AACRA
Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to A.A.
显示更多📈 Telegram 频道 AACRA 的分析概览
频道 AACRA (@addisroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 10 884 名订阅者,在 交通 类别中位列第 2 157,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 3 045 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 10 884 名订阅者。
根据 29 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -5,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 10.62%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.77% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 154 次浏览,首日通常累积 844 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 2。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to ...”
凭借高频更新(最新数据采集于 30 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
数据加载中...
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 30 六月 | +16 | |||
| 29 六月 | 0 | |||
| 28 六月 | +10 | |||
| 27 六月 | +6 | |||
| 26 六月 | +7 | |||
| 25 六月 | +16 | |||
| 24 六月 | +4 | |||
| 23 六月 | +3 | |||
| 22 六月 | 0 | |||
| 21 六月 | 0 | |||
| 20 六月 | 0 | |||
| 19 六月 | +11 | |||
| 18 六月 | 0 | |||
| 17 六月 | +2 | |||
| 16 六月 | +5 | |||
| 15 六月 | +4 | |||
| 14 六月 | +4 | |||
| 13 六月 | +9 | |||
| 12 六月 | +1 | |||
| 11 六月 | +1 | |||
| 10 六月 | +8 | |||
| 09 六月 | +7 | |||
| 08 六月 | +6 | |||
| 07 六月 | +1 | |||
| 06 六月 | 0 | |||
| 05 六月 | 0 | |||
| 04 六月 | +4 | |||
| 03 六月 | +2 | |||
| 02 六月 | 0 | |||
| 01 六月 | 0 |
| 2 | 没有文字... | 993 |
| 3 | ሰዉ አጠፋዉ፤ ሰዉ አለማዉ!!
ፈጣሪ የሰጠንን ቀበና “ሰዉ “ አጠፋዉ ፤ ይህ የተፈጥሮ ስጦታ መጥፋት ቁጭት ያደረበት “ሰዉ “ ደግሞ ቀበናን ዳግም እንደ አዲስ እንዲወለድ አደረገዉ።
የቀበና ወንዝ ለዘመናት በዘፈን እና በትዝታ ብቻ ስሙ ሲነሳና ሲወደስ ኖሮ ዛሬ ግን ዳግም እንዲወለድ አድርጐ አለማዉ!!
አርቲስት ፀሀዬ ዮሀንስ “ቢሻን ቀበና” እያለ ብዙዎች እየዋኙ ያደጉበትን የልጅነት ትዝታን ሲቀሰቅስ ፣የክብር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ “ቢሻን አዲስ አበባ “ እያለ ሲያደናንቅ በዘመናት ውስጥ ግን ትዝታን ብቻ ተሸክሞ የወንዙ ተፈጥሮዊ ማንነት ጠፍቶ ፣የፍሳሽ መዉረጃና የቆሻሻ መጣያ ሆኖ፣ ጠረኑ አላስጠጋ ብሎ ተረስቶ የኖረ ወንዝ ነበር ።
እነሆ እነዚህ የብክለት ፣ የበሽታ ምንጭና የቆሻሻ ማጠራቀሚያ የነበሩትን ወንዞቻችንን ዛሬ ላይ በትጋት እና በላብ እየታከሙ፣ ለነዋሪው ተስፋን ሀሴትን የሚለግሱ የደስታ ምንጭ እየሆኑ ነው፡፡
በአጭር ጊዜ የተገነባው ይህ ድንቅ ፕሮጀክት፣ ከሌሎች የከተማዋ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ጋር ተዳምሮ አዲስ አበባን የውበት ማማ አድርጓታል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ | 857 |
| 4 | ድምቀት ጌጥ እና የውበት ፀዳል!!
