Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 345 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 649,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 354 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 345 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -112,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 39.43%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.21% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 656 次浏览,首日通常累积 1 752 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 345
订阅者
-724 小时
-387 天
-11230 天
帖子存档
14 343
መድረክ ላይ በወጣ ቁጥር ለአማራ ያለውን ጥላቻ መደበቅ የሚሳነውና "የአማራ ሸኔ" የሚል ታርጋ ሲለጥፍ የተሰማው ሰውዬ ከህው*ሓት ጋር ተቧድኖ አማራ ክልልን የሚወርበት ቀን ሩቅ አይሆንም።
14 343
በገጠሩ አካባቢ የሚኖረው ማሕበረሰብ በችግሮቹ ዙሪያ መምከርና የመፍትሔ ሐሳቦችን መቀመር ሲፈልግ ከጠራራ ጸሐይ የሚታደግ ጠለስ ወይንም ጥላ (ታዛ) ያለው ስፍራ ፈልጎ እንዲሰበሰብ ሁሉ ጠለስ ቲዩብም የተለያዩ ሒሶችን እና መወድሶችን የያዙ፣ የአገራችንን ፖለቲካዊ፣ ኦኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ጉዳዮችን በኪናዊ መንገድ የሚያዋዙ፣ በእውነታና በሐቅ ባላዎች ላይ የተመረኮዙ፣ እንዲሁም ሰናይ ክንውኖችን ሲያወድሱ፣ እኩይ ድርጊቶችን የሚያሔሱ ዝግጅቶች የሚቀርቡበት ፕሮግራም ነው፡፡ ስለሆነም ጠለስ ቲዩብን Subscribe በማድረግ ጠለሳችንን ያደምቁልን ዘንድ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡
14 343
ቁንጣን በሚያስደስተው ሆድ ፈንታ የወገን ጥቃት የሚንገበግበው ልብ ይዘው የተፈጠሩ 'ጀግና ልጆቹ' ትግል በጀመሩ ማግስት ከጉያው እየታደኑ ወደ ወሕኒ እና ወደ መቃብር ሲወርዱ፣ አድፍጦ የሚመለከት ማሕበረሰብ፣ በመከራው ወቅት የሚያወርደው እንባና ደም ክንፍ ያለው መልዓክ እስኪያወርድለት ድረስ የሕልውና አደጋውን ጸጋው አድርጎ መቅበዝበዝ ግዴታው ነው።
አሳዬ ደርቤ
14 343
የአፋልጉኝ ማስታወቂያ
የብልጽግና አካሄድና ፖለቲካ ቀድሞ የገባው ይህ ሐቀኛ ፖለቲከኛ ከጨዋታ ሜዳው ላይ ከተሰወረ ወራቶች ተቆጠሩ።
እናም እገታውን የፈጸመው መንፈስ እስክንድርን ለቅቆ የጃንጥራርን ደብዛ እንዲያጠፋልን እንጠይቃለን።
14 343
በልተው የማይጠግቡ፣ ቀምተውና ዘርፈው የማይረኩ፣ ገድለውና አውድመው የማያበቁ፣ ጠይቀው የማያባሩ... አረመኔዎች ሥልጣን ከያዙ በኋላ ከኢትዮጵያ ሰማይ ስር እረፍት ማድረግ እርም ሆነ።
14 343
በመልካም ወጣት ሥም የድሃ ቤት ከማፍረስ አልፎ በሃይማኖት ግጭት የወጣቶችን ደም ለማፋሰስ ቆርጦ የተነሳ እኩይ ሰው!ለነገሩ እነ ሙዓዘ ጥበባትን ያፈራች ቤተክርስቲያን ከዚህ የተሻለ እጣ ሊኖራት አይችልም።
14 343
ከአንድ ወር በፊት ከመስከረም አበራ ጋር ቡና እየጠጣሁ "ሞት እና ስደት ለተፈረደበት ወገንሽ ጠበቃ ሆነሽ የምታደርጊው ሙግት እስራት አምጥቶ ከሕጻን ልጅሽ እንዳይነጥልሽ..." በማለት ስጋቴን ስገልጽላት መስኪ የሰጠችኝ መልስ ... 👇
"አድጎ መራመድ ሲጀምር፥ እናት አገር የማይኖረው፣ የዜግነት ክብር እና የነፃነት አየር የሚጠማው ሕፃን ልጅ ከመኝታ ቤቴ ውስጥ ታቅፌ ጡት እያጠባሁ የወደፊት እጣ-ፈንታውን እና ባርነቱን ከማሰላሰል ይልቅ ፥ ለወለደኝ ወገንም ሆነ ለወለድኩት ሕጻን እኩልነት እና ነጻነት የማደርገው ትግል ሥጋት የፈጠረባቸው ቡከኖች የሚበይኑትን እስራትና ቅጣት ተቀብዬ ያለ እናት እና ያለ ጡት ያድግ ዘንድ የፈረዱበትን ልጄን ማሰብ የተሻለ ምቾት ይፈጥርብኛል" የሚል ነበረ።
አከብርሻለሁ ውዷ እኅቴ!!
