S֮t֮r֮o֮n֮g֮ I֮m֮a֮n֮🇵🇸
❥ሁሌም ቢሆን ለዲንህ ትልቁን ቦታ ስጥ!! «ያ አላህ! ባልሰራበት እንኳ ወደ በጎ ነገር ያመላከተ ሰው የሚያገኘውን አጅር አታሳጣኝ፡፡» ቻናሉ ሚሰጣቸው አገልግሎቶች👇 🌟የ ታላቁ ዳኢ የመሀመድ ሀሰናት ሙሀደራዎች ✨ውቡ ድንቅ አና አስተማሪ ታሪኮች ኢስላማዊ አጀንዳዎች ,islamic qoutes &others 4 any comment at 👉 @strong_iman_bot
显示更多📈 Telegram 频道 S֮t֮r֮o֮n֮g֮ I֮m֮a֮n֮🇵🇸 的分析概览
频道 S֮t֮r֮o֮n֮g֮ I֮m֮a֮n֮🇵🇸 (@strong_iman) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 21 552 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 3 607,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 572 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 21 552 名订阅者。
根据 30 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -192,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 17.51%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.92% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 776 次浏览,首日通常累积 2 355 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 74。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“❥ሁሌም ቢሆን ለዲንህ ትልቁን ቦታ ስጥ!!
«ያ አላህ! ባልሰራበት እንኳ ወደ በጎ ነገር
ያመላከተ ሰው የሚያገኘውን አጅር አታሳጣኝ፡፡»
ቻናሉ ሚሰጣቸው አገልግሎቶች👇
🌟የ ታላቁ ዳኢ የመሀመድ ሀሰናት ሙሀደራዎች
✨ውቡ ድንቅ አና አስተማሪ ታሪኮች
ኢስላማዊ አጀንዳዎች ,islamic qoutes &others
4 any comment at 👉 @strong_iman_bot”
凭借高频更新(最新数据采集于 31 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
数据加载中...
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 31 七月 | 0 | |||
| 30 七月 | +4 | |||
| 29 七月 | 0 | |||
| 28 七月 | +3 | |||
| 27 七月 | 0 | |||
| 26 七月 | 0 | |||
| 25 七月 | +2 | |||
| 24 七月 | +2 | |||
| 23 七月 | +2 | |||
| 22 七月 | 0 | |||
| 21 七月 | 0 | |||
| 20 七月 | +3 | |||
| 19 七月 | +1 | |||
| 18 七月 | +1 | |||
| 17 七月 | 0 | |||
| 16 七月 | 0 | |||
| 15 七月 | 0 | |||
| 14 七月 | +14 | |||
| 13 七月 | 0 | |||
| 12 七月 | +1 | |||
| 11 七月 | 0 | |||
| 10 七月 | 0 | |||
| 09 七月 | +2 | |||
| 08 七月 | +4 | |||
| 07 七月 | +1 | |||
| 06 七月 | +4 | |||
| 05 七月 | 0 | |||
| 04 七月 | +10 | |||
| 03 七月 | 0 | |||
| 02 七月 | 0 | |||
| 01 七月 | 0 |
| 2 | ያልተፃፈው ታሪክ
ክፍል አስራአንድ
ማሂር ንግግሩን ጀምሯል እኔ አይን አይኑን እያየው በሙሉ ልቤ ላዳምጠው ተዘጋጅቻለው። "ሲሁዬ እስቲ በህይወትሽ ምን አተሽ ምን ጎሎሽ ያውቃል"? ንግግሩን በጥያቄ ነበር የጀመረው ደንገጥ ብዬ "እ ምንም አልሃምዱሊላህ ማሂሬ ሁሉ ነገሬን እናቴ ሞልታልኛለች ስለዚህ ምንም አልጎደለበበኝ" አልኩት ሳወራ አይን አይኔን እያየኝ ስለነበረ እየተንተባተብኩ ነው የመለስኩለት "ታድለሽ የኔዋ ስለዚህ አንቺ ኮ ሁሉም አለሽ በቃ"አለኝ አቀርቅሮ፤ እያለቀሰ እንደሆነ ያወኩት አጠገቡ ባለው ወረቀት ላይ እንባው ጠብ ሲል ነው ደነገጥኩኝ ምን ልበለው? ግራ አጋባኝ! አጠገቡ ሄጄ ቁጭ ብዬ "ማሂሬ ስለአንተ ምንም ነገር አላውቅም ግን አንድ ነገር ልንገርህ ከአሁን ቡሀላ ምንም አይነት የብቸኝነት ስሜት እንዲሰማህ አልፈልግም ሁሌም ቢሆን እኔ አለው እኔ ያንተ ነኝ የግልህ ነኝ" የሱ ልሆን ሳጠይቀኝ ተስማምቻለው ምን ሆኜ ነው ግን? " ማሂርን አባብላለው ብዬ የባሰ ሆድ አስባስኩት መሰለኝ ሳብ አድርጎ አቅፎኝ እንደ ህፃን ልጅ ተንሰቅስቆ አለቀሰ፤ አብሬው አለቀስኩ ማባበል፣ አይዞህ ማለት ስችል እንባው አስነባኝ፤ህመሙ አሳመመኝ፤ ሳይነግረኝ ቁስሉ፣ብቸኝነቱ፣ ስብራቱ ገባኝ። የኔው ማሂር አሳዘነኝ፤ እኔ ከሱ ባስኩኝ ትከሻው ላይ ተደፍቼ ተንሰቀሰኩኝ። ማሂር ከትከሻው ላይ ቀና አደረገኝ "የኔዋ ሲሁ በቃሽ አታልቅሺ ታምሜ አሳመምኩሽ አደል? አለኝ መልስ አልሰጠሁትም እስከዛሬ ስላላወኩት ተፀፅቻለው፤ ካለሱ የኖርኩባት እድሜዬ በከንቱ ያለፈ መሰለኝ፤እስከዛሬ በሰፈር ስመላለስ አንድ ቀን እንኳን ዞር ብዬ ያላየሁት ሰውዬ ዛሬ አለሜ ሆኖ ታየኝ ፤በጣም በጥቂት ቀናት ውስጥ ማሂርን ያለምንም ማንገራገር ልቤን ሰጥቼዋለው እሱ ምን እንደሚያስብ እንኳን ምንም አላውቅም።" ሱሁ" ሲለኝ ከሀሳቤ ባነንኩ የት ሄደሽ የኔዋ ምንድነው ምታስቢው "ምንም ምንም" አልኩት "ስሚኝ የኔዋ አንቺ ፣ሰሙ ፣ኡሚ እኔን እንደ አዲስ ህፃን ነው የፈጠራቹኝ ፤ከዘቀጠ ማንነቴ፤ ከብቸኝነቴ ፣ከስብራቴ ነው የጠገናቹኝ፤ግን ሲሁ ፈራለው፤ እንዳላጣቹ ፈራለው፤ ሁሉም ሰው ኮ የኔ ነህ፤ የትም አንሄድብህም፤ እንወድሀለን እያሉ ነወ ጥለውኝ የሄዱት" እንባው እየፈሰሰ ነው። "እናቴ፣አባቴ፣ ሀዩ፤ ሁሉም ሁሉም እኮ ይወዱኝ እንደነበር ነው የሚነግሩኝ አሁን ግን የሉም እና እናንተንም እንዳላጣቹ ፈራለው" በእንባ የታጀበ ንግግር " "አይዞህ የኔ ማሂ አታጣንም አንተ ጥለከን ካልሄድክ እኛ የትም አንሄድም ሁሌም ከጎንህ ነን አልኩት" ፊቱ ላይ ያለገደብ የሚወርደውን እንባ እየዳበስኩ ።ማሂር አሁን ተረጋግቷል ያለገደብ የሚወሩዱ የነበሩ እንባዎቹ ወደከረጢታቸው ተመልሰዋል ፤ከሰዓታት በፊት ሲያለቅስ የነበረው ማሂር አሁን እየሳቀ ነው፤ ሳቁ ህመምን ብቸኝነትን ያስረሳል ፤ሁሌም ሲስቅ ማየትን ተመኘው። ከአጠገቡ የበታተናቸውን ወረቀቶች እየሰበሰበ "በነገራችን ላይ የግጥም አፍቃሪ ነኝ እናም እሞካክራለው አንቺስ የኔዋ?" ቀና ብሎ አየኝ ስለግጥም አንድቀን እንኳን አስቤ ማላውቀው እኔ "አረ ግጥም" አልኩት በመገረም አይነት "ምነው አይመችሽም እንዴ?" " አረ ሳይሆን ቦታ ሰጥቼ አንብቤም አዳሜጬም አላውቅም ለዛ ነው" "እሺ ቆይማ እንደውም አንድ ለምን አላነብልሽም ብሎ የሰበሰበውኝ ወረቀት ድጋሚ በታተነው
እኔ ግን ቆይ ማነኝ?
ለመኖር ያልታደልኩ
ለሞት ያልተመረጥኩ
አለ አይሉኝ ነገር
ወይ አይቀብሩኝ ችግር
ሰው መሆኔን ማላምን ከሰው የተገኘው
ማን እንደሆነ ማላውቅ እኔን እዚህ ያስገኘው
አርግዘው ወለዱኝ ወይስ ከላይ ጣለኝ?
ከመንገድ ተገኘው ወይስ ተናፈጡኝ?
እኔ ግን ቆይ ማነኝ?
አለሁ ባይ የሌለኝ ተርቤ ስጠማ
ያፈቀረውን ሰው ልቤ የተቀማ
እኔ ማን ብሆን ነው?
ከሰው ተለይቼ ስቃዬ የበረታው?
በየትኛው ጥፋቴ እንደዚ ምቀጣው?
አምላክ ምን በድየው?
በሰፊው ሜዳ ላይ ብቻዬን የተወኝ?
ከሰው ተፈጥሬ ብቻዬን ያስቀረኝ?.......
በማሂር ግጥም ውስጥ ታሪኩ ቁልጭ ብሎ ይታያል ለኔ ግን ጎልቶ የታየኝ" ያፈቀረውን ሰው ልቤ የተቀማ" የምትለው ነበረች ማሂር ልቡ ውስጥ አንድ ሴት እንዳለች ልቤ ሙሉ ለሙሉ እርግጠኛ ሆኗል ያበደውም በሷ እንደሆነ ልቤን አሳምኜዋለው። እንባ እና እልህ ሲተናነቀኝ ይታወቀኛል፤ " እንዴ ሲሁ ለግጥሜ አስተያየት አሰጪም እንዴ?" "ያው ግጥም ብዙም ስለማላውቅ እኮ ምን ማለት እንዳለብኝ ስላላወኩ ነው" ብዬ አስቀየስኩት "እሺ የኔዋ ችግር የለውም በቃ እና ስለእኔ ትንሽም ቢሆን አወቅሽ አደል በግጥሜ ውስጥ" አለኝ "አዎ አዎ" አውቄያለው ማፈቅራት ሴት አለች እወቂው እያለኝ ነበር የመሰለኝ። ከዚ በላይ መቆየት አልፈለኩም "በቃ ደናእደር ማሂር እንቅልፌ እየመጣ ነው ጠዋት ስራ ስለምገባ ልተኛ" ብየው መልሱን ሳልጠብቅ ድንገት ብድግ አልኩኝ ማሂር በአካዃኔ ግራ ተጋብቷል "እሺ ደና እደሪ የኔዋ" ሲለኝ የባሰ አናደደኝ ጥየው የክፍሉን በር ወርውሬ በፍጥነት ወደክፍሌ ሮጥኩ አልጋዬ ላይ ተዘርሬ ተንሰቅስቄ አለቀስኩ ማሂርን ያጣሁት መሰለኝ፤ ያንቺ አደለሁም ያለኝ መሰለኝ፤ አለምን ጠላውሀት፤ አግኝቶ ማጣትን አወኩ፤ አመመኝ፣ ተሰበርኩ............
ይሄ ነበር የዛን ቀኑ ክስተት ከስራ አስቀርቶ ምግብ አስትቶ ክፍሌ ውስጥ የቆለፈኝ ስለእናቴ ግድ እንዳይሰጠኝ ያደረገኝን ያቺን ምሽት ጠላውሀት እራሴን ያጣሁበት የተረገመች ምሽት.............
ክፍል 12 ይቀጥላል .......
@strong_iman | 501 |
| 3 | ለሱ መንገር ትቼ ለሰው ነገርኩና
ገርቶ የነበረው ተመልሶ ጠና | 1 128 |
| 4 | ሰደቃ በላን ትመልሳለች በዟሂር ከከባድ አደጋ በትንሽ ብር ሰደቃ ተርፊአለው በቻላቹት መጠን ሰደቃ (መስጠትን) ተለማመዱ!🥰
የጁመዐ የሰደቃ ቤት ነው እየገባቹ የቻላቹት ሰድቁ👉 @sodeqah | 1 390 |
| 5 | ታላቅ ወንድም ማለት ሁለተኛ አባት ነው! | 1 620 |
| 6 | ታላቅ እህት ማለት ሁለተኛ እናት ናት | 1 884 |
| 7 | በዚች ውሸት አለም!
