ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 323 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 541 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 323 名订阅者。
根据 16 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 90,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.85%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.40% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 439 次浏览,首日通常累积 2 050 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 17 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 319
订阅者
+824 小时
+217 天
+9030 天
帖子存档
13 323
የዲሪ - ማሻ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው የዲሪ - ማሻ ምዕራፍ አንድ ጊምቦ - ኪሎ ሜትር 61+960 የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከፍተኛ የፌደራልና የክልል የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተጀምሯል።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የኢፌዴሪ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ጫልቱ ሣኒ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የኢፌዴሪ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ወ/ሮ ሔለን ደበበ እና የክልሉ፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።
የከተማና መሰረተልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ጫልቱ ሳኒ መንግስት ጠንካራ መሰረተ ልማት ለሀገራችን እድገትና ብልፅግና ወሳኝ መሆኑን ተገንዝቦ ተጨባጭ ውጤት በማምጣት ላይ ነው ብለዋል።
ሚኒስትሯ አክለውም ይህም ፍትሀዊ የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በደቡብ ምዕራብ ክልል የተጀመረው የዲሪ-ማሻ መንገድ የሚያመላክት ነው ብለዋል። ይህንንም ትልቅ የልማት ዕቅድ ዕውን ለማድረግ የክልሉ ህዝብና የባለድርሻ ትብብር እንዲያደርጉ አሳስበዋል ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶክተር ነጋሽ ዋጌሾ በበኩላቸው በዛሬው እለት ዳግም የተጀመረው የዲሪ ማሻ መንገድ የዘመናት የህዝብ ጥያቄ ምላሽ ያገኘበት መሆኑን ጠቅሰው መንግስት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ በሰነቀው ራዕይ የመንገድ ተደራሽነትን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ የሚገኝ መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል ።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ሀብት ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አለማየሁ አየለ የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ ያለውን ከፍተኛ ፍይዳ ከግምት ውስጥ በማስገባት በታሰበለት ጊዜና የጥራት ደረጃ ገንብቶ ለማጠናቀቅ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
61 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው ይኸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የበርካታ አመታት የመሰረተ ልማት ጥያቄን ምላሽ ከመስጠቱም ባሻገር የከተማዋን ዕድገት በማሳለጥ ረገድ ሚናው ከፍተኛ ነው።
ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚውለውን 6,281,190,550.95 /ስድስት ቢሊየን ሁለት መቶ ሰማንያ አንድ ሚሊየን አንድ መቶ ዘጠና ሺህ አምስት መቶ ሃምሳ ብር ከዘጠና አምስት ሳንቲም ገንዘብ በፌደራል መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡
መንገዱ ካለው ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ይሆናል።
ግንባታውን የሚያካሂደው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ራስ ሃይል ነው።
የመንገድ ግንባታው በወረዳ ከተማ 26 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እና በገጠር ከ8-10 ሜትር የጎን ስፋት የለዉ ሲሆን አጠቃላይ ግንባታዉም በ 3 (ሶስት) ዓመት ዉስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል።
ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የግብርና ውጤቶች ቡና ፣ ማር እንዲሁም የእንስሳት ምርቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማውጣት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ያደርጋል።
በተጨማሪም ለአካባቢው የግብርና ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ በፕሮጀክቱ አካባቢ የሚገኙ ከፍተኛ የእርሻ እምቅ ቦታዎችን ተደራሽ ለማድረግ እና የኢኮኖሚ ልማትን ለማሳደግ ያስችላል።
