸው መጠበቂያ የሆነውን ሕገ መንግሥት እንዲተርጉም መደረጉ አግባብነት አለው፤ ሙያዊና የሕግ ድጋፉንም የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ያቀርብለታል በማለት ይከራከራሉ።
ያም ሆነ ይህ፣ በጉዳዩ ላይ የተለያዩ የፖለቲካና የሕግ ክርክሮች ቢኖሩም፤ በሥራ ላይ ያለው ሕገ መንግሥት እስካልተሻሻለ ድረስ ሕገ መንግሥቱን የመተርጎምና የመጨረሻ ውሳኔ የመስጠት ሕጋዊ ሥልጣን የዚሁ አካል (የፌዴሬሽን ምክር ቤት) ብቻ ነው።
የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሥልጣንና ተግባር ለመዘርዝር የወጣ አዋጅ ቁጥር 1261/2013 እንደሚያመላክተው ምክር ቤቱ በትርጉም ሂደቱ ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሠራር፣ የመንግሥት አካል ወይም የባለሥልጣን ውሳኔ ከሕገ መንግሥቱ ጋር የሚቃረን ሆኖ ሲያገኘው ተፈጻሚ እንዳይሆን ይወስናል። ሆኖም ምክር ቤቱ በሕገ መንግሥት ትርጉም ላይ የአማካሪነት አገልግሎት የመስጠት ግዴታ የለበትም።
የሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄ ሊቀርብ የሚችለው በሕገ መንግሥቱ ውስጥ ለመንግሥት አካላት ወይም ሌሎች ተቋማት በተሰጡ ሥልጣንና ተግባራት ይዘትና ዳራ ላይ ጥያቄ ሲነሳ ነው። በተጨማሪም በፌዴራል ወይም በክልል ሕግ አውጪዎች የወጡ ሕጎች ከሕገ መንግሥቱ ጋር ይቃረናሉ የሚል ጥያቄ በፍርድ ቤት ወይም በባለጉዳይ ሲቀርብ፣ ወይም ማንኛውም ሰው መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ መብቶቼና ነፃነቶቼ በመንግሥት አካል ወይም ባለሥልጣን የመጨረሻ ውሳኔ ተጥሰዋል ብሎ አቤቱታ ሲያቀርብ አበቱታው ይስተናገዳል። በፌዴራል የመንግሥት አካላት መካከል፣ በፌዴራልና ክልሎች ወይም በክልሎች መካከል አለመግባባቶች ሲፈጠሩ፣ በፍርድ ቤት ሊወሰኑ የማይችሉ (non-justiciable) ሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮች ላይ በሕግ አውጪው ወይም አስፈጻሚው አካል 1/3ኛ አባላት ጥያቄ ሲቀርብ፣ የክልል ሕገ መንግሥት ተርጓሚ አካል በምክር ቤቱ ቀደም ሲል ውሳኔ በተሰጠበት ተመሳሳይ ጉዳይ ላይ ልዩ ልዩ ትርጉም ሲሰጥ፣ እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ ሕገ መንግሥታዊ የትርጉም ጥያቄዎችን ጨምሮ አግባብነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ አቤቱታ ማቅረብ ይቻላል።
የሕግ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ሕገ መንግሥቱን መተርጎም ያስፈልጋል ብሎ የሚያቀርበውን የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ምክር ቤቱ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል። አጣሪ ጉባኤው "ትርጉም አያስፈልግም" ብሎ የሰጠውን ውሳኔ ቅር የተሰኘ ወገን ይግባኙን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ማቅረብ ይችላል። በአጣሪ ጉባኤ ውሳኔ ቅር የተሰኘ ወገን ይግባኙን ውሳኔው በተሰጠ በ 180 የሥራ ቀናት ውስጥ ማቅረብ አለበት። ሆኖም በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 28 የተጠቀሱት በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች፣ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብቶች እና የሥልጣን ክፍፍል ጉዳዮች በይርጋ አይታገዱም።
አመልካቹ ባለጉዳዩ ወይም ሕጋዊ ወኪሉ፣ የሚመለከተው ፍርድ ቤት/የመንግሥት አካል፣ የወካይ ማህበር ወይም የቡድን አባል፣ ወይም ሕጋዊ ጥቅም ያለው ማንኛውም ሰው ሊሆን ይችላል። የሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄ ማቅረብ ከክፍያ ነፃ ነው፤ ሆኖም እንደ አስፈላጊነቱ በምክር ቤቱ ደንብ መሠረት ክፍያ እንዲፈጸም ሊደረግ ይችላል።
በሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄ ላይ በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ አስገዳጅ ነው። ውሳኔው ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ ተፈጻሚ የሚሆን ሲሆን ሕገ መንግሥታዊ ያልሆነ የተባለ ሕግ ወይም ውሳኔ ለሚመለከተው አካል በ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ ይደርሳል። ሕጉ ሕገ መንግሥታዊ አይደለም ከተባለ፣ ሕጉን ያወጣው አካል በ 3 ወር ውስጥ ሕጉን ማሻሻል፣ መለወጥ ወይም መሰረዝ አለበት። የሕግ አካል ሕገ መንግሥታዊ አይደለም ከተባለ፣ ውጤቱ በዚያው በተወሰነው ድንጋጌ ላይ ብቻ የተወሰነ ይሆናል።
ሙሉውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሥልጣንና ተግባር ለመዘርዝር የወጣ አዋጅ ቁጥር 1261/2013 በፒዲኤፍ (PDF) ከዚህ በታች ተያይዞ ያገኙታል።
መልካም ቀን!