"አዲስ አበባችን የነዋሪዎቿን ጥያቄዎችና መሰረታዊ ፍላጎቶች በተጨባጭ እየመለሰች፤ ለህዝባችን ቅድሚያ የሚሰጣቸውንና ከተማዋ የሚመጥናትን ታላላቅ የልማት ስራዎች ሁሉ በላቀ ብቃትና ትጋት እያከናወነች ትገኛለች።"
ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ | 653 |
| 5 | ገንዘብን፣ እውቀትን፣ ጉልበትን፣ ሀሳብን፣ የአመራር ብቃትን ስንደምር የሚከሰተው ነገር እንደዚህ ያለው ውበት ይሆናል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) | 596 |
| 6 | 没有文字... | 921 |
| 7 | የእንጦጦ - ቀበና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት በጥቂቱ፦
ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ከያዛቸው መሰረተ ልማቶች ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፤
- የወንዝ ልማት፦ 1 ትልቅ ግድብ፣ 16 አነስተኛ ግድቦች፣ 3 ቼክ ዳሞች እና 20.2 ኪ.ሜ የድጋፍ ግንብ።
- የወንዝ ዳርቻ ልማት፦ 36,928 ካ.ሜ የአፈር እና ስነ-ምህዳር ጥበቃ ስራዎች (የኮንሶ ጋቢዮን እና እርከን)።
- አረንጓዴ ልማት፦ 59.7 ሄክታር የአረንጓዴ ሽፋን እና 50,330 የተተከሉ ዛፎች።
- የተቀናጀ መሰረተ ልማት፦ 21 የእግረኛ ድልድዮች፣ 33.2 ኪ.ሜ የውስጥ መንገዶች፣ የፍሳሽ መስመር እና 695 ተሽከርካሪዎችን ማቆም የሚያስችሉ 7 ቦታዎች።
ይህ ፕሮጀክት ስነ-ምህዳሩን ከመቀየር ባለፈ፣ በውስጡ በያዛቸው ሱቆች፣ ካፌዎች እና የቱሪዝም መዳረሻዎች አዳዲስ የንግድና የኢኮኖሚ እድሎችን በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል።
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers | 714 |
| 8 | 87.6 ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን እና 10.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውን የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን ዛሬ በይፋ መርቀናል። ይህ ሰፊ መሰረተ ልማት የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ስፍራዎችን በጋራ የያዘ ነው። ፕሮጀክቱ የግንባታ ስኬት ብቻ ሳይሆን፣ መዲናችንን የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋምና ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች፣ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ የጀመርነውን ስልታዊ ሽግግር የሚያፋጥን ታላቅ አጋጣሚ ነው።
የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን!
#EthiopiaDelivers
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ | 906 |
| 9 | እንጦጦ እስከ ቀበና የወንዝ ዳርቻ ሲገለጥ
Entoto to Kebena Riverside Unveiled
#EthiopiaUnveiled
ጠቅላይ ሚኒስት ዶ/ር አብይ አህመድ | 902 |
| 10 | ዛሬም የረዳን ፈጣሪ ይመስገን !
ዛሬ ለከተማችን ነዋሪዎአች አዲስ ድንቅ ሌላ ስጦታ የሆነውን "የእንጦጦ - ቀበና የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት" እና የቀበና ግድብ ፕሮጀክት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መርቀዉልን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።
አዲስ አበባችን የነዋሪዎቿን ጥያቄዎችና መሰረታዊ ፍላጎቶች በተጨባጭ እየመለሰች፤ ለህዝባችን ቅድሚያ የሚሰጣቸውንና ከተማዋ የሚመጥናትን ታላላቅ የልማት ስራዎች ሁሉ በላቀ ብቃትና ትጋት እያከናወነች ትገኛለች።
ዛሬ ለከተማችን አዲስ አበባ ድምቀትና ተጨማሪ ጌጥ እና የውበት ፀዳል ያላበሰውን ይህን የወንዝ ዳርቻ እና የግድብ ልማት በክቡር ቨቅላይ ሚስትራችን ሀሳብ አመንጪነት በተሰጠን የስራ መመሪያ መሰረት በጥራትና በፍጥነት አጠናቀን ለህዝብ አቅርበናል። ፕሮጀክቱ በከተማዋ ከተሰሩት ሌሎች የኮሪዶር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች ጋር ተዋህዶ ሲታይ በእርግጥም አዲስ አበባ በአለም አቀፍ ደረጃ ምርጧ የቱሪስት መዳረሻ ብቻ ሳትሆን የውበት ማማ የሚያደርጋት ድንቅ ፕሮጀክት ነው፡፡
ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 87.6 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሲሆን፣ 10.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው። በውስጡም እጅግ ማራኪ የሆኑ የጋራ አገልግሎት መስጫዎችንና የህዝብ መገልገያዎችን አሟልቶ ይገኛል። ይህም 1 ትልቅ ግድብ፣ 16 አነስተኛ ግድቦች፣ 3 ቼክ ዳሞች፣ 1.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ሃይኪንግ፣እንዲሁም 20.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የወንዝ ድጋፍ ግድግዳን (Retaining Wall) ያካተተ ነው። የተፈጥሮ ውበቱን ይበልጥ ለማጉላትም 3 ማራኪ ፏፏቴዎች እና 1 የውሃ ምንጭ ግንባታ የተከናወነ ሲሆን፣ የመሬት ጥበቃን ለማረጋገጥ 36,928 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው የኮንሶ ጋቢዮንና የኮንሶ እርከን ስራዎች ተሰርተውለታል።
ልማቱ ለተፈጥሮ በሰጠው ልዩ ትኩረት፣ 59.7 ሄክታር የሚሸፍን ውብ የአረንጓዴ ልማት ስፍራን ያበለፀገ ሲሆን፣ 50,330 የተለያየ ዝርያ ያላቸው ዛፎችም ተተክለውበታል። ከመሰረተ ልማት አቅርቦት አኳያ 10.62 ኪሎ ሜትር ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ፣ 33.2 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገዶች፣ እና 33.2 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን ዘመናዊ የመንገድ መብራት ዝርጋታ ተከናውኗል። በተጨማሪም 19.13 ኪሎ ሜትር የፍሳሽ እና የጎርፍ ማስወገጃ መስመር፣ እንዲሁም 23 ንፁህ የመጸዳጃ ቤቶች ተገንብተዋል። ጎብኚዎች ወንዙን በቀላሉና በውበት እንዲሻገሩ ለማስቻል 21 የእግረኛ ድልድዮች፣ 3 ተንጠልጣይ ድልድዮች፣ 6 የእግረኛ የብረት ድልድዮች፣ 1 ሰርኩላር ድልድይ እና 1 የኮንክሪት ድልድይ ተሰርተዋል።
ማህበረሰቡ ዘና እንዲልና የተሟላ አገልግሎት እንዲያገኝ በማሰብ፤ 9 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ በአንድ ጊዜ 695 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችሉ 7 የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች (ፓርኪንጎች)፣ 4 የመሰብሰቢያ ስፍራዎች፣ 7 ፕላዛዎች እና 4 ፓቪሊዮኖች ተገንብተዋል። ለንግድና ለመዝናኛ አገልግሎት የሚውሉ 32 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ ሱቆች፣ 2 አንፊ ቲያትሮች፣ 10 ካፍቴሪያዎች፣ 7 የልጆች መጫወቻ ስፍራዎች፣ እንዲሁም 2 አነስተኛ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት ተካተውበታል።
በመጨረሻም፣ ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በታለመለት የጊዜ እና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ ሌሊት ከቀን የደከማችሁና የታተራችሁ ያስተባበራችሁና የደገፋችሁ በየደረጃው የምትገኙ አመራሮች፣ እንዲሁም ለመላው የአካባቢው ማህበረሰብ በከተማ አስተዳደሩ እና በራሴ ስም ላቅ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ምንጭ፡- አዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት | 914 |
| 11 | 没有文字... | 849 |
| 12 | ቱሪዝም፡ አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር!
ቀደም ሲል ትኩረት ተነፍጎት የቆየው የቱሪዝም ዘርፍ፣ አሁን ላይ የኢትዮጵያን ገጽታ በዓለም አቀፍ መድረክ ከመቀየሩ ባለፈ ከሀገሪቱ ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተሮች አንዱ በመሆን እየጎላ መጥቷል።
ከNBC ኢትዮጵያ ጋር በተደረገ ልዩ የአንድ ክፍል ቃለ ምልልስ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያ የዓለምን ትኩረት ለመሳብ፣ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ እና የኢኮኖሚ ሽግግሩን ለማፋጠን የዘርፉን ሰፊ አቅም እንዴት እየተጠቀመችበት እንደሆነ ያብራራሉ።
በዚሁ ማክሰኞ፣ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 2:30 ላይ ይጠብቁን።
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers | 1 032 |
| 13 | 没有文字... | 988 |
| 14 | ቱሪዝም፡ አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር!
ቀደም ሲል ትኩረት ተነፍጎት የቆየው የቱሪዝም ዘርፍ፣ አሁን ላይ የኢትዮጵያን ገጽታ በዓለም አቀፍ መድረክ ከመቀየሩ ባለፈ ከሀገሪቱ ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገት አንቀሳቃሽ ሞተሮች አንዱ በመሆን እየጎላ መጥቷል።
ከNBC ኢትዮጵያ ጋር በተደረገ ልዩ የአንድ ክፍል ቃለ ምልልስ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያ የዓለምን ትኩረት ለመሳብ፣ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ እና የኢኮኖሚ ሽግግሩን ለማፋጠን የዘርፉን ሰፊ አቅም እንዴት እየተጠቀመችበት እንደሆነ ያብራራሉ።
በዚሁ ማክሰኞ፣ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 2:30 ላይ ይጠብቁን።
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers | 1 |
| 15 | በጀሞ 3 አካባቢ የቦክስ ከልቨርት ግንባታ እየተከናወነ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም - የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ልዩ ስሙ ላፍቶ ሆስፒታል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፤ የጎርፍ አደጋ ስጋትን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል የቦክስ ከልቨርት ግንባታ እያከናወነ ይገኛል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ፤ በክረምት ወቅት ከጀሞ 3 አካባቢ የላይኛው ክፍል በከፍተኛ መጠን የሚመጣውን ጎርፍ በአግባቡ በመቀበል፣ በአቅራቢያው ወደ ሚገኝ ወንዝ ለማስተላለፍ፤ ነባሩን አስፋልት መንገድ በመቁረጥ 50 ሜትር ርዝመት ያለው የጎርፍ ማስወገጃ ከልቨርት ቦክስ ግንባታ እያከናወነ ይገኛል።
ቀደም ሲልም፤ በአካባቢው ይከሰት የነበረውን የጎርፍ ችግር ለመፍታት ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ማህበራትን በማሳተፍ 400 ሜትር ርዝመት ያለው ቦክስ ከልቨርት መገንባቱ ይታወሳል። | 1 294 |
| 16 | ሜካኒካል የአፈር ማረጋጊያ ማሽን በመጠቀም፣ እየተካሄደ የሚገኘው የመንገድ ጥገና፤ የተሻለ አፈፃፀም እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል
ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በዘመናዊ የጥገና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ውጤታማ የመንገድ ጥገና ስራ በማከናወን ላይ ነው።
አሁን ላይ ሜካኒካል የአፈር ማረጋጊያ ማሽን በመጠቀም የመንገድ ጥገና ከተካሄደባቸው አካባቢዎች መካከል፤ ከአየር ጤና - ኪዳነምህረት - አለም ባንክ የሚያገናኘው መንገድ ይገኝበታል።
በዚህ ሥፍራ የተካሄደው የመንገድ ጥገና በአጠቃላይ 1.6 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን ሲሆን፤ በዘመናዊ የመንገድ ጥገና ማሽን በመታገዝ መካሄዱ፤ የመንገዱን ጥንካሬና ዘላቂነት ለማሻሻል የሚያስችል ነው፡፡
ከሁለት ዓመታት በፊት፤ የጃፓን መንግሥት ባደረገው ድጋፍ፣ ወደ ሥራ የገባው ሜካኒካል የአፈር ማረጋጊያ ማሽን፣ በመንገድ ጥገና ወቅት ተቆርጦ ወደ ሌላ ቦታ ሊጓጓዝ የሚችልን የመንገድ ክፍል፤ ባለበት ሁኔታ ይበልጥ በማጠናከር ጥቅም ላይ እንዲውል በማድረግ፤ የጥገና ጊዜና ወጪ እንዲቀንስ አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ ይገኛል። | 1 272 |