እንደ አልባሌ ቦታ የሰላም ቀጠና የለም።
በዛ እውነት አለም ሰላም አገኘሁበት ብለህ ለዘለልክበት አልባሌ ቦታ ሁሉ ሂሳብ ታወራርዳለክ!
በጉዟቹ ሁሉ ቆም እያላቹ አስቡ🥀🖤
@strong_iman | 2 214 |
| 8 | How the mosquito feels after biting me and absorbing my loyal, majestic, tall, nonchalant, , elite aura-filled DNA. | 2 155 |
| 9 | Due to some technical issue my comeback is postponed to 2027 | 2 089 |
| 10 | ✅@strong_iman | 2 252 |
| 11 | ያልተፃፈው ታሪክ
ክፍል አስር
✍️
.....................
ቀኔን ምሽት ያደረገው፤ምሽቴን ከእንቅልፍ ያራቀው፤ስራ እንድጠላ ያደረገኝ፤ ስለራሴ ፣ስለ ቤተሰቦቼ ማሰብ ትቼ ስለ አንድ ሰው ማሰብ እንድጀምር፤በእሱ ውስጥ እንድኖር፤ በእሱ ውስጥ እንድሞት፤ ስለሱ አስቤ እንዳለቅስ፤እሱን አስቤ እንዳለቅስ፤ እሱ ሲኖር የምኖር፤ እሱ ሲሞት የምሞት፤ ያህል እንዲሰማኝ ያደረገው እሱ ነው። "ማሂር" አባቴን በልጅነቴ ስለሆነ ያጣሁት ስለወንድ ልጅ ፍቅር በየትም በኩል መረዳት ለኔ ከባድ ነበር አባቴም፣ ወንድሜም፣ እናቴም፣ እህቴም፣ ዘመዴም ኡሚ ነበረች። ከጊዜያት ቡሀላ ግን ሰሙ የእህትነቱን ቦታ ተካችልኝ። አሁን ግን ስለወንድ ልጅ ፍቅር ማሰብ ጀምሬ እነሱን ረስቻቸዋለሁ
ማሂር ሁለመናዬን ከተቆጣጠረው እንደ ቀልድ ሳምንት አለፈው። ከሀኪምቤት የመጣ ቀን ማታ ሰሙ ወደቤት ልሂድ ብላ ወደቤቷ ሄደች ኡሚም ሰሞኑን እዚ ስለነበረች ልታስገድዳት አልፈለገችም ሸኝቻት ስመለስ ኡሚ "ሲሁ ትንሿን ክፍል ለማሂር አንጥፌለታለው በቃ ይረፍ አስገቢው ወደ ክፍሉ" አለችኝ እና ዊልቸሩን እየገፋው ወደ ክፍሉ አደረስኩት በሩ ላይ ስንደርስ "ደና እደሪ የኔዋ ሲሁ አመሰግናለው" ብሎኝ ከኔ ምንም መልስ ሳይጠብቅ ዊልቸሩን እየገፋ ወደክፍሉ ገባ። ውስጤ በድንጋጤም በደስታም ተሞላ "የኔዋ ሲሁ" የምትለዋ የማሂር ንግግር ውስጤን ሰርስራ ገብታለች ወደክፍሌ ገብቼ ማሂርን አለማሰብ አልቻልኩም አብሬው መቀመጥ ከሱ ጋር ማውራት ፈለኩኝ ግን እኮ መሽቷል ደሞ እንዴት ክፍሉ እገባለው ኡሚ ብታየኝ ምን ትለኛለች ምንድነው ምታስበው ከራሴጋር ሙግት ገጠምኩኝ ደሞስ ሄጄ ምን ፈልገሽ መጣሽ ቢለኝስ ምን እለዋለው እሱ ጋር ለመሄድ ምክንያቶችን ብፈልግም ሳይሳካልኝ ስለቀረ ለመተኛት ወሰኜ ቢጃማዬን ለመቀየር ተነሳሁ ሂጃቤን ሳወልቅ አንገቴ ላይ አድርጌው የነበረው የማሂር ተስቢህ ትዝ አለኝ እናቱ ቆይታበት የመጣችለት ህፃን ልጅ ያህል ነበር የፈነደኩት ተስቢሁን ከአኔገቴ ላይ አወለኩት እና ሂጃቤን አስተካክዬ ለበስኩት ሌላ ቀን እንደነገሩ ጣል አድርጌው ምወጣው ሂጃብ ዛሬ አደራረጉ ሁላ ጠፋብኝ መስታወት አጠገብ ቆሜ እራሴን ስመለከተው በጣም የተዝረከረኩ አስጠሊታ ሴት የሆንኩ መሰለኝ ልብሴን መቀየር ፈለኩኝ ባሏ ፊት ለመጀመርያ ጊዜ የምትቀርብ ሴት ትመስል መሽሞንሞን መቀባባት ፈለኩኝ ግን እሺ ከዛስ? ማሂር ተኝቶ ቢሆንስ ተተስቢሁን ተቀብሎኝ ዞር ብሎ ባያየኝስ? ግንኮ የኔዋ ብሎኛል! ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግራ ገባኝ ማሂር ቀን ባየኝ ልብስ እንዲያየኝ አልፈለኩም ብቀያይር ደሞ ለሱ ብዬ እንደሆነ ያውቅብኛል ምክንያቱም መሽቷል አ በዚ ሰዐት የትም እንደማልሄድ ያውቃል እንደዚማ ፊት አልሰጠውም ቀለል ያለ ልብስ ፍለጋ የቁምሳጥኑን ከፈትኩት ከተንጠለጠሉት ልብሶች መሀከል ኡሚ ሰሞኑን የገዛችልኝን ጁመዐ ለብሰዋለው ብዬ ያስቀመጥኩትን ሺቲ አየሁት ኡሚ እና ሰሙ ለብሼ አሳይቼያቸው በጣም እንደሚያምርብኝ ነግረውኛል ስለዚህ ይህን ልልበስ ምክንያቱም ማሂር የማታ ስለሚመስለው አይጠራራጠርም ብዬ ከልብስ ውስጥ ስቤ አወጣሁት ልብሴን ቀያይሬ ቀለል ያለ ዝነጣ ዘንጬ ኡሚ እንዳታየኝ እያልኩ ዱዐ እያደረኩ ከክፍሌ ወጣው ኮቴዬን አጥፍቼ ስወጣ ሳሎኑ ጭልምልም ብሏል የኔና የማሂር ክፍል ብዙም አይራራቅም የኡሚ ግን ወደኩሽናው መግቢያ ነው ወደማሂር ክፍል ከመሄዴ በፊት ኡሚ እንደተኛች ቼክ ላደርግ ወደኡሚ ክፍል ተራመድኩ ብትወጣ እንኳን ሚጠጣ ውሀ ፈልጌ ነው እላታለው ሺቲዬን እንዳታየው ረዘም ያለ የመኝታ ጋወን ደርቤበታለው ኡሚ እንደተኛች ለማጣራት የኩሽናውን