ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 331 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 541 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 331 名订阅者。
根据 16 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 90,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.85%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.40% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 439 次浏览,首日通常累积 2 050 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 17 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 323
订阅者
+824 小时
+217 天
+9030 天
帖子存档
13 331
የመረዋ - ሶሞዶ - ሰቃ እና ሊሙ መገንጠያ መንገድ ፕሮጃክት አፈጻጸም 53 በመቶ ደረሰ
ጅማ፣ ጥር 17፣ 2017 (ኢ መ አ):- በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን የማና እና የሊሙ ኮሳ ወረዳዎችን የሚያገናኘው የመረዋ - ሶሞዶ - ሰቃ እና ሊሙ መገንጠያ መንገድ ፕሮጃክት አጠቃላይ አፈጻጸም 53 በመቶ ደርሷል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ሲኾን፥ 93 ነጥብ 95 ኪሎሜትር ይሸፍናል።
አሁን ላይ የ28 ኪሎሜትር የቤዝኮርስ እና የአስፋልት፣ የ38 ኪሎሜትር ሰብቤዝ፣ የ70 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም የ38 በመቶ የውኃ ማፋሰሻ ቱቦ ሥራዎች ተጠናቅቀዋል። የአራት ድልድዮች እንዲሁም የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች ሥራም በፕሮጀክቱ ተካትቷል።
የተራዘመ የዝናብ ወራት፣ የሥራ ተቋራጩ የአፈጻጸም ውስንነት እና በወቅቱ እልባት ያላገኙ የወሰን ማስከበር ሥራዎች የፕሮጀክቱ ፈተና ኾነው ቆይተዋል። ችግሮቹን ለመቅረፍ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የመንገድ ወሰኑን ከንብረት ነጻ በማድረግ እና ለግንባታ ዝግጁ በማድረግ በኩል አስፈላጊው ሥራ ተሠርቷል። በሥራ ተቋራጩ በኩል ያሉ ውስንነቶችን ለመፍታትም የእርምት እርምጃዎች ተወስደዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አዎንታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል።
በተያዘው ዓመትም ግንባታውን የሚያከናውነው ዓለም- አቀፉ ቻይና ቲሲጁ ሲቪል ኢንጅነሪንግ ተጨማሪ የ30 ኪሎሜትር አስፋልት ንጣፍ ለማከናወን ዕቅድ አስቀምጧል።
የተባበሩት የምህንድስና አማካሪዎች የፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ያከናውናል። ለፕሮጀክቱ የተመደበው 2 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ወጪ በፌደራል መንግስት ይሸፈናል።
የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከመረዋ አንስቶ እስከ ፕሮጀክቱ ማብቂያ ድረስ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን 6ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 2 ሰዓት ያሳጥረዋል። አካባቢው ቡና አብቃይ እንደመኾኑ ምርት በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል።
የሰሞዶ፣ ብሊዳ፣ ኬንቴሪ፣ ባቡ፣ ሊሙ ገነት፣ ሰቀ እና መሰል ከተሞች የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ያጠናክራል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የአጣጥ ማዞሪያ - ጉንችሬ - ቆሴ - ጌጃ - ሌራ መንገድ ስራ ቀሪ ስራዎችን የማጠናቀቂያ ፕሮጀክት እየተካሄደ ይገኛል
አዲስ አበባ ፤ ጥር 15 /2017 (ኢመአ)፦ ሦስት ዞኖችን የሚያስተሳስረው የአጣጥ ማዞሪያ - ጉንችሬ - ቆሴ - ጌጃ - ሌራ መንገድ ቀሪ ስራዎችን የማጠናቀቂያ ፕሮጀክት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ የሚገኘው መንገዱ 97.01 ኪሎሜትር ርዝማኔ ያለው ሲሆን በወረዳ 21 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር የጎን ስፋት አለው፡፡
በዚህ ፕሮጀክት ላይ የአስፋልት ማንጠፍ ስራ፤ የሰብ ቤዝ እና ቤዝ ኮርስስራ፤ የጠረጋና ምንጣሮ፣የአፈር ቆረጣ፣ የተመረጠ አፈር ሙሌት ሥራ ፤ የውሃ ማፋሰሻ ትቦዎች፤ የድልድይ ስራዎች እንዲሁም የጠጠር መፍጨት ሥራ በመከናወን ላይ ናቸው፡፡
የመንገዱን ግንባታ ሀገር በቀሉ አለማየሁ ከተማ ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥር ሥራ አይዲኮን ኢንፍራስትራክቸር ዴቨሎፕመንት አማካሪ ኃ.የተ. የግ. ማ. እየሰራው ነው፡፡
ለፕሮጀክቱ ግንባታ የሚውለው 5,106,525,941.61 (አምስት ቢሊዮን አንድ መቶ ስድስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሃያ አምስት ሺ ዘጠኝ መቶ አርባ አንድ) ብር በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኗል፡፡
