ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 331 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 541

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 331 名订阅者。

根据 16 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 90,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.85%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.40% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 439 次浏览,首日通常累积 2 050 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 17 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 323
订阅者
+824 小时
+217
+9030
帖子存档
የዎላይታ ሶዶ ከተማ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ሶዶ፣ የካቲት 4፣ 2017 (ኢ መ አ):- በደቡብ የኢትዮጵያ ክልል  በዎላይታ ዞን የሚገኘው የዎላይታ ሶዶ ከተማ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ  እየተሰራ ይገኛል ። የከተማ መንገዱ 12 ነጥብ 39 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን፣የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በሁለት ሎት ተከፍሎ እየተሰራ ይገኛል። ሎት 1 ከሌዊ እስከ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(7.14) ኪሎ ሜትር ሲሆን ሎት 2 ከጦና አደባባይ እስከ አረካመውጫ መገንጠያ ድረስ (6.3) ኪ.ሜትር  የሚዘልቅ ነው። አሁን ላይ የአፈር ቆረጣና እና ሙሌት ፣የውሃ ቱቦ ቀበራ፣ የድጋፍ ግንብ እና አርማታ ፣የቱቦ ማምረት ስራ እና ቤዝኮርስ ስራዎች ተሰርተዋል። አጠቃላይ አፈፃፀሙ 15 በመቶ ደርሷል።  ግንባታውን ለማከናወን መንግስት (2,620,119,958.46 )ሁለት ቢሊዮን ስድስት መቶ ሃያ ሚሊዮን አንድ መቶ አስራ ዘጠኝ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሃምሳ ስምንት ብር ከአርባ ስድስት ሳንቲም ፈሰስ ያደርጋል። ግንባታውን ተረክቦ እያከናወነ የሚገኘው አለማቀፉ ቻይና ፈርስት ሃይዌ ኢንጂነሪንግ  ኮ. ኤልቲዲ /CFHEC/ነው ። ግንባታው  ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ ማድረስ ተችሏል። በ2018 ዓ .ም ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ ይገኛል ። ጂ.ኤን ዋይ ምህንድስና አማካሪ ከደወል አማካሪ መሃንዲሶች ጋር በጣምራ በመሆን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን እያከናወኑ ይገኛሉ። የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም የነበረውን  የትራፊክ መጨናነቅን ከመቀነሱም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት ያፋጥናል። መንገዱ የእግረኛ እና የመንገድ አካፋይን ጨምሮ በከተማ 34 እና 21.5 ሲሆን በገጠር ከተማ 13ነጥብ 6 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው። ከተማዋ በፈጣን ዕድገት ላይ የምትገኝና የደቡብ ክልል የፖለቲካና አስተዳደር ማዕከል በመሆኗ የመንገዱ መገንባት ከፍተኛ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አለው ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Call for side event
Call for side event