በር ከፈትኩት ኡሚ ሌላ ቀን አደለም የኩሽናው በር ተከፍቶ ኮቴ ስትሰማ ነበር ብድግ ምትለው ዛሬ ግን ቀኑን ሙሉ ሽርጉድ እያለች ስለዋለች አልሰማችኝም የኡሚን መተኛት አረጋግጬ ወደ ማሂር ክፍል አመራው የማሂር ክፍል ደርሼ ማንኳኳት ብፈልግም ምን አልባት ኡሚ ልትሰማ ትችላለች ብዬ ስላሰብኩት የበሩን እጀታ ዝቅ አድርጌ ወደ ገባው ወደክፍሉ ስገባ ማሂር ወረቀቶቹን እያገላበጠ ነበር እና በድንጋጤ ነበር ወደበሩ የዞረው ድንጋጤውን ሳይ አንኳክቼ አለመግባቴ አሳፈረኝ" ውይ ሲሁ አንቺ ነሽ እንዴ ኡሚ መስላኝ ወላሂ እንዴት እንደደነገጥኩ" " ይቅርታ ማሂ እ... ተስቢህን ኮ ቅድም አንስቼ አንገቴ ላይ አድርጌው ሳልሰጥህ ረስቼው..... ተንተባተብኩ "ችግር የለውም የኔዋ ደሞኮ ነገ እንሂድ ልልሽ ነበር ተስቢሄን ልንፈልገው ወላሂ አመሰግናለው ሲሁዬ ብሎ ሊቀበለኝ እጁን ዘረጋ ተስቢሁን መስጠት አልፈለኩም ሁሌም በዚ ተስቢህ ምክንያት እያደረኩ ወደሱ መሄድ እፈልጋለው ግን በቃ ግዴታ መስጠት ስለነበረብኝ ይሀው ብዬ የዘረጋው እጁ ላይ አስቀመጥኩለት ተስቢሁን ሳመው እና በረጅሙ ተነፈሶ ወደኔ እየተመለከተ ለኔ ይሄ ተስቢህ ብዙ ትርጉም አለው እሺ ሲሁ ይሄ ተስቢህ ለኔ አደራ ነው" ስለተስቢሁ ማወቅ ፈለኩኝ ንገረኝ ማለት ግን አልደፈርኩም ማሂር ተስቢሁን አስቀምጦ አልጋው ላይ ወደበተነው ወረቀት አቀረቀረ። ነይ ተቀመጪ እንዲለኝ ውስጤ ቢፈልግም ከዚ በላይ መቆየቱ ለኔም ጥሩ አደለም ብዬ ስላሰብኩ ደና እደር በቃ ልሂድ "ደና እደሪ የኔ ሲሁ እንቅልፍሽ ካልመጣ ግን ብትቀመጪ ደስ ይለኛል ትንሸ ማወራሽ ነገር አለኝ" አለኝ። ያለምንም መግደርደር ነበር እሺ ያልኩት አጠገቡ እንድቀመጥ አልጋውን አጠገብ ያለውን ወረቀቶች ሰበሰበልኝ እኔግን አጠገቡ መቀመጥ አልፈለኩም ከክፍሉ ጠርዝ ላይ የነበረውን ወንበር ሳብ አድርጌ ፊትለፊቱ ተቀመጥኩ የበለጠ እንዳየው አይን አይኑን እያየው እንዳወራው ማሂር ንግግሩን ጀመረ .....
ክፍል አስራአንድ ይቀጥላል
@strong_iman | 2 300 |
| 12 | ያልተፃፈው ታሪክ ✍️
ክፍል ዘጠኝ
..............
የማሂር ቤት ፈራርሳለች ቦታው በብዙ ሳንቲሞች ተሞልቷል የወዳዳደቁ ብዙ ወረቀቶች እና ጥቂት ልብሶች ይታዩኛል ማሂር አልኩት ከውሀላው ሆኜ ከዊልቸሩ ወርዶ መሬት ላይ ዝርግፍ ብሎ ተቀምጧል እጁ የደረሰበትን ወረቀቶች እና ሳንቲሞች ይሰበስባል ስጠራው የሰማኝ አይመስለኝም ወደእሱ በጣም ቀረብኩኝ አይኖቹ እንባ ያጎርፋሉ ከወዳደቁት ነገሮች ውስጥ የሆነ ነገር እንደሚፈልግ ስለገባኝ ምንድነው እኔ ልፈልግልህ አልኩት ተስፋዬን ማንነቴን ፍቅሬን አለሜን ፈልጊልኝ? አለኝ መልስ ሳልሰጠው ሄጄ ተጠመጠምኩበት ማሂር አሳዘነኝ አብሬው አለቀስኩ ሁሌም ከአጠገቡ እንደማልለይ እጁን ይዤ ለራሴም ለሱም ቃል ገባሁለት። ልመንሽ ሲሁ?አለኝ ከየት የመጣ ድፍረት እንደሆነ ባላውቅም ጉንጩን ስሜ እመነኝ ማሂ ከገባህበት የተስፋ መቁረጥ ስሜት ከብቸኝነት እኔ አወጣሀለው ድጋሚ ተጠመጠምኩበት እሺ ያጣሁትን ፍቅር ስ ትመለሽልኛለሽ? መልስ ልሰጠው ቀና ስል ሰሙ መጣች ሲሁ ፣ማሂር ምንድነውየሆናቹት በአላህ? ምን ተፈጥሮ ነው? ለምንድነው ማሂር መሬት ላይ የተዘረገፈው? ሰሙ የኛን መልስ ሳትፈልግ ቆይ ሹፌሩን ልጥራው ብላ ወደ መኪናው በረረች ማሂርን ቀና ብዬ የስስት አየሁት አመሰግናለው አለኝ ከወደቁት ነገሮች ውስጥ የቻልነው ያህል ወረቀቶችን እና ልብሶችን ሰበሰብን፡ ሰሙ ሹፌሩን ይዛው መጣች ና ማሂርን ከተቀመጠበት አንስተው ዊልቸሩ ላይ አድርገው እየገፉ መኪና ውስጥ አስገቡት እኔም የማሂርን ንብረቶች ይዤ ተከተልኳቸው ማሂር ተቀምጦበት የነበረበት ቦታ ላይ የማሂርን ቡኒ ተስቢህ አገኘውሀት አሁን ልሰጠው ስላልፈለኩ አንገቴ ውስጥ አስገብቼ በሂጃቤ ሸፈንኩት ሰሙ መኪና ውስጥ እያለን ስለተፈጠረው ነገር ሁሉ እየጠየቀችን ነበር ማሂር ስለተፈጠረው ነገር እያስረዳት መንገዳችንን ቀጥለናል እኔ ግን ምንም መልስ አልሰጠውኋትም እኔ በሀሳብ በዚች ቅፅበት ውስጥ በኔና ማሂር መሀከል ስለተፈጠረው ነገር እያሰብኩ ነበር ምን ሆኜ ነው ግን ? በብዙ ጥያቄዎች እንደተሞላው እቤት ደረስን ኡሚ የሰፈሩን ሰው ሰብስባ ማሂርን በእልልታ እንደ ሙሽራ ተቀበለችው።
......................................................................
