1 510
订阅者
无数据24 小时
-47 天
-930 天
帖子存档
1 510
#ስጠኝ_ስትሰጥ_አይቻለሁ
የእናቴ የሁልጊዜ ጸሎት ነች ።አንድ ቀን እንዲህ ብዬ ጠየኳት?
“የሽዬ ይችን ጸሎት ትወጃታለሽ ለምንድን ነው የምትደጋግሚያት?”
“አይ ልጄ ይስጠኝ ሲሰጥ.... አይቸዋለሁ”
“አምላክን ነው ?”
“እና አባትህን ነው ?” ስቄ ዝም አልኩ .....ከትንሽ ቆይታ በኋላ እንዲህ ተረከችልኝ
“ድሮ ነው ያኔ በደጉ ዘመን አንድ ድሃ ገበሬ ነበር። ጫካ ገብቶ እንጨት ሰብሮ ተሸክሞ ከተማ አምጥቶ ሸጦ ቤተሰቡን የሚያስተዳድር .... አንዴ ታዲያ እንደተለመደው እንጨቱን ሰብሮ ተሸክሞ ወደ ቤቱ ሊሄድ ሲል ይደክመውና አንዱ ዛፍ ስር ደገፍ ይላል ። ከቆይታዎች በኋላ ሙዳ ስጋ የያዘ ትልቅዬ አሞራ ሰውዬው ከተቀመጠበት ዛፍ ፊት ለፊት ካለ ዛፍ ያርፍና በማንቁርቱ ሊበላ ሲጣደፍ ድንገት ስጋው ይወድቃል ይሄኔ እጥፍጥፍ ብሎ ተኝቶ የነበረ አንድ ከሲታ ውሻ አይኖቹን ባለማመን ሙዳ ስጋ ው ላይ ዘሎ ይከመርና እየተጣደፈ መብላት ሲጀምር ያ ምስኪን ሰው ይመለከታል ወደ ሰማይ አንጋጦም እንዲህ ይላል።
.
“አይ እግዛብሄር አንተኮ ታላቅ ነህ .....በርሃብ ሊሞት የነበረውን ውሻ እንዲህ በጥበብ ትመግበው ....ስራህ ግሩም ነው። እግዚአብሄር ሆይ እንግዲህ ስትሰጥ አይቼሃለሁና ለኔም ስጠኝ ....ስጠኝ ስትሰጥ አይቼሃለሁ” ብሎ ተናግሮ እንጨቱን ትቶ ባዶ እጁን ቤቱ ይደርሳል ባለቤቱም ያየችውን ባለማመን “አንተ ሰውየ ቤት ውስጥ የሚበላ ነገር እንደሌለ እያወክ እንዴት የሚሸጥ እንጨት ሳትይዝ ትመጣለህ?” “አይዞሽ አትፍሪ ይስጠኝ ሲሰጥ አይቸዋለሁ” ብሎ ጠፍር አልጋ ላይ ወጥቶ ተኛ:: ሚስት በቁጣ እየለፈለፈች ቀኑ መሸ:: ሊነጋጋ ሲል በአቆማዳ የሞላ ጠገራ ብር ሰርቆ ሲሮጥ የነበረ ሌባ አባራሪዎቹ እየደረሱበት እንደሆነ ሲያውቅ ከሰውዬው ጎጆ በራፍ ላይ አስደግፎት ይሮጣል። በማለዳ ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ የምትወደው የምስኪኑ ገበሬ ሚስት የጎጆዋን በራፍ ስትከፍት በአቁማዳ የሞላው ጠገራ ብር ወደቤቷ ግልብጥ ብሎ ይደፋል።
.
ይሄኔ ሃይለኛ እንቅልፍ ላይ የነበረውን ባለቤቷን ጸሎትህን ሰምቶሃል ተነስ ብላ ቀሰቀሰችው ምስኪኑም ያየውን ባለማመን “እግዚአብሄር ሆይ አመሰግንሃለሁ .... አሁንም ስጠኝ ሰትሰጥ አይቸሃለሁ” አለ ይባላል ልጄ፡፡
ከ TikTok ገፅ ( Abeni 🥰 )
ሳነብ ካገኘውት
@ebuhbhr
@ebuhbhr
@tirrubel
1 510
Repost from ⛧ስሜትና ስሌት🫥 🤳✍️
ለምናልባት ቦታ......... 😌
ወላጅ እናትህ በድገት ብትከዳህ
ያፀድቃል ያልከው ሲኦል ቢነዳህ
ለፈውስ የዋልከው አጉል ቢጎዳህ
የስካሁን ውሎ
የስኮሁን ኑሮ
ቅዠት ነው ቢባል
አስበህዋል⁈
አለህ ወይ ትከሻ
አለህ ወይ መሸሻ
ህመም ማስታገሻ
አለህ ወይ ምንአልባት
ማረፍያ ምቶንህ በዛ ጭቅ ሰአት ?
ሙሉ አለም አትስራ አበጅለት ክፍተት
ልክ ሆነህ አትኑር አክልበት ስተት
ነፍስህ ይደናበር ዝግ ልብህን ስበር
አፍርስ ግርግዳውን ለመስኮትና በር
ሂወት ፀጋ ስትችር ያኔ እድትቀበል።
ቻናሉን ይቀላቀሉ፧።~👇👇👇👇👇
@love_words_qutes
@love_words_qutes
@love_words_qutes
https://t.me/love_words_qutes
1 510
<< ስትሞት ቀድመህ ምታደርገው ምንድነው >>
ስትል ጠየቀችኝ !
መጨረሻዬ ምንም ሆነ ምን ለአምላኬ የማቀርበው አንድ ተማፅኖ ይኖረኛል!
<< ምን የሚል ? >>
በማርያም አንድ ጊዜ መታቀፍን ! በማርያም አንድ ጊዜ መነካትን ! በማርያም አንድ ጊዜ ልጄ መባልን ! በማርያም አንድ ጊዜ መዳሰስን ! ተማፅኖዬ ይሄ ነው !
<< መንግሥትህን አውርሰኝ ትላለህ ብዬ ስጠብቅ ነበር ! >>
አቅፋ ለገሃነም እንደማትሰጠኝ አውቃለሁ! በእሷ ተዳስሼ ሲዖልም ብገባ ጠረኗ ገነት ሆኖ ያቆየኛል!
[ ጥሩቤል ]
@ebuhbhr
@ebuhbhr
@tirrubel