| 17 | በቦሌ መድኃኒዓለም - ሀያት ሆስፒታል ኮሪደር፤ ተደራቢ አስፋልት የማልበስ ሥራ በመከናወን ላይ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን በራስ ኃይል እየገነባቸው ከሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በሆነው የቦሌ መድኃኒዓለም - ሀያት ሆስፒታል የኮሪደር ልማት ተደራቢ አስፋልት እያለበሰ ይገኛል።
የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ የራስ ኃይል ሰሜን መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ቢኒያም ዓለማየሁ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 1.03 ኪሎ ሜትር ርዝመትና በአማካኝ 22 ሜትር የጎን ስፋት አለው።
በእስከ አሁኑ የግንባታ ሂደት፤ የማስፋፊያ ሥራ በተካሄደበት የመንገዱ ክፍል፣ የመጀመሪያ ደረጃ የአስፋልት ንጣፍ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፤ የእግረኛ መንገድ ታይልስ ንጣፍ ሥራም ከ90 በመቶ በላይ ተከናውኗል።
አሁን ላይ ተደራቢ አስፋልት የማልበስ ሥራ በመከናወን ላይ ሲሆን፤ ቀሪ የግንባታ ስራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ የአስፋልት እና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ፣ የመንገድ ዳር አረንጓዴ ስፍራ እና 1,200 ካሬ ሜትር (70 መኪና ማቆም የሚችል) የመኪና ማቆሚያ ቦታ ያካተተ ነው።
የመንገድ ፕሮጀክቱ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ ለአካባቢው ተጨማሪ ውበት የሚያላብስ ከመሆኑም ባሻገር፤ ከመገናኛ ወደ አትላስ ለሚጓዙ አሽከርካሪዎች አቋራጭ መንገድ በመሆን አካባቢው ትራፊክ ፍሰት እንዲሳለጥ በማድረግ በኩል የጎላ ድርሻ እንደሚኖረው ይታመናል፡ | 1 307 |
| 18 | በተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄደ የሚገኘው የመንገድ ሀብት አጠባበቅ የግንዛቤ ማስጨበጫ እንደቀጠለ ነው
ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፡- የምዕራብ አዲስ አበባ መንገድ ኔትዎርክ ማኔጅመንት፤ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በአየር ጤና፣ በካራ፣ ስልጤ ሰፈር፣ አጃምባ፣ ዓለም ባንክ፣ ቤተል፣ የሺ ደበሌ እና ጦር ኃይሎች አካባቢዎች የመንገድ ሀብት አጠባበቅ የግንዛቤ ማስጨበጫ አካሄደ።
የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብሩ፤ የከተማዋ መንገዶች ከጉዳት እንዲጠበቁ እና ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ በማስቻል በኩል የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ ነው።
መንገድ የሁሉም ህብረተሰብ ክፍል የጋራ ሀብት በመሆኑ፤ በመንገድ መሠረተ- ልማት ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ህገወጥ ድርጊቶችን የመከላከል፣ መንገዶችን ከብልሽት እና ከማንኛውም ጉዳት በመጠበቅ ረገድ እያንዳንዱ ዜጋ የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ መልዕክት ተላልፏል።
ባለሥልጣን መስሪያ ቢቱ፤ በመንገድ ኔትዎርክ ማኔጅመንት የሥራ ክፍሎቹ አማካኝነት እያካሄ የሚገኘውን የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብር በማጠናከር፣ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የመንገድ ሀብት አጠባበቅ ስርዓት ለማጎልበት፤ ተመሣሣይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች እያካሄደ ይገኛል። | 1 026 |
| 19 | የኤድናሞል-ሃያ ሁለት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ ማጠናቀቂያ ምዕራፍ ተሸጋገረ
ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፡-የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ከኤድናሞል እስከ ሀያ ሁለት (ጎላጎል) እየተገነባ የሚገኘውን የመንገድ ፕሮጀክት በማጠናቀቅ ሙሉ በሙሉ ለትራፊክ ክፍት ለማድረግ እየተሰራ ነው።
በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ፣ የሰሜን መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ቢንያም አለማየሁ፤ የመጀመሪያ ደረጃ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ መንገዱ በከፊል ለትራፊክ እንቅስቃሴ ክፍት የተደረገ መሆኑን ጠቁመው፣ ቀሪ ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሮጀክቱ በኮሪደር ልማት እሳቤ የተቀረፀ መሆኑን እና የቴሌኮም፣ የኤሌክትሪክ፣ የመንገድ መብራት እና የዘመናዊ የትራንስፖርት ሥርዓት (ITS) መሠረተ ልማት ዝርጋታ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል።
ከዚህም በተጨማሪም የሳይክል መስመር አስፋልት ማጠናቀቂያ ሥራ እና የእግረኛ መንገድ የኮንክሪት ስታምፕ ሥራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።
ከኤድናሞል ወደ ሃያ ሁለት እየተገነባ የሚገኘው የመንገድ ፕሮጀክት በአጠቃላይ 2 ኪሎ ሜትር ርዝመት እና ከ20 እስከ 30 ሜትር የጎን ስፋት አለው። | 1 099 |
| 20 | የተፈታው የ10 ዓመት የህዝብ ጥያቄ የሳህሉ ጫካ ሰባራ ድልድይ ለነዋሪዎች የሰጠው እፎይታ
AMN- ሰኔ 19/2018 ዓ.ም
ከ10 ዓመታት በላይ የህዝብ ጥያቄ ሆኖ የቆየውና ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የሳህሉ ጫካ ሰባራ ድልድይ በአካባቢው የነበረውን እንግልት በማስቀረት ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጥ መሆኑን ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡
ሼህ ቃሲም አወል የልደታ አካባቢ ነዋሪ ሲሆኑ የሳህሉ ጫካ ሰባራ ድልድይ ግንባታ ተጠናቅቆ ከመመረቁ በፊት ወደ ተለያዩ ቦታዎች ለመንቀሳቀስና ወደ መስጂድ ለሶላት ለመሄድ አስቸጋሪ እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡
ለበርካታ ዓመታት ከባድ ችግር ውስጥ ቆይተናል የሚሉት ሼህ ቃሲም አወል፤ የሳህሉ ጫካ ሰባራ ድልድይ ግንባታ ተጠናቅቆ በመመረቁም ደስተኛ መሆናቸውን ያነሳሉ፡፡
ሌላኛዋ የልደታ አካባቢ ነዋሪ ትዕግስት ገብረመድህን በበከሉላቸው፤ ቦታው ለነብሰ ጡር እናቶች እንዲሁም ልጅ አዝሎ ለመሻገር አስቸጋሪ ነበር ይላሉ፡፡
ከዚህ በፊት የነበረው ድልድይ በመሰበሩ ምክንያት ለመንቀሳቀስ፣ ወደ ገበያ ለመሄድና ህሙማንን ወደ ጤና ተቋማት ለማድረስ ፈተና ሆኖባቸው እንደነበር በማንሳት ከዚህ በኋላ ግን የአዲሱ ድልድይ ግንባታ ስለተጠናቀቀ እናቶች እንደማይሳቀቁ ይናገራሉ፡፡
ከተማ አስተዳደሩም የነዋሪዎችን ጥያቄ አዳምጦ ድልድዩን ገንብቶ የነበረባቸውን የዓመታት ችግር በመፍታቱ ነዋሪዎች አመስግነዋል፡፡
የሳህሉ ጫካ ሰባራ ድልድይ ግንባታ አገልግሎት መስጠት፣ የተራራቁ ሰዎችን እንዲገናኙ ፣ አቅመ ደካማዎች ሳይቸገሩ እንዲሻገሩ፣ የእምነት አባቶች ሳይቸገሩ ምዕመናንን ማግኘት እንዲችሉና የከተማዋ ነዋሪዎችም ያለስጋት መንቀሳቀስ እንዲችሉ ያደርጋል ብለዋል፡፡
የሳህሉ ጫካ ሰባራ ድልድይ ለበርካታ አመታት በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ጥያቄ ሆኖ የቆየ በተለይም ለእናቶች ፈተና የነበረ ሲሆን | 1 206 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