ማሂር ተቀይሯል አለባበሱ መልኩ ሁሉም ነገሩ በተቦጫጨቀ ልብስ የማውቀው ማሂር በጠቆረ ፊቱ ማውቀው ማሂር በሀዘኑ ሲስቅ በደስታው ሲያለቅስ ማውቀው ማሂር ዛሬ ፍፁም ሌላ ሰው ሆኗል በምድር ላይ ከሱ ሌላ ቆንጆ፤ ከሱ ሌላ አይንአፋር፤ ከሱ ሌላ ተናጋሪ፤ ከሱ ሌላ ተጫዋች፤ ከሱ ሌላ ቁምነገረኛ፤ከሱ ሌላ ወንድ ያለ እስከማይመስለኝ ድረስ ተቀይሯል! ሀሳቤ ሁላ ተቆጣጥሮታል የሚናገራቸው ቃላቶች ከባድ ሆነው ለመረዳት የሚቀሉ ቀልዶቹ አለ የተባለን ቀልደኛን የሚያስንቁ ናቸው ቁምነገሩ ግን ይከብዳል በመሀል ጣል የሚያደርጋቸው ንግግሮች ከአእምሮ በላይ ናቸው ።
አንቺ ልጅ ምን ሆነሻል ሰሞኑን ልክ አደለሽም እኮ! ታውቆሻል አ? ደሞ ከየት ያመጣሽው የቀን እንቅልፍ ነው ቆይ? ወይስ ከዚ ክፍል እንዳትወጪ ብሎ ያስጠነቀቀሽ ሰው አለ? አንቺ ሲሀም ተነሺ ኮ ነው ምልሽ!የኡሚ ድምፅ ነበር እንቅልፍ ባይወስደኝም ቀን ቀንም ቢሆን ከክፍሌ መውጣት ከተውኩ ሳምንት ሊሆነኝ ነው ስራም ቢሆን ገብቼ አላውቅም ኡሚን ላግዛት ነው በሚል ሰበብ ለሳምንት አስፈቅጃለው ሰሙንም ቢሆን አለቃችን አስጠልቶኛል ስራውን ለቅቄ ከኡሚ ጋር ከምጣላ እረፍት ልውሰድና እመለሳለው ለኡሚ ግን እንዳትነግሪያት ብዬ አስጠንቅቄያታለው ሰሙን ካወኳት ጀምሮ አንድም ቀን ዋሽቻትም ሆነ አታልያት አላውቅም ነበር አሁን ግን ማሂር አሸነፈኝ ብዙ ጊዜ ከስራ ስትመጣ ሁሉንም ነገር ልነግራት እወስን እና መልሼ እፈራለው እሷም ምታወራኝ ነገር እንዳለ ሁሌ ትነግረኛለች እኔ ግን ስለእኔ እና ስለማሂር ይሆናል ብዬ ስላሰብኩ በሰበብ እያደረኩ ቀጠሮዋችንን ሰርዛለው ደግሞ እሷም ብትሆን እንደ በፊት ብዙ እቤት መምጣት አቁማለች እኔም አልጠየኮትም ኡሚ ምንሆና ነው ተጣልታቹ ነው ብላ ስትጠይቀኝ አደለም ሰሞኑን ብቻዋን ስለሆነች ስራ ስለሚበዛባት እቤት አምጥታ ነው ምጨርሰው እዚ ደሞ አይመችም ብያታለው ባይዋጥላትም ብቻ ደና ትሁን ግድ የለም ብላ ተቀብላኛለች ኡሚ ስራ ማልገባው ባለፈው ሳምንት ስራ ስለበዛብን አለቃችን በተራ በተራ እረፉ እንዳለን ነው ምታውቀው። እሺ ኡሚ እነሳለው ትንሽ እራሴን ስላመመኝ ነው ኮ! ስንት ቀንሽ ነው እራሴን ስቲ?ነይ ተነሺ በይ ሀኪም ቤት እንሂድ! አለችኝ አሁን ይሻለኛል ትንሽ ተኝቼ ልነሳ ብያት በብርድልሴ ተጠቀለልኩ፤ እሺ ሌላው ቢቀር ተነሺና ይህን ልጅ አጫውቺው አረ ተይ ምን ይልሻል? እሺ ትንሽ ልተኛ እና እነሳለው አልኩ እኮ ደሞ አንቺ አለሽ አይደል ብያት እንቅልፍ እንዳሰከረው ሰው ብስጭጭት አልኩ ኡሚ ከኔጋ መጨቃጨቅ ከሰለቻት ቆይቷል አንቺ እኮ እኔን አልሰማም ካልሽ ቆይተሻል! ብላ በብስጭት በሩን ወርውራው ሄደች። የኡሚ መበሳጨት ከምንም ሳልቆጥር በሃሳብ ወደማሂር ተመለስኩ ኡሚ እንቅልፍ እንዳበዛው ታስብ እንጂ እኔ ግን ማሂር ከመጣበት ምሽት ጀምሮ የሰላም እንቅልፍ አልተኛሁም ማሂር የመጣ ቀን ማታ ተስቢሁን ልሰጠው ከመኝታ ቤት ወደሱ መኝታ ቤት ሄጄ ስለ ተፈጠረው ማሂር ስላለኝ ነገር ስለነገረኝ ታሪክ እያሰብኩ አይደለም እንቅልፍ ምግብም ኡሚ አንዳትቆጣ ለነገሩ ነው ምቀማምሰው ........