በአጣጥ ማዞሪያ - ጉንችሬ - ቆሴ - ጌጃ - ሌራ የመንገድ ግንባታ ሂደት ላይ ያጋጠሙ የወሰን ማስከበር ችግሮችን ለመፍታት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከወረዳና ከዞን አስተዳደሮች ጋር በጋራ እየሰራ ይገኛል፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የጉራጌ ፣የሀድያ ፣የስልጤ ዞኖችን እንዲሁም ሌሎች ስድስት ወረዳዎችን በቀላሉ በማገናኘት የእርስ በእርስ ትስስርን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል፡፡
በተጨማሪም በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የእንሰት ተክል ፣የበቆሎ፣ የበርበሬ፣ የቡና እንዲሁም የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በቀላሉ በማውጣት የገበያ ተደራሽነትን ለማስፋፋት ያግዛል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
በወራቤ - ቦዠባር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አስፋልት ንጣፍ ተጀመረ
አዲስ አበባ ፤ ጥር 14 /2017 (ኢመአ)፦ የጉራጌ ዞንን ከስልጤ ዞን ጋር በሚያገናኘው የወራቤ - ቦዠባር የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አስፋልት ማንጠፍ ተጀመረ።
41.3 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው በዚህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ላይ ከአስፋልት ንጣፍ ጎን ለጎን የአፈር ቆረጣና ሙሌት ፣ የውሀ ማፋሰሻ ስራዎች፣ የ 1 ድልድይ እና 40 የውሀ ማፋሰሻ ፉካዎች ፣5 አነስተኛ ድልድዮች፣ የመንገድ ዳር እና የትራፊክ ምልክት ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው፡፡
በአሁኑ ወቅት የመንገድ ፕሮጀክቱ 54.4 በመቶ የደረሰ ሲሆን ቀሪ የግንባታ ስራዎች በተያዘላቸው እቅድ መሰረት እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
መንገዱን ለመገንባት የሚውለው የገንዘብ መጠን 2,777,252,940 (ሁለት ቢሊዮን ሰባት መቶ ሰባ ሰባት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሃምሣ ሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ አርባ) ብር የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡
የመንገዱ አጠቃላይ የጎን ስፋት በዞን ከተማ 21.5 ሜትር ፣በወረዳ 21 .5 ሜትር፣ በቀበሌ 15 ሜትር እና በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ነው፡፡
ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ የአማራ መንገድ ስራዎች ድርጅት ሲሆን ኤስጂ አማካሪ መሐንዲሶች ኃላ/የተ/የግ/ማ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራ እየሰራ ይገኛል፡፡
ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜና ጥራት መጠናቀቅ ይችል ዘንድ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የቡታጅራ የመንገድ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በኩል ክትትልና ድጋፍ እየተደረገበት ነው፡፡
መንገዱ በዋናነት የወራቤ ፣ኩተሬ ፣ ቃዋቆቶ እና ቦዠባር ከተሞችን በቅርበት በማስተሳሰር ረገድ ከፍተኛ ጥቅም ይሰጣል ፡፡
ከዚህም ጎን ለጎን በአካባቢው የሚመረቱ እንደ ገብስ፣ ስንዴ እና የቅመማ ቅመም ምርቶችን ለገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ነው፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
በጋምቤላ ክልል የተጀመሩ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈፃፀምን አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ
አዲስ አበባ ፤ ጥር 12 /2017 (ኢመአ)፦ በጋምቤላ ክልል የሚገኙ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈፃፀምን አስመልክቶ በክልሉ ርዕሰ ከተማ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በውይይቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ፣ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን እና ሌሎች የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