Jura Legal Update
ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ | 335 |
| 3 | لا يوجد نص... | 1 |
| 4 | 175142.pdf | 434 |
| 5 | በኤሌክትሪክ አደጋ ምክንያት ለሚደርስ ጉዳት ተገልጋዮች ከአገልግሎት ሰጪው እውቅና እና ፈቃድ ውጭ በራሳቸው በሚዘረጉት የኤሌክትሪክ መስመር ለሚደርሰው ጉዳት አገልግሎት ሰጪው ተቋም ተጠያቂ አይሆንም።
እንደ ኤሌክትሪክ አደጋ ባሉ የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ የአደጋውን መንስኤ ለማወቅ በፖሊስ የሚደረግ የባለሙያ (Forensic) ምርመራ ከፍተኛ የማስረጃነት ዋጋ (High Probative Value) አለው። ይህንን የባለሙያ ምርመራ ውጤት ያለ በቂ ምክንያት ወደ ጎን በማለት ውሳኔ መስጠት መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው።
አገልግሎት ሰጪው ኃላፊነት የሚኖርበት እሱ ራሱ በዘረጋውና ባለቤት በሆነበት መስመር ላይ ለሚደርስ ጉዳት ብቻ ነው። በተገልጋዮች ጥፋት ለሚደርስ አደጋ ተቋሙ ካሣ የመክፈል ግዴታ የለበትም።
የኤሌክትሪክ ኃይል ባለቤት መሆን ብቻውን ኃላፊነትን አያስከትልም፤ ኃላፊነት ሊኖር የሚችለው ተገቢው ጥንቃቄ ካልተደረገ እና ጥፋት ከተፈጸመ ብቻ ነው።
ሰ/መ/ቁ.175142 (ግንቦት 24 ቀን 2012 ዓ.ም)
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/ | 446 |
| 6 | +1 የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ 2018 I.pdf | 598 |
| 7 | የፌዴሬሽን ምክር ቤት በ2018 ዓ.ም በሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄዎች ላይ ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች አጠቃሎ የያዘውን ፋይል ከዚህ በታች በPDF አያይዘናል። 👇 | 541 |
| 8 | HoF (151).pdf | 608 |
| 9 | በወንጀል የተከሰሰ ማንኛውም ሰው ድርጊቱን ስለመፈጸሙ በዐቃቤ ሕግ በኩል "ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በላይ" (beyond reasonable doubt) ካልተረጋገጠ በቀር ጥፋተኛ ተብሎ የቅጣት ውሳኔ ሊሰጥበት የማይገባ መሆኑን እና ይህ ሳይረጋገጥ የሚሰጥ የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔ ሕገ-መንግሥታዊ እንዳልሆነ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 20 (3) ሥር ከተረጋገጠው "ንጹህ ሆኖ የመገመት መብት" አንጻር የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስገዳጅ የሕገ-መንግሥት ትርጉም ውሳኔ ሰጥቷል። በተጨማሪም ተከሳሽ ጥፋተኛ አለመሆኑን በተራው የሚጠበቅበት በዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ላይ ምክንያታዊ ጥርጣሬን (reasonable doubt) መፍጠር በቂው እንደሆነ ተወስኗል።
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ፣ መዝገብ ቁጥር 151፣ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም 👇 | 611 |
| 10 | HUJL-Vol. 10-2026.pdf | 619 |
| 11 | Hawassa University Journal of Law (HUJL)
Volume 10 | July 2026
This volume features a rich selection of peer-reviewed articles, reflections, case comments, and book reviews addressing key legal developments in Ethiopia and beyond.