ሀገር  አቀፉ  የመንገድ  ሴክተር  ጉባኤ  ምክክር   ተካሄደ ጎንደር ፣ የካቲት 1፣ 2017 (ኢመአ):- ሀገር  አቀፉ  የመንገድ  ሴክተር  ጉባኤ  ምክክር  ከፍተኛ   የፌደራል እና  የክልል  የሥራ ኃላፊዎች  እንዲሁም  የከተማ አስተዳደሮች  በተገኙበት  ተካሄዷል። በጉባኤው  ላይ የፌደራል  የክልሎች እና የከተማ  መስተዳድር   የመንገድ ኤጀንሲዎች  የ 2017  በጀት  ዓመት   የስድስት ወራት መደበኛና  ወቅታዊ  የመንገድ  ግንባታ  እና  ጥገና እቅድ  አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቧል። የመንገድ  ኤጀንሲዎቹ  በበጀት  አመቱ  ያከናወኑትን  አጠቃላይ  የመንገድ  ግንባታ  እና  ጥገና  አፈፃፀም  አስመልክቶም  ግምገማ  ተደርጓል። መድረኩ  በመላው  ሀገሪቱ  የዜጎችን   ፍላጎት  የሚመጥን  የመንገድ  ሽፍን  ለማሳደግ  መንግስት  በሰጠው ልዩ  ትኩረት  የመንገድ ልማት  ማዕቀፍን  በመተግበር  ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት  የሚያግዝ  መሆኑን የከተማና  መሰረተ ልማት ሚኒስቴር  ሚኒስትር  ክብርት ጫልቱ ሳኒ ገልፀዋል። አያይዘውም በመንገድ ዘርፋ የታየው ስኬት አመርቂ  ውጤት የታየበት በመሆኑ ለህብረተሰቡ  ተገቢውን  ምላሽ  ለመስጠት የዘርፉ  አስፈፃሚዎች  የጋራ  ቅንጅት   በመፍጠር  መሥራት ይገባቸዋል ብለዋል። በሀገሪቱ የተከሰቱ  የፀጥታና አለመረጋጋት ችግሮች ፣ የበጀት እና የግብአት እንዲሁም የማሽነሪ መለዋወጫ እጥረቶች የመንገድ ግንባታዎችን እና  ጥገናዎች ለማካሄድ ችግሮችን መፍጠራቸው ታውቋል። ይህንን ለመፍታት የመንገድ ፈንድ ገቢን ለማሳደግ እና በቀጣይ የመንገዶች ጥገና  ሽፋንን ለመጨመር  የሚያስችል ስትራቴጂክ እቅድ  ተይዞ እየተሰራ  እንደሚገኝ ተጠቁሟል። በአስር አመቱ መንገድ ልማት ዘርፍ  ፕሮግራም የተገኘውን ውጤት የበለጠ ለማሻሻል እና የሚጠበቀውን ውጤት ለማምጣት  አስፈላጊው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል። ከዚህም ባሻገር በዘርፉ የተነሱ  ችግሮችን  ለመፍታትና  ደረጃ  በደረጃ  መፍትሄ ለማምጣት  የመንገድ ኤጀንሲዎች ፎረም ምስረታ ተከናውኗል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የሀሚድ ድልድይ ተለዋጭ መንገድ አገልግሎት መስጠት ጀመረ የወልድያ ሮቢት የመንገድ ክፍል የሆነው የሀሚድ ድልድይ ተለዋጭ መንገድ ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። በድልድዩ ጉዳት የተፈጠረውን የትራ
የሀሚድ  ድልድይ  ተለዋጭ  መንገድ   አገልግሎት  መስጠት  ጀመረ የወልድያ  ሮቢት  የመንገድ   ክፍል የሆነው   የሀሚድ   ድልድይ  ተለዋጭ  መንገድ   ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። በድልድዩ  ጉዳት   የተፈጠረውን   የትራንስፖርት  መስተጓጎል   ለመፍታት  በተደረገው  ከፍተኛ  ጥረት  የተለዋጭ  መንገዱ ለአነስተኛ እና  ለትላልቅ  መኪኖች አገልግሎት  እየሰጠ ይገኛል። ለድልድዩ ዘላቂ መፍትሄ  እስኪገኝ  ድረስ ድልድዩን  የሚጠቀሙ  ተሽከርካሪዎች በመጠባበቅ እንዲተላለፉ የኢትዮጵያ  መንገዶች አስተዳደር  ያሳስባል።