በወቅቱ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን ኢመአ ውስጣዊ አሰራሮችን በማጠናከርና የፕሮጀክት ፈፃሚዎችን በማትጋት በሁሉም አካባቢዎች በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አክለውም በጋምቤላ ክልል በሂደት ላይ የሚገኙ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በማፋጠንና ተጀምረው በአፈፃፀም ችግር ምክንያት የተቋረጡትን በማስቀጠል ለህብረተሰቡ የመንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በትጋት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።
ተቋሙ በክልሉ እያከናወናቸው ለሚገኙት የመንገድ ፕሮጀክቶች ስኬታማነት የክልሉ መንግስት ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባውም ዋና ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው ክልሉ ቀደም ሲል በነበሩት ዓመታት በሚጠበቀው ደረጃ የመንገድ መሰረተ ልማት ተጠቃሚ ሳይሆን መቆየቱን አስረድተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የክልሉን ህዝብ የመንገድ መሰረተ ልማት ጥያቄዎች ለመፍታት በፌዴራል መንግስት የተጀመሩት ስራዎች የሚበረታቱ ቢሆንም በተወሰኑ የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ የአፈፃፀም ችግሮች የሚስተዋሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በክልሉ በሂደት ላይ የሚገኙ መንገዶች ግንባታን ለማፋጠንና የተቋረጡትን ለማስቀጠል የክልሉ መንግስት ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ኢመአ በዚሁ በጀት ዓመት መሰል መድረኮችን ከሌሎች ክልሎች ጋር ማካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ፣ ውይይቱ ባልተካሄደባቸው ክልሎች በቀጣይ የሚያካሄድ ይሆናል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
Title ECOROADS for Ethiopia
Date Wednesday January 22,
Via virtual
Time morning 9:00-10:00 am
Link: https://meet.google.com/int-kbuw-vxp
13 331
የአዘዞ-ጎንደር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በቅርቡ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው
አዲስ አበባ ፣ ጥር 8 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ) አጠቃላይ 12 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ርዝመት የሚሸፍነውን የአዘዞ-ጎንደር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በቅርቡ ለማጠናቀቅ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡ የፌደራል መንግስት በመደበው 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው ይኸው ፕሮጀክት ከዚህ ቀደም በሌላ የሀገር በቀል የስራ ተቋራጭ አማካኝነት ግንባታው ሲከናወን ቆይቶ ከአፈጻጸም ውስንነት ጋር በተያያዘ ውሉ መቋረጡ ይታወቃል።
የፕሮጀክቱን ቀሪ ሥራዎች በፍጥነት ለማጠናቀቅ እንዲቻል በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ግንባታውን ተረክቦ እየሠራ ይገኛል። 21 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ በሚገኘው በዚሁ ፕሮጀክት አብዛኛው የስትራክቸርና ተጨማሪ ዋና ዋና የፕሮጀክቱ ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን ፣ አሁን ላይ የአስፋልት ማንጠፍ ስራዎች በመካሄድ ላይ ናቸው፡፡
በአሁኑ ወቅት በመንገዱ የቀኝ አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ አስፋልት የማንጠፍ ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ የግራው አቅጣጫ ደግሞ 1.5 ኪሎ ሜትር ሲቀር የአስፋልት ንጣፍ ተደርጎለታል፡፡
የመንገዱ የግንባታ ሂደት በመዘግየቱ ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች ለትራንስፖርት መስተጓጎል ችግር ሲዳረጉ የነበረ ሲሆን ፤ አሁን ላይ የግንባታ ሂደቱ እየተፋጠነ በመሆኑ ችግሩ እየተቀረፈ ይገኛል፡፡
መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም ይስተዋል የነበረውን የከተማውን የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ችግር የሚያቃልል ከመሆኑም ባሻገር ከሰሜን ጎንደር ወደ መተማ እና ሌሎች የማዕከላዊ ጎንደር አካባቢዎች የሚደረገውን የትራንስፖርት ፍሰት ያሳልጣል ተብሎ ይታመናል።
ዲስትሪክቱ አሁን ላይ ከዚህ ፕሮጀክት በተጨማሪ 700 ሜትር የጎንደር ከተማ አስፋልት ስራ እና ሌሎች ተጨማሪ ተግባራትን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የዳዬ-ግርጃ - መልካደስታ እና መለያ -መጆ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጄክት በመካሄድ ላይ ነው