ከዚህም ባሻገር መንገዱ በሚገነባበት አካባቢ ለሚገኙ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ የኡፋ፣ የጌቲያ (አዲስ አምባ) ፣ የኩቲ ፣ የመኒያ ፣ የጤና ፣ የዱማ ፣ የኮቤቺ ፣ የሳጃ ፣ የጎጀብ ፣ የሜዳቦ እና የኮንዳ ከተሞችን በአስፋልት መንገድ የሚያስተሳስር ነዉ።
የዲሪ - ማሻ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም በስራ ተቋራጭ የአቅም ውስንነት ምክንያት ተቋርጦ እንደነበር የሚታወስ ነው ።
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 323
የኢተያ - ሮቤ - ሴሩ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 85 ነጥብ 4 በመቶ ደረሰ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 16፣ 2017 (ኢመአ):- 75.6 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የኢተያ - ሮቤ ምዕራፍ አንድ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 85 ነጥብ 4 በመቶ ደርሷል፡፡
በአሁኑ ወቅት በመንገዱ ግንባታ ላይ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የድሬኔጅ ስራዎች፣ የስትራክቸር ስራዎች፣ የሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣የቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ሲሆን ከዚህም መካከል 68 .43 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተገባድዷል፡፡
የፕሮጀክቱን ግንባታ በተያዘው በጀት አመት እንዲጠናቀቅ ለማስቻል በሥራ ተቋራጩ ላይ የተስተዋሉ ውስንነቶች እንዲቀረፉ ለማድረግ ብሎም ሥራዎች እንዲፋጠኑ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ክትትልና ድጋፍ በማድረጉ በመንገዱ ክልል ውስጥ የሚገኙ የካሳ ክፍያዎች በአብዛኛው እንዲፈጸሙ ተደርጓል፡፡
ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ሬል ዌይ ቁጥር 3 ኢንጅነሪግ ግሩፕ (CRTG) የተባለው አለም አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ሲሆን የኘሮጀክቱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢንጅነሪግ ኮርፖሬሽን፣ የትራንስፖርት ዘርፍ ነው፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ የጎን ስፋት በወረዳና በከተማ ከ 19 – 21 ሜትር (የአግረኛ እና የውሃ ማፈሰሻ ጨምሮ) ፣ በቀበሌ 15 ሜትር (የውሃ ማፈሰሻ ጨምሮ) ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር (የመንገድ ትከሻን ጨምሮ) ያለው ነው፡፡
መንገዱ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም አኳያ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በአስፋልት ኮንክሪት እየተገነባ ይገኛል፡፡
የመንገዱ መገንባት በአርሲ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የሄጦሣ፣ የሎዴ ሄጦሳ፣ የዲክሲስ እና ሮቤ ወረዳዎችን እንዲሁም ቦሩ ሌንጫ፣ የጎበያ፣ የአርብ ገበያ ፣ የእድገት ፋና እና የቡላላ ቀበሌዎችን በማስተሳሰር ምቹ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር ያስችላል፡፡
በተጨማሪም በአካባቢው ላይ የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ መሃል አገር እንዲወጣ በማድረግ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 323
የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት የኢ መ አ የምርምር እና የሥልጠና ማዕከላትን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 09፣ 2017 (ኢ መ አ):- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ መሠረተ- ልማት እና ትራንስፖርት ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አባላት የኢ መ አ የመንገድ ምርምር እና የስልጠና ማዕከላትን ጎብኝተዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ እሸቱ ተመስገን (ዶ/ር)፤ የመንገድ ዘርፉን በዕውቀት፣ በቴክኖሎጂ እና በብቁ ባለሞያ በመምራት ረገድ ማዕከላቱ እያደረጉት ያለው አስተዋጽዖ የሚበረታታ ነው ብለዋል።
ማዕከላቱን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ዘመኑ የደረሰበትን ወጪ ቆጣቢ የቴክኖሎጂዎች ውጤቶችን መተግበር ይኖርበታልም ብለዋል።
በዚህ ረገድ የሥልጠና ማዕከሉን ወደ ሮድ አካዳሚ ለመቀየር የቀረበው ፍኖተ-ካርታ የመንገድ ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ ትልቅ ሚና ይኖረዋል።
ለመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም መሻሻልም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራህማን (ኢ/ር)፤ ማዕከላቱን ይበልጥ በማዘመን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል እየተሠራ እንደኾነ ተናግረዋል።
የመንገድ ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ በኩልም የምርምር እና የሥልጠና ማዕከላቱ የማይተካ ሚና ይኖራቸዋል ብለዋል።
