1 094
订阅者
-224 小时
+17 天
-330 天
帖子存档
+1
✅ ዛሬ ከ17 አመት በታች አዳማ ሊግ አስረኛ ጫዋታችንን ትወደድ እናት ፕሮጀክትን ከጫዋታ ብልጫ ጋር በብዙ ጎል 7⃣ ለ 1⃣ ማሸነፍ ችለናል ።
✅ የጎሎቹ ባለቤት
በእምነት ስንታየሁ ⚽️
ውዳሴ ኤርሚያስ ⚽️
ኤርሚያስ አብዱልቃድር ⚽️
ነብዩ እስራኤል ⚽️
አብርሀም ንጉሴ ⚽️⚽️⚽️
✅ የጫዋታው ኮከብ
አብርሀም ንጉሴ
🏟 አዳማ አበበ ቢቂላ
👉 ማሸነፍ ልማድ ነው 💪💪💪
+2
✅ የ6ተኛና 8ተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሁሉም የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ከሰኞ 08/10/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 12/10/2018 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል !!!
👉 ለኮሌጅ አዳማ እግር ኳስ ማሰልጠኛ ተጫዋቾችም በዚህ ሳምንት የሚሰጠውን የምዘና ፈተና በአግባቡ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ለፈተና ብቁ በመሆን ፈተናውን በብቃት እንድትፈተኑ ስንል በትህትና እየገለፅን ። ተማሪዎች ከዚህ ቀደም ከነበረው የጥናት ዝግጅት በተሻለ መልኩ በማጥናት ፈተናችሁን በአግባቡ እንድትወጡ ይሁን !!!
🕊" መልካም ፈተና!!!"🕊
📆 ቅዳሜ 06/10/2018 ዓ.ም
🇪🇹 አዳማ 🇪🇬
⚽️ ኮሌጅ አዳማ እግርኳስ ማሰልጠኛ ⚽️
✅ የአዳማ ከተማ ከ17 አመት በተች ሊግ
አስረኛ ጫዋታችንን እሁድ 6 :00 ሰዓት ከትወደድ እናት ጋር የምንጫወት ይሆናል ።
🏟 አዳማ አበበ ቢቂላ
👉 ማሸነፍ ልማድ ነው 💪💪💪
ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ በ20 የተለያዩ ከተሞች የውስጥ ውድድር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
▼
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በታዳጊ እግር ኳስ ልማት ላይ እያወናወነ የሚገኘው ሥራ ከጅማሮው ውጤት እያስገኘ ይገኛል። ይህንን ተግባር በማጠናከር ጠንካራ መሠረት እንዲኖር ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
ፌዴሬሽኑ በያዘው የእግር ኳስ ልማት ፕሮግራም ዘንድሮ ስኬታማ ጅማሮ በማድረግ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድናችን ከ22 ዓመታት በኋላ ተሳትፎ ባደረገበት የአፍሪካ ዋንጫ እጅግ አስደናቂ ጉዞ በማድረግ ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ጫፍ መድረሱ የሚታወስ ሲሆን ይህንን ተስፋ ሰጪ ጅምር በወጥነት ለማስቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ፌዴሬሽኑ ካለፈው ዓመት ጀምሮ ከክልሎች ጋር የጋራ ሥምምነት በማድረግ የታዳጊዎች የውስጥ ሊጎች በክልሎች እንዲከናወኑ አቅጣጫ ቢያስቀምጥም ባለፈው ዓመት በሲዳማ ክልል እና አዲስ አበባ ከተማ፣ ዘንድሮ ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ እና ኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ብቻ የውስጥ ውድድር ሲከናወን ቆይቷል። ይህንን የውድድር መሠረት ለማስፋት በተያዘው ዕቅድ ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ በ20 የተለያዩ ከተሞች የውስጥ ውድድር እንደሚካሄድ ተገልጿል። ኢትዮጵያ በህዝብ ቁጥርም ሆነ በቆዳ ስፋት ሰፊ ሀገር እንደመሆኗ የለተያየ የአካል ብቃት እና የአጨዋወት ባህርይ ያላቸው ተጫዋቾችን ለማግኘት የሚያስችል እምቅ አቅም እንዳለ ይታመናል። ይህንን አቅም በአግባቡ ለመጠቀምም በመላ ሀገሪቱ አቅም ያላቸው አካባቢዎችን በመለየት የታዳጊዎች ውድድሮች ለማከናወን ታቅዷል።
ፌዴሬሽኑ ጥብቅ የሆነ የተጫዋቾች፣ የቡድኖች እና የውድድሮች ምዝገባ መስፈርት በማውጣት ስታንዳርዱን የጠበቀ ውድድር በየክልሉ የሚከናወን ሲሆን የፊፋ እግርኳስ ተሰጥኦ ልማት (FIFA TDS) ባስቀመጠው ሳምንታዊ የሦስት ቀን ልምምድ እና የሳምንቱ መጨረሻ ጨዋታዎችን ስታንዳርድ በማሟላት ታዳጊዎች በእድሜያቸው ሊያገኙ የሚገባቸው ተመጣጣኝ የጨዋታ መጠን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው። በተጨማሪም ከመኖርያ አቅራቢያቸው ሳይርቁ ስልጠና እና ውድድር ማግኘታቸው ትምህርት እና እግር ኳስን ጎን ለጎን ማስኬድ የሚያስችል ነው።
በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ የሚገኙ የክልል እና ከተማ መስተዳድሮች ከ16-20 ቡድኖችን የሚያሳትፍ የዙር ውድድር የሚያከናውኑ ሲሆን እያንዳንዱን ውድድር የሚከታተሉ የተሰጥኦ ልየታ ባለሙያዎች ፌዴሬሽኑ ለእያንዳንዱ ውድድር ይመድባል። በተጨማሪም ለተሳታፊ ቡድኖች እና ለአወዳዳሪ አካል የመጫወቻ ኳሶች እንዲሁም ለውድድር ማስፈጸምያ የበጀት ድጋፍ በፌዴሬሽኑ የሚሸፈን ይሆናል። የአሰልጣኞች ስልጠና እና ሌሎች ቴክኒካዊ ድጋፎችም በፌዴሬሽኑ አማካኝነት ይከናወናሉ።
ከክልላዊ ውድድሮች በኋላ ውጤታማ የሚሆኑ ቡድኖች ብሔራዊ ማጠቃለያ ውድድር የሚያከናውኑ ሲሆን ከውድድሮች በተሰጥኦ ልየታ ባለሙያዎች ለሚመለመሉ ታዳጊዎች ክልላዊ ማቆያ በማዘጋጀት ስልጠና ይሰጣል። በመጨረሻ ደግሞ ወደ ብሔራዊ ማቆያ በመግባት ልዩ ስልጠና ተሰጥቷቸው ለብሔራዊ ቡድን ብቁ የማድረግ ሥራ የሚከናወን ይሆናል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይህንን ውጥን ከግብ ለማድረስ ከክልል እና ከተማ አስተዳደርሮች ጋር ውይይት በማከናወን ላይ ሲገኝ በትናንትናው ዕለትም ከድሬዳዋ ከተማ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በውድድሩ አስፈላጊነት፣ በታዳጊዎች እግር ኳስ ልማት እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት ተደርጓል። በዚህ ውይይት ላይ ከፌዴሬሽኑ በተጨማሪ የከተማው ስፖርት ኮሚሽን፣ የከንቲባ ጽሕፈት ቤት እና የከተማው ትምህርት ቢሮ ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን በተቀናጀ ሁኔታ ውድድሮች እንዲከናወኑ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ዙርያ ውይይት ተደርጓል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ዳኛቸው ንግሩ (ዶ/ር) እንዲሁም የሜዲካል ዳይሬክተር እና የኢ/እ/ፌ ስትራቴጂክ አማካሪ ዶ/ር ሳሙኤል የሺዋስ ስለ ልማት ፕሮግራሙ፣ እስካሁን የታለፉባቸው ሒደቶች እና በዚህ ፕሮግራም ለማምጣት ስለታለመው አላማ ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።
በቀጣይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውድድር እንዲካሄዱ ከተመረጡባቸው ክልሎች እና የከተማ አስተዳደር እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ጋር የመግባቢያ ስምምነት በማከናወን ወደ ሥራ የሚገባ ይሆናል።
ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ በ20 የተለያዩ ከተሞች የውስጥ ውድድር እንደሚካሄድ ተገልጿል።
▼
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በታዳጊ እግር ኳስ ልማት ላይ እያወናወነ የሚገኘው ሥራ ከጅማሮው ውጤት እያስገኘ ይገኛል። ይህንን ተግባር በማጠናከር ጠንካራ መሠረት እንዲኖር ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
ፌዴሬሽኑ በያዘው የእግር ኳስ ልማት ፕሮግራም ዘንድሮ ስኬታማ ጅማሮ በማድረግ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድናችን ከ22 ዓመታት በኋላ ተሳትፎ ባደረገበት የአፍሪካ ዋንጫ እጅግ አስደናቂ ጉዞ በማድረግ ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ጫፍ መድረሱ የሚታወስ ሲሆን ይህንን ተስፋ ሰጪ ጅምር በወጥነት ለማስቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ፌዴሬሽኑ ካለፈው ዓመት ጀምሮ ከክልሎች ጋር የጋራ ሥምምነት በማድረግ የታዳጊዎች የውስጥ ሊጎች በክልሎች እንዲከናወኑ አቅጣጫ ቢያስቀምጥም ባለፈው ዓመት በሲዳማ ክልል እና አዲስ አበባ ከተማ፣ ዘንድሮ ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ እና ኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ብቻ የውስጥ ውድድር ሲከናወን ቆይቷል። ይህንን የውድድር መሠረት ለማስፋት በተያዘው ዕቅድ ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ በ20 የተለያዩ ከተሞች የውስጥ ውድድር እንደሚካሄድ ተገልጿል። ኢትዮጵያ በህዝብ ቁጥርም ሆነ በቆዳ ስፋት ሰፊ ሀገር እንደመሆኗ የለተያየ የአካል ብቃት እና የአጨዋወት ባህርይ ያላቸው ተጫዋቾችን ለማግኘት የሚያስችል እምቅ አቅም እንዳለ ይታመናል። ይህንን አቅም በአግባቡ ለመጠቀምም በመላ ሀገሪቱ አቅም ያላቸው አካባቢዎችን በመለየት የታዳጊዎች ውድድሮች ለማከናወን ታቅዷል።
ፌዴሬሽኑ ጥብቅ የሆነ የተጫዋቾች፣ የቡድኖች እና የውድድሮች ምዝገባ መስፈርት በማውጣት ስታንዳርዱን የጠበቀ ውድድር በየክልሉ የሚከናወን ሲሆን የፊፋ እግርኳስ ተሰጥኦ ልማት (FIFA TDS) ባስቀመጠው ሳምንታዊ የሦስት ቀን ልምምድ እና የሳምንቱ መጨረሻ ጨዋታዎችን ስታንዳርድ በማሟላት ታዳጊዎች በእድሜያቸው ሊያገኙ የሚገባቸው ተመጣጣኝ የጨዋታ መጠን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው። በተጨማሪም ከመኖርያ አቅራቢያቸው ሳይርቁ ስልጠና እና ውድድር ማግኘታቸው ትምህርት እና እግር ኳስን ጎን ለጎን ማስኬድ የሚያስችል ነው።
በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ የሚገኙ የክልል እና ከተማ መስተዳድሮች ከ16-20 ቡድኖችን የሚያሳትፍ የዙር ውድድር የሚያከናውኑ ሲሆን እያንዳንዱን ውድድር የሚከታተሉ የተሰጥኦ ልየታ ባለሙያዎች ፌዴሬሽኑ ለእያንዳንዱ ውድድር ይመድባል። በተጨማሪም ለተሳታፊ ቡድኖች እና ለአወዳዳሪ አካል የመጫወቻ ኳሶች እንዲሁም ለውድድር ማስፈጸምያ የበጀት ድጋፍ በፌዴሬሽኑ የሚሸፈን ይሆናል። የአሰልጣኞች ስልጠና እና ሌሎች ቴክኒካዊ ድጋፎችም በፌዴሬሽኑ አማካኝነት ይከናወናሉ።
ከክልላዊ ውድድሮች በኋላ ውጤታማ የሚሆኑ ቡድኖች ብሔራዊ ማጠቃለያ ውድድር የሚያከናውኑ ሲሆን ከውድድሮች በተሰጥኦ ልየታ ባለሙያዎች ለሚመለመሉ ታዳጊዎች ክልላዊ ማቆያ በማዘጋጀት ስልጠና ይሰጣል። በመጨረሻ ደግሞ ወደ ብሔራዊ ማቆያ በመግባት ልዩ ስልጠና ተሰጥቷቸው ለብሔራዊ ቡድን ብቁ የማድረግ ሥራ የሚከናወን ይሆናል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይህንን ውጥን ከግብ ለማድረስ ከክልል እና ከተማ አስተዳደርሮች ጋር ውይይት በማከናወን ላይ ሲገኝ በትናንትናው ዕለትም ከድሬዳዋ ከተማ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በውድድሩ አስፈላጊነት፣ በታዳጊዎች እግር ኳስ ልማት እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት ተደርጓል። በዚህ ውይይት ላይ ከፌዴሬሽኑ በተጨማሪ የከተማው ስፖርት ኮሚሽን፣ የከንቲባ ጽሕፈት ቤት እና የከተማው ትምህርት ቢሮ ተሳትፎ ያደረጉ ሲሆን በተቀናጀ ሁኔታ ውድድሮች እንዲከናወኑ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ዙርያ ውይይት ተደርጓል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ዳኛቸው ንግሩ (ዶ/ር) እንዲሁም የሜዲካል ዳይሬክተር እና የኢ/እ/ፌ ስትራቴጂክ አማካሪ ዶ/ር ሳሙኤል የሺዋስ ስለ ልማት ፕሮግራሙ፣ እስካሁን የታለፉባቸው ሒደቶች እና በዚህ ፕሮግራም ለማምጣት ስለታለመው አላማ ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።
በቀጣይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውድድር እንዲካሄዱ ከተመረጡባቸው ክልሎች እና የከተማ አስተዳደር እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ጋር የመግባቢያ ስምምነት በማከናወን ወደ ሥራ የሚገባ ይሆናል ።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