ክፍል አስር ይቀጥላል ......
@strong_iman | 2 169 |
| 13 | ጥጋብ ሲወጥረኝ የታናሽ ወንድሜን ቀብር ሄጄ እጎበኛለሁ ጥጋቤ ይለቀኛል..😢
አለ አንዱ😔
@strong_iman | 2 192 |
| 14 | So hawasaniyas ar u all right?
ዝናቡ እንዴት ነበር? there is no that much damege right | 2 305 |
| 15 | ቦሌ ሚካኤል አየር ማረፍያ አካባቢ ምትኖሩ ሴቶች ካላቹ በ @abdenest አናግሩኝ 🙏😊 | 175 |
| 16 | @Strong_iman | 2 822 |
| 17 | ያልተፃፈው ታሪክ
ክፍል ስምንት
.................
ቀኑ ጁመዐ ነው ማሂር ከሀኪም ቤት የሚወጣበት ቀን በመሆኑ በጠዋት መነሳት አለብን ስራ እንደማንገባ ለአለቃችን ነግረነዋል እሮብ ለት ከኡሚ ጋር አውርተን ማሂር እስኪሻለው እኛ ቤት እንዲሆን ከዛ ቡሀላ ደሞ ሰሙ እኛ ቤት መታ እሱ እዛ ሊኖር ተስማምተናል ሰሙ ዛሬም እኛ ቤት ነው ያለችው ወደ ቤቷ ከሄደች ሳምንት አልፏታል ኡሚ በጠዋት ጉድ ጉድ ማለት ጀምራለች ማሂር ሳይሆን ሙሽራ ሚመጣባት ነበር ምትመስለው መነሳታችንን እንኳን ልብ አላለችም ደና አደርሽ ኡሚ አልኳት ውይ ተነስታቹሀል እንዴ? በሉ ቶሎ ቁርሳቹን ብሉ ና ማሂር ጋ ሂዱለት ደሞ እንደይከፋው አለችኝ እህ ኡሚ ደሞ ገና 8 ሰዐት ነው እኮ ይወጣል የተባለው አይደል ሰሙ?የተነገርኩትን ለማረጋገጥ፡ አንገቷን በአውንታ ነቀነቀችልኝ አይይ ቢሆንም ልጄ የሀኪም ቤት ጣጣ አያልቅም እሱን እስክትጨራርሱ 10 ሰዐትም በመጣቹ ...........................
ሰአቱ 7:30 ሆኗል ማሂር ጋር ከገባን አራት ሰዐት አለፈን ሰሙ እንደገባን አንቺ ማሂር ጋር ቁጭ በይ እኔ መጨረስ ያለብንን ነገር ልጨርስ አለችኝ በሀሳቧ ተስማምቼ እኔ ማሂር ጋር ቁጭ ብያለው ሰሙም አልተመለሰችም ወረፋው በጣም ብዙ ነው ብቆይ እንኳን እንዳታስቡ ማሂርን አዳብሪው የሚል መልእክት ከሰአታት በፊት ስላከችልኝ አልተጨነኩም ሰኢድ ወጪውን ሙሉ ልኮልን ስለነበር ብር አልተቸገረንም ከገባው ጀምሮ ከማሂር ጋር ብዙም አላወራንም። ሊወጣ 30 ደቂቃ ቀርቶታል ሰሙ እስካሁን አልመጣችም ኡሚ እንዳለችው እስከ 10 መቆየታችን በቃ መቀመጡ በጣም አሰልችቶኛል ስልኬ ቻርጅ ስለዘጋ ሰሙን ማግኘት አልችልም የት ይሆን ያለችው ወጥቼ አልፈልጋት ነገር የሀኪም ቤቱ መግቢያና መውጫ ብዙ ነዉ ደሞ እሷ ስትመጣ እኔ ስሄድ ብንሸዋወድስ? ይህን እያብሰለሰልኩ
ሲሁ የሚል ድምፅ ከሀሳቤ አባነነኝ ማሂር ነበር የጠራኝ ወዬ አልኩት አጠራሩ አስደንግጦኛል ኡሚ እናንተ ቤት እንደማርፍ ነግራኛለች ግን እቤት ከመግባታችን በፊት ወደራሴ ቤት መሄድ እፈልጋለው እቤቴ?አልኩት በመደናገጥ አይነት ማሂር አጠያየቄ ስለገባው ፈገግ ብሎ እሺ ማዳበሪያዬ ጋር ከመልሱ ይልክ ፈገግታው አስደንግጦኛል ሌላ ቀን አይደርስም ? አሁን ይሁንልኝ በአላህ አጠያየቁ የህፃን ልጅ ነበር የሚመስለው እሺ እንደፈለክ ግን አንተ ከመኪና መውረድ ስለማትችል እኔ ምትፈልገውን ትነግረኛለህ እኔ አመጣልሀለው አልኩት፤በሀሳቤ ስማማት አልፈለገም ግን ደሞ ከመኪና ለመውረድ የግድ ሰው እንደሚያስፈልገው ያውቃል አይሆንም ቢል እኛን ማስቸገር ነው እሺ በቃ ወረቀቶች ናቸው ታመጪልኛለሽ ግን ሲሁ ልመንሽ? አለኝ ጥያቄው ያስደነግጣል እንደደበረው ስለገባኝ እኔ ምለው የሀገር ጉዳይ ነው እንዴ ብዬ ቀለድኩበት ፈገግ ብሎ ዝም አለ የማሂር ዝምታ ያስፈራል።! መጣው ሰሙን ልፈልጋት ብዬ ብድግ ብዬ ወጣው አወጣጤ እንዳልኩት ሰሙን ለመፈለግ ሳይሆን የማሂር