Attached below is the full PDF.
Regards,
Jura Legal Update | 621 |
| 12 | ስለ ቅጥር ውል አይነትና የማስረዳት ሸክም
በአሰሪና ሰራተኛ ህግ መሠረታዊ መርህ መሠረት በማንኛውም ሁኔታ የአንድ ሰራተኛ የቅጥር ውል ላልተወሰነ ጊዜ እንደተደረገ ይቆጠራል። አንድን የቅጥር ውል ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ስራ ነው ለማለት ውሉ በአዋጁ ላይ ለተወሰነ ጊዜ ሊደረጉ ይችላሉ ተብለው በተዘረዘሩት የሥራ አይነቶች ስር ሊወድቅና ሊረጋገጥ ይገባል።
ውሉ ለተወሰነ ጊዜ ነው ብሎ የሚከራከረው አሰሪው በመሆኑ፣ ውሉ በህጉ ስር ከሚጠቀሱት ምክንያቶች በአንዱ መደረጉን የማስረዳት ግዴታው በራሱ በአሰሪው ላይ ይወድቃል። በአንጻሩ ሰራተኛው ውሉ ላልተወሰነ ጊዜ ነው ብሎ ሲከራከር በህጉ ግምት (Presumption) ስለሚታገዝ አስቀድሞ የማስረዳት ሸክም የለበትም።
ዋናው ሊታወቅ የሚገባው ነጥብ የቅጥር ውል በጽሁፍ ላይ ለተወሰነ ጊዜ ተብሎ መገለጹ ብቻውን በቂ አለመሆኑ ነው። ይልቁንም የውሉ መሠረት የሆነው የስራ ባህሪ በህጉ ከተዘረዘሩት ልዩ ሁኔታዎች ውስጥ በአንዱ ሊወድቅ ይገባል።
ይህንን የህግ ትርጓሜ በተመለከተ ሰፋ ያለ ግንዛቤ ለማግኘት የሰበር መዝገብ ቁጥር 11924 (ቅጽ 3) እንዲሁም ተመሳሳይ ጭብጥ ያላቸውን ሌሎች የሰበር ውሳኔዎችን እንድታነቡ እጋብዛለሁ። በነዚህ መዝገቦች ላይ የተሰጡት ትንታኔዎች በአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት ውስጥ ለሚነሱ መሰረታዊ የክርክር ነጥቦች ጠቃሚነት ያላቸው ናቸው።
መልካም አዳር!
Jura Legal Update
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/share/1c2WCxGTV7/ | 631 |
| 13 | የወንጀል ክስ በአንድ በኩል ተጎጂዎች ፍትሕ የሚያገኙበት የሕግ ሂደት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በወንጀል የተጠረጠሩ ወይንም የተከሰሱ ግለሰቦች ነፃነት በሕግ የሚገደብበት ነው። በዚሁ መሠረት የወንጀል ክስ መመስረቻ ጊዜ ገደብ በሕግ ወስኖ ማስቀመት በሁለቱ ተፃራሪ መብቶች መካከል ሚዛን ለመጠበቅ የሚያስችል ነው። ስለሆነም ማንኛውም ክስ በሕግ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ሊቀርብ ይገባል።
በፍትህ ሚኒስቴር በንቃተ ሕግና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ | 584 |
| 14 | የወንጀል ክስ ይርጋ በኢትዮጵያ
መግቢያ
ወንጀል ፈፃሚዎች ለፈፀሙት ጥፋት በሕግ ፊት መጠየቃቸውና ተገቢውን ቅጣት መቀበላቸው ተገቢና አስፈላጊም ነው፡፡ ይህም በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ አንድ እንደተመለከተው በወንጀል ሕጉ መሰረት ወንጀል የተደረጉ ድርጊቶች እና የሚያስከትሉትን ቅጣት በመደንገግ ሰዎች ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠቡ አሰቀድሞ ቅድመ-ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ ቢሆንም ቅድመ-ማስጠንቀቂዎች በቂ ባልሆኑ ጊዜ ወንጀል ፈፃሚዎች ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲታቀቡና ለሌሎችም ማስተማሪያ እንዲሆኑ ማድረግን ግቡ ያደረገ ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ግን በወንጀል ሕጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ክስ ሊመሠረት እና አጥፊዎችን ለሕግ ማቅረብ የሚገባ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ክሱ በይርጋ የሚታገድ ይሆናል፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት፣ በሕግ የተመለከተውን የክስ ይርጋ ዘመን እናአቆጣጠር እንዲሁም የክስ ይርጋ ዘመን መቋረጥና መታገድ በአጭሩ እንመለከታለን፡፡