አዲስ አበባ ፣ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ) የሲዳማ ክልልን ከኦሮሚያ ጋር የሚያገናኘው የዳዬ-ግርጃ - መልካደስታ እና መለያ -መጆ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጄክት በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ አሁናዊ አፈፃፀሙም 42 ነጥብ 20 በመቶ ደርሷል።
65 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ይህ መንገድ በወረዳ 21.8 ሜትር ፣ በቀበሌ 14.8 ሜትር ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር አጠቃላይ የጎን ስፋት አለው።
በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ የአፈር ሙሌት እና ቆረጣ ፣ የአነስተኛ ድልድይ ግንባታ ፣ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦና የድጋፍ ግንብ ፣ የካፒንግ ፣ የሰቤዝ ንጣፍ ፣ የቤዝኮርስ እንዲሁም የአስፋልት ኮንክሪት ንጣፍ ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው።
መንገዱ በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ውስጥ ከሚገኘው ዳዬ ከተማ መነሻውን በማድረግ ግርጃ/መልካ ደስታ እና መጆ ከተማ ላይ ያበቃል።
ግንባታውን ቻይና ቲሲጁ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የተባለ የሥራ ተቀራጭ በማካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራውን ደግሞ ዩናይትድ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የተ/የግ/ድ በማከናወን ላይ ይገኛል።
ለመንገዱ ግንባታ የሚውለው 1,555,708,167 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሀምሳ አምስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ሰባት) ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው።
ፕሮጄክቱን በተቀመጠው ጊዜ እና ጥራት ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን ግንባታዉ ሲጠናቀቅ የመስመሩን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት በማፋጠን ረገድ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ይታመናል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የጅማ - ጭዳ መንገድ ፕሮጀክት ወደ አስፋልት የማንጠፍ ምዕራፍ ተሸጋገረ
ጅማ፣ ጥር 02፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኦሮሚያ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎችን የሚያገናኘው የጅማ - ጭዳ 80 ኪሎሜትር መንገድ ፕሮጀክት ወደ አስፋልት የማንጠፍ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ በሁለቱ ክልሎች የሚገኙ ሦስት ወረዳዎችን የሚያስተሳስር ሲኾን፣ አሁን ላይ የ10 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ተከናውኖለታል።
በተጨማሪም የ14 ኪ.ሜ ሰብቤዝ፣ 11 ኪ.ሜ ቤዝኮርስ እና የ52 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ሥራዎች ተሠርተዋል። እንዲሁም የአንድ ድልድይ ግንባታ በሂደት ላይ ይገኛል። አጠቃላይ አፈጻጸሙ 31 በመቶ ደርሷል።
የፕሮጀክቱን የተሻለ አፈጻጸም በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል የሚያስችሉ በማሽነሪ፣ የሥልጡን ባለሞያ ቅጥር እና በግብአት በኩል በቂ ዝግጅት መደረጉን ቦታው ድረስ በተደረገ ቅኝት መመልከት ተችሏል።
ከዚህም ባሻገር ግንባታው የአካባቢውን ሥነ-ምኅዳር ባገናዘበ መልኩ የአካባቢ እና የማኅበራዊ ደኅንነት መርሆዎችን ተከትሎ በጥንቃቄ እየተከናወነ ይገኛል።
ቻይና ቲሲጁ ኢንጅነሪንግ ግንባታውን የሚያከናውን ሲኾን፣ ኪዮንግዶንግ ኢንጅነሪንግ፣ ኦሪየንታል ኮንሰልቲንግ እና ኮር ኮንሰልቲንግ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን በጥምረት ይሠራሉ። ለግንባታው የተመደበው 2 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ወጪ በአፍሪካ የልማት ፈንድ እና በጃፓን ዓለም-አቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት የፋይናንስ ድጋፍ ይሸፈናል።
መንገዱ ሲጠናቀቅ ቀድሞ ከጅማ ከተማ አንስቶ እስከ ጭዳ ከተማ ለመድረስ የሚወስደውን 4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ከአንድ ሰዓት ተኩል ባነሰ ጊዜ ለመግባት ያስችላል። የጅማ፣ ዴዶ፣ ሚቴሶ እና መሰል ከተሞች ትስስርን በማጠናከር ምርት በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል።
የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ እና የሃላል ኬላ መዳረሻ እንደመኾኑም መንገዱን ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ ረገድ ጉልህ አስተዋጽዖ ያበረክታል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