የሀሚድ ድልድይ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል የወልድያ ሮቢት የመንገድ ክፍል በሆነው የሀሚድ ድልድይ ላይ ጉዳት መድረሱን ተከትሎ የተስተጓጎለውን የትራንስፖርት አገልግሎት ለማስጀመር
የሀሚድ  ድልድይ  አገልግሎት እንዲሰጥ  ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል የወልድያ   ሮቢት   የመንገድ   ክፍል   በሆነው   የሀሚድ   ድልድይ  ላይ  ጉዳት መድረሱን ተከትሎ የተስተጓጎለውን የትራንስፖርት  አገልግሎት  ለማስጀመር  እየተሰራ  ይገኛል። የሀሚድ  ወንዝ  የብረት ድልድይ  ላይ  ጉዳት  ያጋጠመው  ከተፈቀደው  በላይ  ትርፍ  ጭነት  በጫነ  ተሽከርካሪ  የተነሳ  ሲሆን   ይህም   የትራንስፖርት   መስተጓጎል  እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል። በድልድዩ  ጉዳት   የተፈጠረውን  የትራንስፖርት  መስተጓጎል   ለመፍታት    በጊዜያዊነት  የተለዋጭ  መንገድ   ተሰርቶ አነስተኛ  ተሽከርካሪዎች  እንዲሸጋገሩ  የተደረገ  ሲሆን   ትልልቅ  መኪኖች  እንዲያልፉ  ለማስቻል  ጥረቶች  ተጠናክረው  ቀጥለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት  ለድልድዩ   ዘላቂ  መፍትሄ   ለመስጠት  ይቻል  ዘንድ   በኢትዮጵያ  መንገዶች  አስተዳደር  በኩል  ከፍተኛ  ክትትል  እየተደረገ  ይገኛል። የድልድዩ   ተጠቃሚዎችም  መስሪያቤቱ   ድልድዩን  ጠግኖ  አገልግሎት  እስኪሰጥ  ድረስ  በትእግስት እንዲጠባበቁ  መልእክቱን  ያስተላልፋል፡፡

ከአዲስ  አበባ  የሚወጡ  4  የፍጥነት መንገዶች ለመገንባት ጥናት እየተደረገ ይገኛል ከአዲስ    አበባ   በተለያዩ   መስመሮች   የሚወጡ   4   አዳዲስ   የፍጥነት   መንገዶችን  ለመገንባት  የሚያስችል  ጥናት እየተደረገ  ይገኛል፡፡ ጥናቱ   እየተደረገ   የሚገኘው    ከአዲስ  አበባ ደሴ ፣ከአዲስ  አበባ  ጅማ ፣ከአዲስ  አበባ  ደብረማርቆስ  እና  ከአዲስ አበባ  ነቀምት    በሚዘልቁት   መንገዶች  ላይ  ነው፡፡ እነዚህ    የፍጥነት  መንገዶች   የሚገነቡበት   የጥራት  ደረጃ ፣ የሚኖራቸውም   አጠቃላይ የጎን  ስፋት  ከፍ  ያለ  እና  የሚገነቡበት  መልክአ  ምድር  አብዛኛውን   ተራራማ  ቦታዎችን  የሚሸፍን  በመሆኑ  ከፍተኛ  የሆነ   ወጪ እና   የቆረጣ   ስራዎችን  የሚጠይቁ  ናቸው፡፡ በጥናቱ   መሰረት   ፕሮጀክቶቹ   የሚኖራቸው   ርዝመት   በአማካይ   300  ኪሜ   ሲሆን   ግንባታቸውም   በተለያዩ  ምዕራፎች  እና  በተወሰነ   ኪሎሜትር ተከፋፍሎ የሚጀመር ይሆናል፡፡ በአሁኑ  ወቅት  የፕሮጀክቶቹ  የአዋጭነት፥ እንዲሁም  መሰረታዊ  የዲዛይንና  የዝግጅት ሥራ እየተከናወነ ሲሆን ለዝግጅት  ሥራው  የሚያስፈልጉ   የጥናት  ስራዎችንም  ለማጠናቀቅ  እየተሰራ ነው። አራቱን  የፍጥነት  መንገዶች  ለመገንባት የሚያስፈልገው   ወጪ  የሚሸፈነው  በመንግስትና   የግል   አጋርነት  ትብብር   ነው፡፡ ከፍጥነት  መንገዶቹ  መካከል  የአዲስ  ጅማ እና አዲስ ደብረ ማርቆስ ፕሮጀክቶች ለገንዘብ ሚኒስቴር የመንግስት የግል  አጋርነት  ቦርድ  የቀረቡ  ሲሆን  ቀሪዎቹም  በቅርቡ  ይቀርባሉ  ተብለው ይጠበቃል ። ፕሮጀክቶቹም   በገንዘብ  ሚኒስቴር  የመንግስት  የግል  አጋርነት  ትብብር  ቦርድ   ከጸደቁ  በኋላ  ወደ ቀጣይ ስራ ይገባሉ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር - Telegram 频道 @ethioroads 的统计与分析