የወንጀል ክስ ይርጋ ምንነት
የወንጀል ሕጉ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት በተመለከተ ቀጥተኛ ትርጓሜ ባይሰጥም ከወንጀል ሕግ አንቀጽ 217 በመነሳት የወንጀል ክስ ይርጋ ማለት በማናቸውም ወንጀል ጉዳይ በግል አቤቱታ ወይም በወንጀል ክስ አቅራቢነት ጉዳዩ በዳኝነት ከመታየት የሚታገድበት በሕግ የተመለከተ ጊዜ መሆኑን መረዳት ይቻላል።
የመደበኛ ክስ ይርጋ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217 መደበኛ የክስ ማቅረቢያ ጊዜን የደነገገ ሲሆን
• የሞት ፍርድ ወይም የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አምስት ዓመት
• ከአስር ዓመት በላይ እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችሉ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አመት
• ከአምስት ዓመት በላይ እስከ አስር ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስራ አምስት አመት
• ከአምስት አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስር ዓመት
• ከአንድ ዓመት በላይ በቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአምስት ዓመት
• እስከ አንድ ዓመት ቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወይም በመቀጮ ብቻ ለሚያስቀጣ ወንጀል በሦስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ ክሱ በይርጋ ይታገዳል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ተደራራቢ ወንጀሎች ተፈጽመው ሲገኙ የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች ተመሳሳይ በሚሆኑበት ጊዜ የአንዱ ወንጀል የክስ ማቅረብያ የይርጋ ዘመን በሁለቱም ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆንና የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች የተለያዩ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ከሁሉም ከባድ የሆነው ወንጀል የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን በሌሎች ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217(2) ይደነግጋል፡፡
በግል አቤቱታ አቅራቢነት የሚያስቀጡ ወንጀሎች ይርጋ
በወንጀል ሕጉ ልዩ ክፍል ወይም በሌላ ማሟያ የወንጀል ሕግ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ እንደሚያስቀጡ የተደነገጉ ወንጀሎች የግል ተበዳዩ ወይም ሕጋዊ ወኪሉ የግል አቤቱታ ካላቀረበ በስተቀር ክስ እንደማይመሰረት በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 212 ተደንግጓል ፡፡ ለአንብነትም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 560 የእጅ እልፊት ወንጀል በግል አቤቱታ ሲቀርብ የሚስቀጣ ወንጀል መሆኑ ተደንግጓል፡፡ መሰል በግል አቤቱታ የሚቀርቡ ወንጀሎች የተፈፀመበት የግል ተበዳይ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 213 መሠረት አቤቱታውን ማቅረብ የሚጠበቅበት ሲሆን የእነዚህ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ የሚያስቀጡ ወንጀሎች የክስ ይርጋ ዘመን ሁለት አመት እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 218 ተደንግጓል፡፡
ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን
በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 222 ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን የተደነገገ ሲሆን በማናቸውም ምክንያት ከላይ የተመለከትነው መደበኛ የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን እጥፍ ጊዜ ካለፈ ወይም በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎች ሲሆኑ ደግሞ ከላይ ከተመለከትነው በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎችን የይርጋ ዘመን በግማሽ የሚበልጥ ጊዜ ካለፈ በወንጀሎቹ ላይ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡
የክስ ይርጋ አቆጣጠር
በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 219 መሠረት የክስ የይርጋ ዘመን የሚታሰበው የቅጣት ማክበጃ ወይም ማቅለያ ሁኔታዎች ግምት ውስጥ ሳይገቡ በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ሲሆን የተፈፀመው ወንጀል በተለዋጭ ወይም በተደራራቢ ተፈፃሚነት በሚኖራቸውም ቅጣቶች የሚያስቀጣ ሲሆን የይርጋ ዘመኑ የሚታሰበው ከሁሉም ከባድ ለሆነው ወንጀል በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ይሆናል፡፡
የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረውም ጥፋተኛው የወንጀል ድርጊቱን ከፈጸመበት ቀን አንስቶ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱ እየተደጋገመ የተፈፀመ ከሆነም የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የመጨረሻው የወንጀል ድርጊት ከተፈፀመበት ቀን አንስቶ ነው፡፡ የወንጀል ድርጊቱ ለረጅም ጊዜ ሲፈፀም የቆየ ከሆነ ደግሞ የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የወንጀል ድርጊቱ ካቆመበት ቀን ጀምሮ ይሆናል፡፡
የክስ ይርጋ መታገድ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 220 የወንጀል ክስ ይርጋ የሚታገድበትን ሁኔታ የደነገገ ሲሆን ይኸውም
በሕግ ወይም በፍሬ ነገር ክሱ እንዳይጀመር ወይም እንዳይቀጥል የሚያግድ መሰናክል ካለ መሰናክሉ እስካለ ድረስ
ክስ ቀርቦ ነገሩ በዳኝነት በመታየት ላይ ከሆነ ወይም በሌላ ችሎት የቀረበ ክስ ሳይፈፀም ተከሳሹ በተከሰሰበት የወንጀል ክስ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ የማይገባ በሆነ ጊዜ
የይርጋ ዘመኑ ታግዶ ይቆያል፡፡ መታገዱን ያስከተለው መሰናክል ሲወገድ ግን የይርጋ ዘመኑ ወዲያውኑ መቆጠር ይጀምራል፡፡
የይርጋ ዘመን መቋረጥ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 221 እንደሚያመለክተው ከወንጀሉ ወይም ከወንጀለኞቹ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ምርመራ እንዲካሄድ፣ ብርበራ እንዲደረግ፣ መጥሪያ እንዲሰጥ ወይም ክስ እንዲቀርብ የሚሰጥ ትዕዛዝ፣ የሚፈፀም ድርጊት ወይም የሚሰጥ ውሳኔ የይርጋ ዘመኑን መቆጠር ያቋርጣል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ የይርጋ ዘመን እንደገና እንደ አዲስ መቆጠር ይጀምራል፡፡ በድንጋጌው መሠረት የይርጋ ዘመኑ መቋረጥ ፍፁም የሆነ ውጤት የሚኖረው ሲሆን በወንጀሉ ተካፋይ መሆናቸው ለታወቀውም ሆነ ላልታወቀው ሁሉ መቋረጡ ይፀናባቸዋል፡፡ ይህ ማለት የወንጀል ተካፋይ መሆናቸው ወንጀሉ በተከሰተበት ጊዜ ያልታወቁ ሰዎች ያኔ ባለመታወቃቸው ምክንያት የይረጋ መቋረጥ አስመልክቶ ሊኖር የሚችል ልዩነት እንደሌለ መረዳት ይቻላል፡፡
በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች
በመርህ ደረጃ የወንጀል ድርጊቶች ከተፈፀሙ በኋላ ክስ ለማቅረብ የሚቻልበት የጊዜ ገደብ በግልፅ ሰፍሮ ያለ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ በሌላ ሕግ ከተደነገገ በይርጋ የማይታገዱ ወንጀሎች እንዳሉ ከወንጀል ሕጉ እንቀጽ 216(1) መገንዘብ ይቻላል፡፡ ከዚህ አንፃር የኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕገ መንግሥት ቀዳሚው ሲሆን በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 28(1) መሠረት ኢትዮጵያ ባፀደቀቻቸው ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶችና በሌሎች የአገራችን ሕጎች የሰው ልጅ ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች ተብለው የተወሰኑ ወንጀሎች፣ የሰው ዘር የማጥፋት፣ ያለፍርድ የሞት ቅጣት እርምጃ የመውሰድ፣ በአስገዳጅ ሰውን የመሰወር ወይም የኢሰብዓዊ ድብደባ ድርጊቶችን በፈፀሙ ሰዎች ላይ ክስ ማቅረብ በይርጋ አይታገድም።
ማጠቃለያ | 609 |
| 15 | لا يوجد نص... | 486 |
| 16 | Ethiopia-Capital-Market-Proclamation-No.1248_2021.pdf | 693 |
| 17 | የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ግብይት እንዲኖር መሠረት የጣለ የሕግ ማዕቀፍ ነው።
የአዋጁ ዋና ዋና ዓላማዎች፡ ኩባንያዎችና መንግሥት ለልማትና ለንግድ ማስፋፊያ የሚሆን የረጅም ጊዜ ገንዘብ ከአክሲዮንና ከቦንድ ሽያጭ ማግኘት እንዲችሉ ማድረግ፤ ግለሰቦችና ተቋማት በቁጠባ ያስቀመጡትን ገንዘብ በካፒታል ገበያ ላይ በማዋል ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ማመቻቸት እና የኢንቨስትመንት ስጋቶችን ለብዙ ባለሀብቶች በማካፈል የፋይናንስ ሥርዓቱን ማጠናከር ናቸው።
አዋጁ ገበያው በነፃነትና በፍትሐዊነት እንዲመራ የሚያደርጉ ቁልፍ ተቋማዊ መዋቅሮችን ገንብቷል። ከነዚህም መካከል የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን (ECMA) ገበያውን የሚቆጣጠር፣ ፈቃድ የሚሰጥና የኢንቨስተሮችን ከማጭበርበር የሚጠብቅና ገበያው ግልጽና ፍትሐዊ እንዲሆን የሚያደርግ ራሱን የቻለ ተቆጣጣሪ ተቋም ሆኖ ተቋቁሟል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ (ESX) የአክሲዮኖች፣ ቦንዶችና ሌሎች የፋይናንስ ሰነዶች ግብይት የሚካሄድበት ዘመናዊ መድረክ ሆኖ የተዘረጋ ሲሆን፣ በገበያው ላይ የሚነሱ ክርክሮችንና አቤቱታዎችን ፈጣንና ልዩ በሆነ መንገድ ለመዳኘት የሚያስችል የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም ተደርጓል።
የካፒታል ገበያ ስኬታማ የሚሆነው የኢንቨስተሮች እምነት ሲጠበቅ በመሆኑ፣ አዋጁ ለክትትልና ጥበቃ የሕግ ማዕቀፍ ፈጥሯል። በተጨማሪም ሰነደ ሙዓለ ንዋይ የሚያወጡ ኩባንያዎች ትክክለኛና ወቅታዊ የፋይናንስ መረጃዎቻቸውን ለሕዝብ ይፋ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ይደነግጋል።
የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 ሙሉ የPDF ሰነድ ከዚህ በታች ተያይዞ ያገኙታል። 👇
Jura Legal Update | 679 |
| 18 | የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ ዘመናዊና የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ግብይት እንዲኖር መሠረት የጣለ የሕግ ማዕቀፍ ነው።
የአዋጁ ዋና ዋና ዓላማዎች፡ ኩባንያዎችና መንግሥት ለልማትና ለንግድ ማስፋፊያ የሚሆን የረጅም ጊዜ ገንዘብ ከአክሲዮንና ከቦንድ ሽያጭ ማግኘት እንዲችሉ ማድረግ፤ ግለሰቦችና ተቋማት በቁጠባ ያስቀመጡትን ገንዘብ በካፒታል ገበያ ላይ በማዋል ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ማመቻቸት እና የኢንቨስትመንት ስጋቶችን ለብዙ ባለሀብቶች በማካፈል የፋይናንስ ሥርዓቱን ማጠናከር ናቸው።
አዋጁ ገበያው በነፃነትና በፍትሐዊነት እንዲመራ የሚያደርጉ ቁልፍ ተቋማዊ መዋቅሮችን ገንብቷል። ከነዚህም መካከል የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን (ECMA) ገበያውን የሚቆጣጠር፣ ፈቃድ የሚሰጥና የኢንቨስተሮችን ከማጭበርበር የሚጠብቅና ገበያው ግልጽና ፍትሐዊ እንዲሆን የሚያደርግ ራሱን የቻለ ተቆጣጣሪ ተቋም ሆኖ ተቋቁሟል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ (ESX) የአክሲዮኖች፣ ቦንዶችና ሌሎች የፋይናንስ ሰነዶች ግብይት የሚካሄድበት ዘመናዊ መድረክ ሆኖ የተዘረጋ ሲሆን፣ በገበያው ላይ የሚነሱ ክርክሮችንና አቤቱታዎችን ፈጣንና ልዩ በሆነ መንገድ ለመዳኘት የሚያስችል የካፒታል ገበያ አስተዳደራዊ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም ተደርጓል።
የካፒታል ገበያ ስኬታማ የሚሆነው የኢንቨስተሮች እምነት ሲጠበቅ በመሆኑ፣ አዋጁ ለክትትልና ጥበቃ የሕግ ማዕቀፍ ፈጥሯል። በተጨማሪም ሰነደ ሙዓለ ንዋይ የሚያወጡ ኩባንያዎች ትክክለኛና ወቅታዊ የፋይናንስ መረጃዎቻቸውን ለሕዝብ ይፋ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ይደነግጋል።
የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 ሙሉ የPDF ሰነድ ከዚህ በታች ተያይዞ ይገኛል። 👇 | 1 |
| 19 | በነገራችን ላይ፣
ከሁለት ወይም ሶስት ቀናት በፊት ባስነበብኳችሁ የሰበሩ ውሳኔ ላይ እንደተመለከትነው፣ በትዳር ዘመን የተገኘ የደም ካሣ የጋራ ንብረት ነው ወይስ የግል? የሚለው ጭብጥ አከራካሪ ጉዳይ ነው። ይህ ጥያቄ የሕጉን ቀጥተኛ ቃላት ብቻ ሳይሆን የሕጉን መንፈስና የሕግ አውጪውን መሠረታዊ ሀሳብ መመርመርን ይጠይቃል። አንድ እናት በቀደመ ትዳሯ የወለደችው ልጇ በአደጋ ምክንያት ቢሞትባትና የተከፈላትን የካሣ ገንዘብ ለቤት መስሪያ ብታውለው፣ በኋላ ከሁለተኛ ባሏ ጋር በሚፋቱበት ጊዜ ይህ ንብረት እንደ ማንኛውም በትዳር ዘመን እንደተገኘ ገቢ ተቆጥሮ እኩል ሊከፈል ይገባል ወይስ አይገባም? የሚለው ጭብጥ ምርመራ የሚያስፈልገው ጉዳይ ነው።
በቀደመው ልጥፍ እንደገለጽነው፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 26953 (ቅጽ 5) በሰጠው ውሳኔ፣ መልስ ሰጪ (ሚስት) ቤቱ በልጅ ሞት ምክንያት በተሰጠ የደም ካሣ የተሰራ በመሆኑ የግል ሀብቴ ሆኖ ይቀጥላል ማለቷን ጠቅሶ፣ ነገር ግን አባባሏን የሚደግፍ በቂ የሕግ ክርክር አላቀረበችም በሚል አቋም ይዟል። ችሎቱ የካሣ ክፍያው ምክንያት ምንም ይሁን ምን ክፍያ ማግኘቷንና በእርሱም ቤቱ መሰራቱን ስላልካደች፣ ክፍያው በትዳር ውስጥ እያሉ የተገኘ ገቢ በመሆኑ የጋራ ንብረት ነው በሚል ድምዳሜ ላይ ደርሷል።