ዝምታ አስፈርቶኝ ነው ወጥቼ ኮሪደሩ ላይ ቆምኩኝ ሳይታወቀኝ በሀሳብ ጭልጥ ብያለው የማሂር ፈገግታ ሲናገር እርጋታው የዝምታው ማስፈራት እና ማዳበሪያ ውስጥ ስላለው ወረቀት...... ሲሁ የሚለው የሰሙ ድምፅ ከሀሳቤ አባነነኝ እህ አልኳት የት ሄድሽ ደሞ ምነው ማሂርን ጥለሽው ወጣሽ እ ልፈልግሽ ወጥቼ ኮ ሰሙ የሆነ ነገር እንደሆንኩ ገብቷታል አትዋሺ ሲሁ ማሂር ምን ብሎሽ ነው አለችኝ ስለነገረኝ ነገር ነገርኳት እና ምን ችግር አለው በራይድ ስለሆነ የምንሄደው እዛው ጋር ስንደርስ እናወረደዋለን አለችኝ እሺ በቃ እንዳልሽ ጨረሽ አሁን አ እንሂድ አልኳት አይ ቆይ ትንሽ ይቀረኛል ሰኢድ ደውሎ ማሂርን አገናኚኜ ስላለኝ ነው የመጣሁት ብላኝ ወደ ውስጥ ገባች ተከትያት ገባው ሰሙ ማሂርን ከሰኢድ ጋር አገናኝታቸው በቃ አውርተው ሲጨርሱ ስልኬን ተጠቀሚበት እንዳይደብርሽ እኔ ልጨራርስ ትንሽ ነው የቀረኝ ብላኝ ሄደች ማሂር ከሰኢድ ጋር ለ30 ደቂቃ አወራ እንደዚ ለረጅም ደቂቃ ሲያወራ ለመጀመርያ ጊዜ አየሁት ንግግራቸውን በተመስጦ ነበር ስሰማ የነበረው አይደለም 30 ደቂቃ 1 ደቂቃ ያወራ አይመስልም እርግት ብሎ ነበር ሚያወራው እሺ ዋአለይክሰላም ሰያ እናወራለን በቃ ብሎ ስልኩን ዘግቶ ለኔ አቀበለኝ ተቀብዬው ሰሙ ስልክ ላይ ባፈጥም ስለ ማሂር ግን ማሰብ አላቆምኩም ነበር ላወራው ብፈልግም ግን ምን እንደማወራው ግራ ገብቶኛል ሰሙ ስላመጣችው ሀሳብ ልነግረው ፈለሰጊዪለው ግን ደሞ እንዳትነግሪው ቦታው ላይ ወስደን ነው ምናሳየው ብላ አስጠንቅቃኛለች እሱም አያወራም እኔም አላወራም በዝምታ ተውጠን ሁለታችንም በሀሳብ ነጉደናል ሲሁ ግን ልመንሽ? የሚለው የማሂር ጥያቄ ምንም ከጭንቅላቴ ሊወጣ አልቻለም ፤ ሰሙ 12:30 ሲሆን የማሂርን የሀኪም ቤት ጉዳይ ጨራርሳ መጣች ራይድ ደውለን ጠርተን ማሂርን በዊልቸር እየገፋው ሰሙ እቃዎቹን ሰብስባ ከሀኪም ቤት ወጣን የራይዱን ሹፌር ሰሙ ቀድማ ቦታውን ነግራው ስለነበር የማሂር ሸራ ጋር አቆመን ማሂር እየሆነ ባለው ነገር ግራ ተጋብቷል እሱ የገመተው ወደቤት እየሄድን እንደነበረ ነው ይሀው እንውረድ እና ምትፈልገውን ነገር ውሰድ አለችው ሰሙ ፊቱ በአንዴ በደስታ ተሞላ በሹፌሩ እገዛ ማሂርን ከመኪና አውርደን ዊልቸሩ ላይ አስቀመጥነው ዊልቸሩን እየገፋ ወደናፈቀችው ቤቱ ማዳበርያው ገባ የሚፈልገው ነገር ካለ እንድታግዢው ተከተይው አለችኝ እኔ ግን ሲሁ ልመንሽ ያለኝ ነገር ስላለ አይ ሰሙ አጋዥ ቢፈልግ ይጠራን ነበር እዚው እንጠብቀው አልኳት መኪና ውስጥ ተቀምጠን 30 ደቂቃ ሆኖናል ማሂር እስካሁን አልመጣም ልቤ በጣም ተጨንቆል ከሱ ሌላ ምንም ማሰብ አልቻልኩም አረ ይሄ ልጅ ቆየ አለ ሹፌሩ መልስ አልሰጠሁትም ተነሺ እስቲ ሲሁ እይው በአላህ አለችኝ ሰሙ እግሯ ላይ ያስቀመጠችው ነገር ስለነበረ ለመነሳት አልተመቻትም እሺ ቆይ ትንሽ 10 ደቂቃ እንየው እና እሄዳለው አልኳት ሰሙ ማሂር ልመንሽ ወይ እንዳለኝ ስላልነገርኳት እንጠብቀው ስላት ብስጭት አለች መልስ አልሰጠችኝም 10 ደቂቃው አልፎ 15 ደቂቃ ጠበቅነው እሺ አሁንስ አለች ሰሙ አሁን ግን ከሷ ይበልጥ ማሂር ለምን ቆየ የሚለው ነገር እኔን አሳስቦኛል 10 ደቂቃ እንዳለፈው ባውቅም ሂጂ እስኪሉኝ ነበር የጠበኩት እሺ መጣው በቃ ልየው ብዬ ከመኪናው ወረድኩ የምን መጣው ነው ይዘሽው ነይ እንጂ ኡሚኮ እየጠበቀችን ነው ነው አለችኝ ትዛዝ መሆኑ ነው እሺ እሺ አመጣዋለው ብዬ ወደ ማሂር ማዳበርያ ሄድኩ።የማሂር ማዳበርያ ጋር ስደርስ ያገኘሁት ግን ያልጠበኩት ነው ..........
ክፍል ዘጠኝ ይቀጥላል ........
@strong_iman | 3 038 |
| 18 | إِنَّهُمْ فِتْيَةٌ آمَنُوا بِرَبِّهِمْ وَزِدْنَاهُمْ هُدًى»
"እነሱ በጌታቸው ያመኑ ወጣቶች ናቸው፤ ቅኑን መንገድንም ጨመርንላቸው።" (ሱረቱል ካህፍ 18:13)
ባለፈው የቁርአን ማሰባሰብ ጥሪያችን ላይ በአካል ቁርአን ማበርከት የምትፈልጉ ቢሮአችን ማምጣት ትችላላችሁ ማለታችን ይታወሳል።
ዛሬ ግን አንድ ደስ የሚልና ክስተት እንንገራችሁ... አያት አካባቢ የሚኖር የ23 ዓመት ወጣት የቻናላችን ተከታታይ ፖስተራችንን አይቶ 29 አዳዲስ ቁርአኖች አሉኝ መጥታችሁ ተረከቡኝ ብሎ ደወለልን🤌
ይህ ወጣት ከዚህ ቀደም በሚያገኛት ደሞዙ ላይ እየቀነሰ ቁርአን እያስመጣ ቁርአን ለሚፈልጉ አካባቢዎች በአቅሙ ይልክ እንደነበርና በቅርቡ ግን የሚያደርስለት ሰው በመሞቱ ምክንያት ቁርአኖቹ እጁ ላይ ቀርተው እንደነበር ነግሮናል። ዛሬም በስራ ምክንያት ቢሮ እራሱ ይዞ ለመምጣት ባይመቸውም እቤቱ ድረስ ሄደን ስንቀበለው የትራንስፖርት ወጪ ሸፍኖልን ቁርአኖቹን አስረክቦናል።
ይህ ወጣት ከእኛ የፈለገው አንድ ነገር ብቻ ነው። "ዱአ አድርጉልኝ"😍
ያአላህ ይህንን ወጣት በወጣትነቱ እድሜው መልካም ስራን ጨማምሮ እንዲወድ አግራለት🤲
ያአላህ በስራው፣ በዕውቀቱ፣ በጤናውና በህይወቱ ላይ ታላቅ በረካን አውርድበት🤲
በሚሰራው ስራ ሁሉ ስኬትን፣ በረካንና ሰፊ ሲሳይን ይክፈትለት🤲
ባወጣው እና በለገሰው እያንዳንዷ ሰደቃ ምትክ አላህ በዱንያም በአኼራም ካሰበው ሪዝቅ በላይ አብዝቶ ይስጠው🤲
ያረብ እነዚህ 28 ቁርአኖች በተማሪዎች እጅ ገብተው በተቀሩ እና በተሸመደዱ ቁጥር ለእርሱ ፣ ለወላጆቹ እና ለቤተሰቦቹ ቀጣይነት ያለው የሶደቀቱል ጃሪያህ ምንዳ አድርግለት🤲
የልቡን መሻት ሁሉ አላህ ይሙላለት፤ ከክፉ ነገር ሁሉ አላህ ይጠብቀው🤲
ዋናውን ነገር ረስቼው😁
ያአላህ ለወንድማችን የአይኑ ማረፊያ፣ የልቡ ሰኪና የምትሆን፣ ለአኼራውና ለዱንያው የምትረዳው ሷሊህ ሚስት ወፍቀው🤩 (ለኔም ወፍቀኝ😁)
ትዳሩን የበረካ አድርግለት አላህን የሚፈሩ መልካም ልጆችንም ስጠው🤲
ከዚህ ቀደም ቁርአኑን ያደርስለት የነበረውንና ህይወቱ ያለፈውን ወንድማችንንም አላህ ረህመቱን ያውርድበት ጀነተል ፊርደውስን ይወፍቀው🤲
ይሄ የኔ ዱዓ ነው እስኪ እናንተም ዱዓ አርጉለት😍🫶 | 2 742 |
| 19 | ሰይድና ሩሚ (ቀደሰላሁ ሲረሁ) እንዲህ ይላሉ፦
« የእምነት ግብ የገዛ ነፍስ ላይ የበላይነትን መቀዳጀት እንጂ ሌሎች ሰዎች ላይ የበላይ ለመኾን አይደለም።»
ሕሊናቸውን ለኾኑ ቡድኖችና ጥቅማዊ ግንኙነቶች ያሰሩ ሰዎች ቢያደርጉ የሚመከረው ነገር ቢኖር ...
አንዳንድ ቀን ዝም ብለህ ሰው መኾንን መለማመድ አስፈላጊ መኾኑን ነው። በቃ የሰው ልጅ እኮ ውብ ፍጥረት ነው፣ ክቡር ነው! ስለ ሰውነት ስናወራ የአባታችን አደምን ፍጥረት ማስታወስ በቂ ነው። ለማዘን የጥቅስ ጋጋታ አያስፈልግም፣ ሰዎችን ለመርዳትና ከእነርሱ ጋር ለማውራት ትምሕርት አይፈልግም። የምንማረው፣ የምናነበው እኮ ሰው መኾን ምን ማለት እንደሆነ የበለጠ እንድንረዳ ነው።
አንዳንዴ አልገጠመህም ባለንጹሕ ሕሊናዎች የበለጠ ሰውነት ይገባቸዋል። ንጹሕ ሕሊና ወደ ፈጣሪ የምታደርገውን ጉዞ ያፋጥናል። አንዳንድ "ሓይማኖተኝነት" ደግሞ በተቃራኒው እምነት እንዳይኖርህ ሰው እንዳትኾን እንቅፋት ይኾናል። የምንቀራው፣ የምንሰግደው፣ ለኢስላም ቀን ከሌት የምንደነቁረው፣ መስጂድ የምንመላለሰው፣ አምልኮዎች ላይ አዘውትረን የምንመላለሰው፣ አላህ ደጃፍ የምንጠናው ልክ አደም በነበረበት የሰውነት ቁመና ጋር ለመድረስ ነው።
አንዳንድ ጊዜ ሁኔታዎችን ስንከታተል የለበስነው የጥቅም፣ የቡድን፣ ካባ ካለ አውልቆ በንጹህ ሰውነት መመለከት ከአላስፈላጊ ባሕርያት ይጠብቃል። እንደአማኝ በተለይም የኢስላም ሊቃውንቶች፣ ሙጃሂዶች፣ ለኢስላም ውለታ የሰሩ ሰዎች ሲያልፉ ለያየቶ መመለከት ያስፈልጋል።
ልብ በሉ ዑለማዎች በአመለካከት መስመራቸው ከሚለያቸው ሰዎች ዕውቀት ወስደዋል፣ የነርሱን ደጋግ ነገሮች እንደወረደ ለታሪክ ጽፈው ሰንደዋል።
አላህ ሰው ያድርገን🤲
የልቤ ወዳጅ🥀🖤
@strong_iman | 2 556 |
| 20 | ያስታመመ ሲቀብር አያለቅስም.. | 2 736 |