14 343
የታፋኙ ማስታወሻ😆
▬▬▬▬▬▬
ልፋቴ በሞት እስኪጠናቀቅ ድረስ ላለፉት ሃያ ቀናት የመድሃኒት ማዘዣ አንጠልጥዬ ሆስፒታል ለሆስፒታል ስንከራተት ነበር። በዚህም የተነሳ፥ ይሄ እንኩቶ ሥርዓት የሚፈጽመውን የሕፃን ጨዋታ የምቃወምበት በቂ ጊዜ አላገኘሁም ነበር።
እንዲያም ሆኖ ታዲያ ኦነግ መራሹ ሥርዓት "አሳዬ ደርቤ የአዲስ አበባ ተማሪዎችን አመጽ ሲያቀነባብር ነበር" በማለት ከእነ ስንታየሁ ቸኮል፣ መስከረም አበራ፣ መዓዛ መሐመድ፣ ዶክተር ቴዎድሮስና ዘሪሁን ገሰሰ ጋር የእስር ማዘዣ እንዳወጣብኝ ሰማሁ።
እናም መረጃው እውነት ሆኖ ይሄ እንኩቶ ፓርቲ ሙሥና እና የዜጎች ደም ባጨቀየው መዳፉ ለሁለተኛ ጊዜ ሳያፍነኝ በፊት ጀግኖቹን እያስበላ ቂጣውን ለሚያላምጠው ከንቱ ፍጥረት "የታሠሩ ልሳኖችህን ማስፈታት ቢሳንህ እንኳን እስር ቤት ሄደህ ጠይቃቸው" ማለት እሻለሁ።
በተረፈ በሕይወት እስካለሁ ድረስ ይሄንን አስነዋሪ ሥርዓት መታገሌን አጠናክሬ የምቀጥል መሆኔን እገልጻለሁ።
ዝንታለም አማራ!!
14 343
የእኅቴ ኀዘን ላይ ብሆንም፤ የኦሮሞ አመራሮች፣ ፖለቲከኞች እና አክቲቪስቶች በሚፈጽሙት አገር የማተራመስ መርሐ ግብር አማራዎችን እና የአዲስ አበባ ልጆችን ማሰር ልክ አይደለም እላለሁ።
የአዳነች አቤቤ ካቢኔ ከሕፃናት ጋር በሚያደርገው ግብግብ እነ መስከረም አበራን እና ናትናኤል ያለምዘውድን እያፈኑ ከእስር ቤት መጎድጎድ እጅግ አስነዋሪ ወንጀል ነው እላለሁ።
14 343
የሆነ ነገር በጻፍኩ ቁጥር "እባክህ እነዚህ አረመኔዎች እንዳይገድሉህ..." እያለች የምትጨቀጭቀኝን ታላቅ እኅቴን አፈር አለበስኳት።
ነፍስሽን ይማረው እኅታለም!!
14 343
የዘር ማጥፋት ቅስቀሳ ማድረግ የተፈቀደለት ውርንጭላ...!!
የሚገርመው ነገር ለሚዲያዎች እውቅና ለመስጠት አንድ ዓመት የሚፈጅበት የመገናኛ ብዙሐን ባለሥልጣን፤ ይህ ጥጃ ጥላቻውን ለሚያዝረበርብበት ሚዲያ እውቅና የሰጠው በአንድ ሳምንት ውስጥ መሆኑ ነው።
14 343
ከትናንት ወዲያ ማታ ገጀራ የያዙ ወጣቶችን እና ልዩ ሃይሎችን የጫነ 30 መኪና ወደ አንገር ጉትን መጠጋት ጀምሮ ነበር። የእናንተ ጩኸትና እሪታ ግን በዚህ የጥፋት ኃይል ፈንታ መከላከያን ማስገባት ችሏል።👏
14 343
ሕዝቡ ይሄን ሥርዓት ማሽቀንጠር አለበት" የሚል ትዕዛዝ ከማስተላለፍህ በፊት የብልጽግና አባል ተብለው ወርሐዊ ክፍያ ከሚከፍሉትና ፓርቲውን ከተሸከሙት 4 ሚሊዮን አማራዎች መሀከል አንዱ አለመሆንህን አረጋግጥ!
14 343
በንጹሐን እንባ የተለኮሰው የሳቅህ እድሜ ሲገመት ለአረመኔዎች አሳልፈህ ከሰጠኸው ሕዝብ የለቅሶ ዘመን አይረዝምም።
እናም...
በብዙዎች ሳግ የብቻህን ሳቅ እንደፈጠርክ ሁሉ፤ እንደ በረከት ስምዖን ለብቻህ የምታዝንበት ረዥም የትካዜ ወቅት ከፊትህ አለ።
በመሆኑም የእንባህ ዘመን ከመድረሱ በፊት የጎዳና ተዳዳሪውን ፓርቲ ማሕተም ለባለቤቱ አስረክበህ መሐረብ ግዛ።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