ሆኖም ይህ ዓይነቱ ሜካኒካዊ የሕግ አተገባበር የቤተሰብ ሕጉን መሠረታዊ ፍልስፍና እና የካሣ ሕግን ተፈጥሮ ያገናዘበ አይደለም። በተሻሻለው የፌዴራል የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 62 ስር በትዳር ዘመን የተገኘ ንብረት ወይም ገቢ የጋራ እንደሚሆን የተደነገገ ሲሆን፣ በአንቀጽ 63 ስር ደግሞ አንደኛው ተጋቢ የግል ሀብቱ መሆኑን ካላስረዳ በስተቀር ማንኛውም ንብረት የጋራ እንደሆነ የሚወሰድ የሕግ ግምት ተቀምጧል። በአንቀጽ 62 ንዑስ አንቀጽ 1 ላይ ባልና ሚስት ከግል ጥረታቸውና ከንብረታቸው የሚያገኟቸው ገቢዎች ሁሉ የጋራ ሀብቶቻቸው እንደሚሆኑ ይደነግጋል።
ነገር ግን የደም ካሣ በሥራ፣ በጥረት ወይም በንግድ እንቅስቃሴ የተገኘ የኢኮኖሚ ጥቅም አይደለም። የደም ካሣ በባህሪው ለደረሰ ሀዘን፣ ጉዳትና ስብራት የሚሰጥ ማጽናኛ ነው። ክፍያው የተጎዳውን ወይም ሀዘን የደረሰበትን ወገን ለማካካስ የሚሰጥ እንጂ ከግል ወይም ከጋራ ጥረት የተገኘ ገቢ ሊሆን አይችልም። በስጦታ ወይም በውርስ የተገኘ ንብረት በቤተሰብ ሕጉ አንቀጽ 57 ስር የግል ሀብት እንዲሆን የተደረገበት ምክንያት ከግል ወይም የጋራ ጥረት ውጪ የተገኘ በመሆኑ ከሆነ፣ በሰው ሕይወት ማለፍ ምክንያት የሚገኝ የጉዳት ካሣና ማጽናኛማ ከስጦታና ከውርስ በበለጠ ሁኔታ ከግለሰቡ ጋር በጥብቅ የተያያዘ የግል ሀብት ሊሆን ይገባ ነበር።
ዶክተር መሐሪ ረዳኢ "የፌደራል የቤተሰብ ሕግ፡ ይዘት እና አተገባበር" (2012 ዓ.ም፣ ገጽ 88-89) በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ የሰበር ሰሚ ችሎቱን ውሳኔ ሲተቹ፣ የጉዳት ካሣ እንደ መደበኛ ገቢ ተቆጥሮ የጋራ ሀብት የሚሆንበት አሰራር አሳማኝ አለመሆኑን ይሞግታሉ። የጉዳት ካሣ የሥራና የጥረት ውጤት ተደርጎ የሚወሰድ ገቢ ሳይሆን፣ ለደረሰ መራራ ሀዘን ማካካሻ ተብሎ የሚሰጥ ማጽናኛ በመሆኑ፣ በግብር ሕግም ሆነ በአሠሪና ሠራተኛ ሕግ ስር ገቢ ተብሎ ግብር እንደማይከፈልበት ሁሉ በቤተሰብ ሕግም በተመሳሳይ ዕይታ ሊቃኝ እንደሚገባ ያመላክታሉ። እናት በሞተ ልጅ ሕመም ያገኘችውን ማጽናኛ ከተለየችው ባሏ ጋር እንድትካፈልና በእርሱ የተገዛን ንብረት እንድታጣ ማድረግ ሁለተኛ ሞትና ልጃቸውን የሚያስታውሱበትን ምልክት ማጣት እንደሆነ በመግለጽ፣ የሰበር ሰሚ ችሎቱ አቋም ከሕግ አውጪው መንፈስ ጋር የሚጣጣም እንዳልሆነ ይሞግታሉ።
በሌሎች ሀገራት የቤተሰብ ሕግ ተሞክሮም፣ ለምሳሌ በፖላንድ ሕግ፣ በአካልና በስነ-ልቦና ላይ ለሚደርስ ጉዳት የሚከፈል የሞራል ካሣ በግልጽ የተጎጂው የግል ሀብት ተደርጎ ይወሰዳል።
ሲጠቃለል፣ በትዳር ዘመን የተገኘ የደም ካሣም ሆነ በእርሱ የተገዛ ንብረት፣ ከባልና ሚስት የግል ወይም የጋራ ጥረት የተገኘባለመሆኑ እና ሙሉ በሙሉ ግላዊ ባህሪ ያለው በመሆኑ፣ የእንደዚህ ዓይነቱ ጉዳት ሰለባ የሆነው ተጋቢ የግል ሀብት እንጂ የጋራ ንብረት ሊሆን አይገባም። በመሆኑም ወደፊት ሕግ አውጪው ሕጉን ሲያሻሻል እንዲህ አይነት ልዩ ሁኔታዎች (exceptions) በግልጽ ሊደነግግ ይገባል። እስከዚያው ድረስ ግን፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የካሣን መሠረታዊ ባህሪ፣ የሕጉን መንፈስ እና የሕግ አውጪውን ዓላማ ባገናዘበ መልኩ ቀደሞ የሰጠውን የሕግ ትርጉም በድጋሚ ሊመረምረውና ሊያርመው የተገባ ነው።
መልካም አዳር!
Jura Legal Update
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቴሌግራም: https://t.me/JuraLegalUpdate | 683 |
| 20 | لا يوجد نص... | 680 |