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 323
የአደሌ - ግራዋ የአስፋልት መንገድ ሥራ ፕሮጀክት 84 በመቶ ደረሰ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2017 (ኢ መ አ) ፡- 53 ኪሎሜትር ርዝማኔ ያለው የአደሌ - ግራዋ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ሥራ ፕሮጀክት 84 በመቶ ደርሷል፡፡
በአሁኑ ወቅት በመንገድ ፕሮጀክቱ ላይ የቤዝ ኮርስ ፣የአስፋልት ንጣፍ እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች እየተከናወኑ የሚገኙ ሲሆን ፣ በእስካሁኑም 32 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራም ለማከናወን ተችሏል፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቱ ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንፃር በተቀመጠለት ጊዜ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል ክትትል እየተደረገበት ይገኛል፡፡
ግንባታው እያከናወነ የሚገኘው የቻይናው ሂቤ ኮንስትራክሽን ግሩፕ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ ሲሆን፣ የማማከሩን ሥራ የሚሠራው ጎጎት አማካሪ መሐንዲሶች ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ነው፡፡ ለግንባታው የተመደበው 1,436,300,000.00 (አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰላሳ ስድስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሺህ ብር) በፌደራል መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡
መንገዱ በወረዳ እና በከተማ 14 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር አጠቃላይ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡
የመንገዱ መገንባት በአደሌ እና በግራዋ ከተሞች መካከል የሚገኙ ወረዳዎችንና ቀበሌዎችን ከማስተሳሰር ጎን ለጎን በሥፍራው የሚገኙ የበቆሎ ፣ የማሽላ ፣ የገብስ ፣ የስንዴ እና ሌሎች በአካባቢው የሚመረቱ የግብርና ውጤቶችን ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ይሆናል ።
ከዚህም በተጨማሪ በሥፍራው የሚገኘውን የልጅ እያሱን ቤተ-መንግሥት ለሚጎበኙ ቱሪስቶች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 323
የጎንደር - ሁመራ ከባድ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክት ተጀመረ
አዲስ አበባ ሚያዚያ 1 ፣2017 (ኢ መአ):- ሁለት ዞኖችን የሚያገናኘው የጎንደር - ሁመራ የመንገድ ጥገና ፕሮጀክት ተጀምሯል፡፡
የጥገና ፕሮጀክቱ የአፈር ሥራ፣የቆረጣ ሥራ ፣የሙሌት ሥራ ፣ የመንገድ ትክሻ ስራዎች ፣የምርጥ ገረጋንቲ (የሰብ ቤዝ)፣የተፈጨ ጠጠር ማንጠፍ ስራ (Base course)፣ የአለት ድንጋይ ሙሌት (Rock fill) የድልድይ/ፉካና የዉሃ ማፋሰሻ ስራዎች እንዲሁም የአስፓልት ስራዎች (Bituminous Surfacing) ስራዎች ያካተተ ነው፡፡
አሁን ላይ የጥገናው ሥራ እንዳይስተጓጎል ለማድረግም የተለዋጭ መንገድ ተሰርቶ የጥገናው ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡
ጥገናው የሚካሄድለት ይህ መንገድ ባጠቃላይ 4 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው ሲሆን ያለው የጎን ስፋቱ 7 ሜትር ነው፡፡
ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚውለው 29,000,000 ብር የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ሲሆን ጥገናው በጎንደር ዲስሪክት አማካኝነት እየተከናወነ በመሆኑ በተያዘለት እቅድ መንገዱን ጠግኖ ለማጠናቀቅም በትኩረት እየተሰራ ነው ፡፡
የጎንደር መንገድ አዉታር ማኔጅመንት ቅርንጫፍ ቢሮ የማማከሩን እና የቁጥጥሩን ሥራ በመስራት ላይ ነው፡፡
የመንገድ ጥገናው መደረጉ በሰቲት ሁመራ እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ብሎም በትክል ዲንጋይ ፣ በሳንጃ ፣ በጠገዴ ፣በቃፍቲያ ወረዳዎች መካከል ምቹና ቀልጣፋ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር ያስችላል፡፡
በተጨማሪም በአካባቢው በስፋት የሚመረቱ የሰሊጥ ፣የኑግ ፣የማሽላ እና የጥጥ ምርቶችን ወደ ገበያ ለማውጣት በማስቻል የግብይት እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን ለማስፋፋት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ይሆናል፡፡
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 323
የነቀምት -ቡሬ፣ ክፍል 1፡ ነቀምት - አንገር ጉቲን -አንዶዴ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ውስጥ የሚገኘው 86.1 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የነቀምት - አንገር ጉቲን -አንዶዴ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን ነቀምት ከተማ አድርጎ እስከ አንዶዴ የሚዘልቅ ነው።
በእስካሁኑ የመንገድ ግንባታ ስራ የአስፋልት ንጣፍ (21 ኪ.ሜ) አፈር ቆረጣ እና ሙሌት (25.23 ኪ.ሜ)፣ የድሬኔጅ ስራዎች( 69%)፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ (22 ኪ.ሜ)፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ ( 21 ኪ.ሜ) እንዲሁም በርካታ የስትራክቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,948,446,483.18 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ አርባ ስምንት ሚሊዮን አራት መቶ አርባ ስድስት ሺህ አራት መቶ ሰማንያ ሶስት ብር ከአስራ ስምንት ሳንቲም) ብር የሚሸፈነው በአለም ባንክ ነው ።
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው ቾንግኪንግ ኢንተርናሽናል ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ሬናርዴት ከዩናይትድ አማካሪ መሐንዲሶች (ዩኒኮን) ኃ.የተ.የግ.ማ. ጋር በጣምራ በመሆን እያከናወኑት ይገኛሉ።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል።
የዚህ መንገድ ግንባታ መጠናቀቅ ከዚህ በፊት የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍየ የአካባቢው ነዋሪ በተመጣጣኝ ዋጋ ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታን ይፈጥራል።
አርሶ አደሮች ምርታቸውን ካለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ማዕከላዊ እና የውጭ ገበያ በማውጣት አምራችና እና ሸማቾችን በቀላሉ በማገናኘት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፡፡
በተጨማሪም የነቀምት፣ ጉዳቱ ፂገ፣ ሁከ፣ አንገር ጉቲንና አንዶዴ ከተሞችን በአስፋልት ኮንክሪት መነገድ የሚይገኛኝ ይሆናል።
የመንገድ ግንባታው በዞን እና በወረዳ 21.5 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር እና በገጠር 7 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ ነው የሚገኘው ።
13 323
የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ በመልካም የአፈፃፀም ደረጃ ላይ ነው
አዲስ አበባ መጋቢት 26 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኮምቦልቻ ከተማ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘው የኮምቦልቻ ከተማ የአስፋልት ኮንክሪት ተለዋጭ የመንገድ ግንባታ በመልካም የአፈፃፀም ደረጃ ላይ ይገኛል።
ለመንገዱ ግንባታ 1,138,807,808 (አንድ ቢሊዮን አንድ መቶ ሰላሳ ስምንት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሰባት ሺህ ስምንት መቶ ስምንት ብር ) ወጪ በፌደራል መንግስት ተመድቧል፡፡
ግንባታው በሀገር በቀሉ ዮንአብ ኮንስትራክሽን እየተከናወነ የሚገኘውና 7 ነጥብ 58 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ይህ መንገድ የመንገድ ትከሻን እና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ 20.6 ሜትር አጠቃላይ የጎን ስፋት ያለው ነው፡፡የመንገዱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ሃገር በቀሉ ኢትዮ ኢንፍራ ኢንጂነሪንግ እያከናወነው ይገኛል ፡፡
አሁን ላይ ከመንገድ ፕሮጀክቱ 24.7 በመቶ የሚሆነው ሥራ የተገባደደ ሲሆን የአፈር ጠረጋ ፣ የአፈር ቁፋሮ፣ የአፈር ሙሌት፣ የማፋሰሻ ቱቦ በማምረት በመንገዱ ላይ የመግጠም ፣የሰብ ቤዝ ፣የድልድይ እና የደጋፊ ግንብ ስራዎች በሂደት ላይ ያሉ ሲሆን በእስካሁኑም የአራት ድልድይ ስራዎችን ማጠናቀቅ ተችሏል።
በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ወቅት የጸጥታ ችግር፣የወሰን ማስከበር ችግር ፣የካሳ ክፍያ በወቅቱ አለመከፈል፣ ከዚህም ጋር ተያይዞ ለስራ ተቋራጩ ለስራ በቂ የሆነ የመስሪያ ቦታ ከንብረት ነፃ በማድረግ መስጠት አለመቻሉ፣ ለምርጥ ድንጋይ ማምረቻ የሚሆን ቦታ (Quarry Site)አለመገኘቱ፣ የሲሚንቶ፣ ነዳጅ፣ብረት እና ሌሎች የግንባታ ግብአቶች እጥረት አጋጥመዋል።
ችግሩን ለመቅረፍ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኮምቦልቻ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት በኩል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሠራ ይገኛል፡፡
የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ ቁጥራቸው በርከት ያሉ ከባድ ተሸከርካሪዎች ወደ ከተማው ሳይገቡ ለማስተናገድ እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ግብዓቶች ምርት ማውጫ በመሆን ከፍተኛ ጠቀሜታ የሚሰጥ በመሆኑ በከተማዋ ውስጥ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ በከፍተኛ ደረጃ ይቀርፋል ተብሎ ይጠበቃል።
የመንገድ ኘሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በአካባቢው የሚገኙ የመስተዳድር አካላት፣ የክልሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ትብብር እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል፡፡
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
