uk
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Відкрити в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 13 323 підписників, посідаючи 1 756 місце в категорії Транспорт та 2 541 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 13 323 підписників.

За останніми даними від 16 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 90, а за останні 24 години на 8, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 40.85%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.40% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 439 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 050 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 17.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 17 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Транспорт.

13 319
Підписники
+824 години
+217 днів
+9030 день
Архів дописів
የዲሪ - ማሻ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ በደቡብ  ምዕራብ ኢትዮጵያ  የሚገኘው የዲሪ - ማሻ  ምዕራፍ  አንድ ጊምቦ - ኪሎ ሜትር 61+960 የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከፍተኛ የፌደራልና የክልል የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት  ተጀምሯል። በመርሃ-ግብሩ  ላይ የኢፌዴሪ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ጫልቱ ሣኒ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የኢፌዴሪ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ወ/ሮ ሔለን ደበበ እና የክልሉ፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል። የከተማና መሰረተልማት ሚኒስቴር  ሚኒስትር ክብርት ጫልቱ ሳኒ መንግስት ጠንካራ መሰረተ ልማት ለሀገራችን እድገትና ብልፅግና ወሳኝ  መሆኑን ተገንዝቦ ተጨባጭ ውጤት በማምጣት ላይ ነው ብለዋል። ሚኒስትሯ አክለውም ይህም ፍትሀዊ የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በደቡብ ምዕራብ ክልል የተጀመረው  የዲሪ-ማሻ  መንገድ የሚያመላክት ነው ብለዋል። ይህንንም ትልቅ የልማት ዕቅድ ዕውን ለማድረግ የክልሉ ህዝብና የባለድርሻ  ትብብር እንዲያደርጉ አሳስበዋል ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶክተር ነጋሽ ዋጌሾ በበኩላቸው በዛሬው እለት ዳግም የተጀመረው  የዲሪ ማሻ መንገድ የዘመናት የህዝብ ጥያቄ ምላሽ ያገኘበት መሆኑን ጠቅሰው መንግስት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ በሰነቀው ራዕይ የመንገድ ተደራሽነትን  ለማሳደግ  ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ የሚገኝ  መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል ። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር  የመንገድ ሀብት ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አለማየሁ አየለ  የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ  ያለውን ከፍተኛ ፍይዳ ከግምት ውስጥ በማስገባት በታሰበለት ጊዜና የጥራት ደረጃ ገንብቶ ለማጠናቀቅ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። 61 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው ይኸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የበርካታ አመታት የመሰረተ ልማት ጥያቄን ምላሽ ከመስጠቱም ባሻገር የከተማዋን ዕድገት በማሳለጥ ረገድ ሚናው ከፍተኛ ነው። ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚውለውን 6,281,190,550.95 /ስድስት ቢሊየን ሁለት መቶ ሰማንያ አንድ ሚሊየን አንድ መቶ ዘጠና ሺህ አምስት መቶ ሃምሳ ብር ከዘጠና አምስት ሳንቲም  ገንዘብ በፌደራል መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ መንገዱ ካለው ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳ አንፃር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ይሆናል። ግንባታውን የሚያካሂደው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ራስ ሃይል ነው። የመንገድ ግንባታው  በወረዳ ከተማ 26 ሜትር  ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እና በገጠር ከ8-10 ሜትር የጎን ስፋት የለዉ ሲሆን አጠቃላይ ግንባታዉም በ 3 (ሶስት) ዓመት ዉስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል። ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የግብርና ውጤቶች ቡና ፣ ማር እንዲሁም የእንስሳት ምርቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማውጣት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ያደርጋል። በተጨማሪም ለአካባቢው የግብርና ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ በፕሮጀክቱ አካባቢ የሚገኙ ከፍተኛ የእርሻ እምቅ ቦታዎችን ተደራሽ ለማድረግ እና የኢኮኖሚ ልማትን ለማሳደግ ያስችላል። ከዚህም ባሻገር መንገዱ በሚገነባበት አካባቢ ለሚገኙ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ይጠበቃል። የመንገድ ፕሮጀክቱ የኡፋ፣ የጌቲያ (አዲስ አምባ) ፣ የኩቲ ፣ የመኒያ ፣ የጤና ፣ የዱማ ፣ የኮቤቺ  ፣ የሳጃ ፣ የጎጀብ ፣ የሜዳቦ እና የኮንዳ  ከተሞችን በአስፋልት መንገድ የሚያስተሳስር ነዉ። የዲሪ - ማሻ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም በስራ ተቋራጭ የአቅም ውስንነት ምክንያት ተቋርጦ እንደነበር የሚታወስ ነው ። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢተያ - ሮቤ - ሴሩ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 85 ነጥብ 4 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 16፣ 2017 (ኢመአ):- 75.6 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የኢተያ - ሮቤ ምዕራፍ አንድ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 85 ነጥብ 4 በመቶ ደርሷል፡፡ በአሁኑ ወቅት በመንገዱ ግንባታ ላይ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የድሬኔጅ ስራዎች፣ የስትራክቸር ስራዎች፣ የሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣የቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም የአስፋልት ንጣፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ሲሆን ከዚህም መካከል 68 .43 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተገባድዷል፡፡ የፕሮጀክቱን ግንባታ በተያዘው በጀት አመት እንዲጠናቀቅ ለማስቻል በሥራ ተቋራጩ ላይ የተስተዋሉ ውስንነቶች እንዲቀረፉ ለማድረግ ብሎም ሥራዎች እንዲፋጠኑ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ክትትልና ድጋፍ በማድረጉ በመንገዱ ክልል ውስጥ የሚገኙ የካሳ ክፍያዎች በአብዛኛው እንዲፈጸሙ ተደርጓል፡፡ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ሬል ዌይ ቁጥር 3 ኢንጅነሪግ ግሩፕ (CRTG) የተባለው አለም አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ሲሆን የኘሮጀክቱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢንጅነሪግ ኮርፖሬሽን፣ የትራንስፖርት ዘርፍ ነው፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ የጎን ስፋት በወረዳና በከተማ ከ 19 – 21 ሜትር (የአግረኛ እና የውሃ ማፈሰሻ ጨምሮ) ፣ በቀበሌ 15 ሜትር (የውሃ ማፈሰሻ ጨምሮ) ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር (የመንገድ ትከሻን ጨምሮ) ያለው ነው፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም አኳያ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በአስፋልት ኮንክሪት እየተገነባ ይገኛል፡፡ የመንገዱ መገንባት በአርሲ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የሄጦሣ፣ የሎዴ ሄጦሳ፣ የዲክሲስ እና ሮቤ ወረዳዎችን እንዲሁም ቦሩ ሌንጫ፣ የጎበያ፣ የአርብ ገበያ ፣ የእድገት ፋና እና የቡላላ ቀበሌዎችን በማስተሳሰር ምቹ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር ያስችላል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው ላይ የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ መሃል አገር እንዲወጣ በማድረግ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Registration Now Open for the 20th ILO Regional Conference!
Registration Now Open for the 20th ILO Regional Conference!

መልካም በዓል!
መልካም በዓል!

የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት የኢ መ አ የምርምር እና የሥልጠና ማዕከላትን ጎበኙ አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 09፣ 2017 (ኢ መ አ):- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ መሠረተ- ልማት እና ትራንስፖርት ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አባላት የኢ መ አ የመንገድ ምርምር እና የስልጠና ማዕከላትን ጎብኝተዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ እሸቱ ተመስገን (ዶ/ር)፤ የመንገድ ዘርፉን በዕውቀት፣ በቴክኖሎጂ እና በብቁ ባለሞያ በመምራት ረገድ ማዕከላቱ እያደረጉት ያለው አስተዋጽዖ የሚበረታታ ነው ብለዋል። ማዕከላቱን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ዘመኑ የደረሰበትን ወጪ ቆጣቢ የቴክኖሎጂዎች ውጤቶችን መተግበር ይኖርበታልም ብለዋል። በዚህ ረገድ የሥልጠና ማዕከሉን ወደ ሮድ አካዳሚ ለመቀየር የቀረበው ፍኖተ-ካርታ የመንገድ ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ ትልቅ ሚና ይኖረዋል። ለመንገድ ዘርፍ አፈጻጸም መሻሻልም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራህማን (ኢ/ር)፤ ማዕከላቱን ይበልጥ በማዘመን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል እየተሠራ እንደኾነ ተናግረዋል። የመንገድ ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍ በኩልም የምርምር እና የሥልጠና ማዕከላቱ የማይተካ ሚና ይኖራቸዋል ብለዋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአደሌ - ግራዋ የአስፋልት መንገድ ሥራ ፕሮጀክት 84 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2017 (ኢ መ አ) ፡- 53 ኪሎሜትር ርዝማኔ ያለው የአደሌ - ግራዋ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ሥራ ፕሮጀክት 84 በመቶ ደርሷል፡፡ በአሁኑ ወቅት በመንገድ ፕሮጀክቱ ላይ የቤዝ ኮርስ ፣የአስፋልት ንጣፍ እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች እየተከናወኑ የሚገኙ ሲሆን ፣ በእስካሁኑም 32 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራም ለማከናወን ተችሏል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንፃር በተቀመጠለት ጊዜ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል ክትትል እየተደረገበት ይገኛል፡፡ ግንባታው እያከናወነ የሚገኘው የቻይናው ሂቤ ኮንስትራክሽን ግሩፕ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ ሲሆን፣ የማማከሩን ሥራ የሚሠራው ጎጎት አማካሪ መሐንዲሶች ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ነው፡፡ ለግንባታው የተመደበው 1,436,300,000.00 (አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰላሳ ስድስት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሺህ ብር) በፌደራል መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ መንገዱ በወረዳ እና በከተማ 14 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር አጠቃላይ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡ የመንገዱ መገንባት በአደሌ እና በግራዋ ከተሞች መካከል የሚገኙ ወረዳዎችንና ቀበሌዎችን ከማስተሳሰር ጎን ለጎን በሥፍራው የሚገኙ የበቆሎ ፣ የማሽላ ፣ የገብስ ፣ የስንዴ እና ሌሎች በአካባቢው የሚመረቱ የግብርና ውጤቶችን ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ይሆናል ። ከዚህም በተጨማሪ በሥፍራው የሚገኘውን የልጅ እያሱን ቤተ-መንግሥት ለሚጎበኙ ቱሪስቶች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጎንደር  -   ሁመራ  ከባድ የመንገድ   ጥገና  ፕሮጀክት ተጀመረ አዲስ አበባ ሚያዚያ 1 ፣2017 (ኢ መአ):- ሁለት   ዞኖችን    የሚያገናኘው   የጎንደር  -  ሁመራ     የመንገድ  ጥገና  ፕሮጀክት  ተጀምሯል፡፡ የጥገና   ፕሮጀክቱ    የአፈር  ሥራ፣የቆረጣ ሥራ ፣የሙሌት ሥራ ፣ የመንገድ  ትክሻ  ስራዎች ፣የምርጥ  ገረጋንቲ (የሰብ ቤዝ)፣የተፈጨ  ጠጠር  ማንጠፍ ስራ (Base course)፣ የአለት ድንጋይ ሙሌት (Rock fill) የድልድይ/ፉካና የዉሃ ማፋሰሻ ስራዎች እንዲሁም  የአስፓልት ስራዎች (Bituminous Surfacing) ስራዎች  ያካተተ ነው፡፡ አሁን  ላይ   የጥገናው  ሥራ  እንዳይስተጓጎል  ለማድረግም   የተለዋጭ መንገድ  ተሰርቶ  የጥገናው ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ ጥገናው  የሚካሄድለት  ይህ   መንገድ  ባጠቃላይ  4 ኪሎ ሜትር   ርዝማኔ   ያለው  ሲሆን  ያለው   የጎን  ስፋቱ  7 ሜትር  ነው፡፡ ለፕሮጀክቱ   ማስፈፀሚያ  የሚውለው  29,000,000 ብር  የተሸፈነው  በኢትዮጵያ  መንግስት  ሲሆን  ጥገናው በጎንደር  ዲስሪክት  አማካኝነት  እየተከናወነ  በመሆኑ  በተያዘለት   እቅድ መንገዱን   ጠግኖ  ለማጠናቀቅም   በትኩረት   እየተሰራ ነው ፡፡ የጎንደር   መንገድ   አዉታር  ማኔጅመንት  ቅርንጫፍ   ቢሮ   የማማከሩን  እና  የቁጥጥሩን  ሥራ  በመስራት ላይ ነው፡፡  የመንገድ  ጥገናው መደረጉ  በሰቲት ሁመራ  እና  በማዕከላዊ  ጎንደር ዞን  ብሎም   በትክል ዲንጋይ  ፣ በሳንጃ ፣ በጠገዴ ፣በቃፍቲያ  ወረዳዎች  መካከል  ምቹና  ቀልጣፋ  የትራፊክ  ፍሰት  እንዲኖር ያስችላል፡፡ በተጨማሪም   በአካባቢው   በስፋት  የሚመረቱ  የሰሊጥ ፣የኑግ ፣የማሽላ እና የጥጥ  ምርቶችን  ወደ  ገበያ  ለማውጣት   በማስቻል  የግብይት   እና  ኢኮኖሚያዊ  እንቅስቃሴዎችን  ለማስፋፋት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ይሆናል፡፡ በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Invitation for workshop
Invitation for workshop

የነቀምት -ቡሬ፣ ክፍል 1፡ ነቀምት - አንገር ጉቲን -አንዶዴ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአጠረ ጊዜ  ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29  ቀን  2017   ዓ.ም (ኢ መ አ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ውስጥ የሚገኘው  86.1 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው  የነቀምት - አንገር ጉቲን -አንዶዴ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ  መነሻውን ነቀምት ከተማ አድርጎ እስከ አንዶዴ  የሚዘልቅ ነው። በእስካሁኑ  የመንገድ ግንባታ ስራ  የአስፋልት ንጣፍ (21 ኪ.ሜ) አፈር ቆረጣ እና ሙሌት (25.23 ኪ.ሜ)፣ የድሬኔጅ ስራዎች( 69%)፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ  (22 ኪ.ሜ)፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ ( 21 ኪ.ሜ) እንዲሁም በርካታ የስትራክቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።   ለግንባታ  ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ  1,948,446,483.18 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ አርባ ስምንት ሚሊዮን አራት መቶ አርባ ስድስት ሺህ አራት መቶ ሰማንያ ሶስት ብር ከአስራ ስምንት ሳንቲም) ብር የሚሸፈነው  በአለም ባንክ ነው ። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads የግንባታ ፕሮጀክቱን እያካሄደ የሚገኘው  ቾንግኪንግ ኢንተርናሽናል ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ሬናርዴት ከዩናይትድ አማካሪ መሐንዲሶች (ዩኒኮን) ኃ.የተ.የግ.ማ. ጋር በጣምራ በመሆን እያከናወኑት ይገኛሉ። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል። የዚህ መንገድ ግንባታ መጠናቀቅ  ከዚህ በፊት የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍየ የአካባቢው ነዋሪ  በተመጣጣኝ ዋጋ ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታን ይፈጥራል። አርሶ አደሮች ምርታቸውን ካለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ማዕከላዊ እና የውጭ ገበያ በማውጣት  አምራችና እና ሸማቾችን በቀላሉ በማገናኘት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፡፡ በተጨማሪም  የነቀምት፣ ጉዳቱ ፂገ፣ ሁከ፣ አንገር ጉቲንና አንዶዴ ከተሞችን በአስፋልት ኮንክሪት መነገድ የሚይገኛኝ ይሆናል። የመንገድ ግንባታው  በዞን እና በወረዳ 21.5 ሜትር፣  በቀበሌ  12 ሜትር እና በገጠር 7 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ ነው የሚገኘው ።

የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ በመልካም የአፈፃፀም ደረጃ ላይ ነው አዲስ አበባ መጋቢት 26 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኮምቦልቻ ከተማ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘው የኮምቦልቻ ከተማ የአስፋልት ኮንክሪት ተለዋጭ የመንገድ ግንባታ በመልካም የአፈፃፀም ደረጃ ላይ ይገኛል። ለመንገዱ ግንባታ 1,138,807,808 (አንድ ቢሊዮን አንድ መቶ ሰላሳ ስምንት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሰባት ሺህ ስምንት መቶ ስምንት ብር ) ወጪ በፌደራል መንግስት ተመድቧል፡፡ ግንባታው በሀገር በቀሉ ዮንአብ ኮንስትራክሽን እየተከናወነ የሚገኘውና 7 ነጥብ 58 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ይህ መንገድ የመንገድ ትከሻን እና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ 20.6 ሜትር አጠቃላይ የጎን ስፋት ያለው ነው፡፡የመንገዱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ሃገር በቀሉ ኢትዮ ኢንፍራ ኢንጂነሪንግ እያከናወነው ይገኛል ፡፡ አሁን ላይ ከመንገድ ፕሮጀክቱ 24.7 በመቶ የሚሆነው ሥራ የተገባደደ ሲሆን የአፈር ጠረጋ ፣ የአፈር ቁፋሮ፣ የአፈር ሙሌት፣ የማፋሰሻ ቱቦ በማምረት በመንገዱ ላይ የመግጠም ፣የሰብ ቤዝ ፣የድልድይ እና የደጋፊ ግንብ ስራዎች በሂደት ላይ ያሉ ሲሆን በእስካሁኑም የአራት ድልድይ ስራዎችን ማጠናቀቅ ተችሏል። በፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ወቅት የጸጥታ ችግር፣የወሰን ማስከበር ችግር ፣የካሳ ክፍያ በወቅቱ አለመከፈል፣ ከዚህም ጋር ተያይዞ ለስራ ተቋራጩ ለስራ በቂ የሆነ የመስሪያ ቦታ ከንብረት ነፃ በማድረግ መስጠት አለመቻሉ፣ ለምርጥ ድንጋይ ማምረቻ የሚሆን ቦታ (Quarry Site)አለመገኘቱ፣ የሲሚንቶ፣ ነዳጅ፣ብረት እና ሌሎች የግንባታ ግብአቶች እጥረት አጋጥመዋል። ችግሩን ለመቅረፍ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኮምቦልቻ አካባቢ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ጽ/ቤት በኩል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሠራ ይገኛል፡፡ የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ ቁጥራቸው በርከት ያሉ ከባድ ተሸከርካሪዎች ወደ ከተማው ሳይገቡ ለማስተናገድ እንዲሁም ለኢንዱስትሪ ግብዓቶች ምርት ማውጫ በመሆን ከፍተኛ ጠቀሜታ የሚሰጥ በመሆኑ በከተማዋ ውስጥ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ በከፍተኛ ደረጃ ይቀርፋል ተብሎ ይጠበቃል። የመንገድ ኘሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በአካባቢው የሚገኙ የመስተዳድር አካላት፣ የክልሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ትብብር እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል፡፡ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads