ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 331 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 541 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 331 名订阅者。
根据 16 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 90,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.85%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.40% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 439 次浏览,首日通常累积 2 050 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 17 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 323
订阅者
+824 小时
+217 天
+9030 天
帖子存档
13 331
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚከናወኑ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ
ሆሳዕና ፣ የካቲት 26 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የሚከናወኑ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እና የጥገና ስራዎች አፈጻጸምን አስመልክቶ ከክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡
በውይይቱ ወቅት የክልሉን ርዕሰ መስተዳደርን ጨምሮ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን እና ሌሎች የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዞን እና የልዩ ወረዳዎች ዋና አስተዳዳሪዎች ተሳትፈዋል።
በወቅቱ በክልሉ በተለያየ የግንባታ ደረጃ ላይ የሚገኙ 14 ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ከእነዚህ ፕሮጀክቶች ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች የዘገዩ ፕሮጀክቶች የሚገኙ ሲሆን ፣ በፕሮጀክቶቹ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮቹን በመለየት እና መፍትሄ በመስጠት አፈፃፀማቸውን በማሻሻል ፕሮጀክቶቹን ማጠናቀቅ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡
ከዚህም ባሻገር ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በክልሉ 849 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸው መንገዶች በጥገና ሂደት ላይ እንደሚገኙ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ፣ አፈፃፀሙም መልካም መሆኑ ተገምግሟል፡፡
በተጨማሪም በክልሉ በግንባታ ሂደት ላይ ከሚገኙ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በቀጣይ ወደ ግንባታ የሚሸጋገሩ 10 ፕሮጀክቶች በዲዛይን እና በግዢ ሂደት ላይ ይገኛሉ፡፡
በምክክር መድረኩ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን በክልሉ በትገበራ ሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን በቀሪ ጊዜያት አፋጥኖ በማስቀጠል አፈፃፀማቸዉን በሚጠበቅበት ደረጃ ለማድረስ ይሰራል ብለዋል፡፡ በዚህም ረገድ በመንገድ ፕሮጀክቶቻችን እያጋጠሙ ካሉ ተግዳሮቶች አኳያ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ መድረክ በኋላ ከክልሉ ጋር የጋራ መርሃ-ግብር በመቅረፅ መተግበር እንደሚገባ የገለፁ ሲሆን በዚህ መልኩ መጓዝ ከተቻለ በፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ላይ ተጨባጭ ለዉጥ ማምጣት ይቻላልም ብለዋል፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከክልሉ መንግስት ጋር በትብብር ለመስራት እያሳየ ያለውን የላቀ ተነሳሽነት አድንቀዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በክልሉ በመንገድ መሰረተ ልማት የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ላደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።
በክልሉ በግንባታ ሂደት ያሉ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተገቢዉን ክትትልና ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል፡፡ ከዚህም አኳያ በፕሮጀክቶቹ አፈፃፀም ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን እየለዩ መፍትሄ መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም በክልሉ በግንባታ ሂደት ላይ ከሚገኙት በተጨማሪ አዳዲስ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እንዲጀመሩ ፍላጎቶች ስላሉ በዕቅድ የሚካተቱበትን ሁኔታ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር በቀጣይ በጋራ ዉይይት እንደሚደረግባቸው ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የአፖስቶ - ሀገረ ሠላም አስፋልት መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው
ሐዋሳ፣ የካቲት 20፣ 2017 (ኢ መ አ):- በሲዳማ ክልል ከአፖስቶ እስከ ሀገረ ሠላም ያለው አስፋልት መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው።
መንገዱ በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ባለመኾኑ ነው ጥገናው ያስፈለገው።
የመንገድ ጥገናው 106 ሚሊዮን ብር በጀት ተይዞለት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሻሸመኔ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ ኃይል ነው እድሳት እየተደረገለት የሚገኘው።
የጥገና ፕሮጀክቱ 48 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ አሁን ላይ የተጎዳውን የመንገዱ ክፍል ሙሉ በሙሉ በማንሳት የሰብቤዝ፣ ቤዝኮርስ እና አስፋልት የማንጠፍ ሥራዎችን እየተከናወኑለት ነው።
ይህም በመኾኑ አሸከርካሪዎችን እንዲሁም ኅብረተሰቡን ለእንግለትና ለትራንስፖርት መጉላላት ይዳርጉ የነበሩ ችግሮችን መቅረፍ ያስችላል። አደጋን በማስቀረት ረገድም አስተዋጾዖው የጎላ ነው።
ዲስትሪክቱ በተመሳሳይ ከአለታወንዶ - ዲላ እንዲሁም ከአለታወንዶ - ዳዬ በንሳ ባለው መሥመር ላይ መጠነ ሠፊ የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከመንገድ ግንባታው ጎን ለጎንም በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጠሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን፥ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ እያደረገ ይገኛል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የዲላ - ቡሌ - ሐሮ - ዋጮ መንገድ ፕሮጀክት አፈጻጸም በሚሻሻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ
ዲላ፣ የካቲት 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኦሮሚያ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎችን የሚያገናኘው የዲላ - ቡሌ - ሐሮ - ዋጮ 68 ኪሎሜትር መንገድ ፕሮጀክት ያጋጠሙ ችግሮችን በመቅረፍ አፈጻጸሙ በሚሻሻልበት ሁኔታ ላይ በዲላ ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ ላይ በከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አሥራት የተመራ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን እንዲሁም የጌዲዮ ዞን ከፍተኛ አመራር አካላት ተሳትፈዋል።
በወቅቱ የመንገድ ፕሮጀክቱ ከአንድ ዓመት ከስድስት ወር በፊት ቢጀመርም አሁንም ድረስ እልባት ያላገኙ የወሰን ማስከበር ሥራዎች እንዲሁም የጠጠር መፍጫ ማሽን (ክሬሸር) መትከያ ቦታ በዞን አስተዳደሩ አለመፈቀዱ ጋር ተያይዞ ፕሮጀክቱ ለከፍተኛ ወጪ እና መጓተት መዳረጉ ተመልክቷል።
ለዚህም የባለድርሻ አካላት ትብብር እና ቅንጅት ማነስ ችግሩን በቀላሉ ላለመፈታቱ በመንስኤነት ተነስቷል።
በመኾኑም በአጭር ጊዜ ውስጥ የመንገድ ወሰኑን ከንብረት ነጻ ለማድረግ እና የጠጠር መፍጫ ማሽን (ክሬሸር) መትከያ ቦታ ችግሩን በመቅረፍ የመንገድ ግንባታውን ለማፋጠን እንደሚሠራ መድረኩ ከጋራ መግባባት ላይ ደርሷል።
በዚህ ረገድ የመንገድ ግንባታው በታለመለት ጊዜ ተጠናቅቆ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዲችል የአካባቢው ማኅበረሰብ እና በየደረጃው የሚገኙ የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እና ትብብር እንዲያደርጉ ተጠይቋል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዲዮ ዞን እና በኦሮሚያ ዞን የጉጂ ዞኖችን ያገናኛል። ለግንባታው 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲኾን፥ ወጪው በአረብ ልማት ባንክ፣ በነዳጅ ላኪ ሀገራት (ኦፔክ) እና በፌደራል መንግስት ይሸፈናል።
ዓለም-አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ግንባታውን ያከናውናል። ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ያከናውናል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
በሲዳማ ክልል እየተገነቡ በሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ እና ውይይት ተካሄደ
ሐዋሳ፣ የካቲት 12፣ 2017 (ኢ መ አ):- በከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አሥራት የተመራ ድጋፋዊ የሱፐርቪዥን ቡድን በሲዳማ ክልል እየተገነቡ በሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ እና ውይይት አካሂዷል።
ሚኒስትር ዴኤታው አቶ የትምጌታ አሥራት፤ የድጋፋዊ ሱፐርቪዥኑ ዓላማ ፕሮጀክቶችን በአካል ተገኘቶ ማየት፣ ድጋፍ የሚደረግባቸውን ጉዳዮች መለየት እና ድጋፍ የሚደረግባቸውን ሁኔታዎች ማመቻቸት መኾኑን አስረድተዋል።
የመስክ ምልከታ የተደረገባቸው የዳዬ - ጭሪ - ነንሴቦ እና የዳዬ - ግርጃ - መልካደስታ መንገድ ፕሮጀክቶች በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ የሚገኙ መኾኑን የጠቆሙት ሚንስትር ዴኤታው፣ የሃዌላ - ቱላ -ያዬ -ወተራሬሳ - ወራንቼ ፕሮጀክት ጅማሮው ላይ መቀዛቀዝ ቢታይበትም በክልሉ መንግስት እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በተደረገው የጋራ ጥረት አሁን ላይ በጥሩ መነቃቃት ላይ ይገኛል ብለዋል።
ለዚህም በሲዳማ ክልል በከፍተኛ አመራር ደረጃ እየተደረገ የሚገኘው ድጋፍ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙ የፌደራል የመንገድ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም እንዲፋጠን ማድረጉን ገልጸዋል።
በቀጣይም በሚኒስቴር መ/ቤቱ በኩል የሚደረገው ቴክኒካዊ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ የትምጌታ አሥራት አረጋግጠዋል።
የኮንስትራክሽን ዘርፍ በባህሪው ውስብስብ በመኾኑ ኢንዱስትሪውን ውጤታማ ለማድረግ በየመዋቅሩ የሚገኙ የዘርፉ ተዋንያን በመናበብ፣ በመቀናጀት እና በመተባበር መሥራት ይኖርባቸዋልም ብለዋል።
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው ድጋፋዊ ሱፐርቪዢኑ ያደረገውን ምልከታ አድንቀው፣ በቡድኑ በኩል የተለዩ ክፍተቶች እና ጥያቄዎችን እውቅና በመስጠት በተነሱ ጉዳዮች ላይ በአጭር ጊዜ ምላሽ እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል።
ከዚህም ባለፈ በክልሉ መንግስት እየተደረገ የሚገኘው ሁለንተናዊ ድጋፍ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የደቡብ ሪጅን ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ዳይሬክተር ዳዊት ጥጋቡ (ኢ/ር)፤ በመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ የተመዘገቡ መልካም ውጤቶችን አጠናክሮ ከማስቀጠል እና ያጋጠሙ ችግሮችን በመቅረፍ በኩል ውይይቶቹ እና ምልከታዎቹ ፍሬያማ እንደነበሩ አውስተዋል።
ድጋፋዊ ሱፐርቪዢኑ በቀጣይ ጊዜያትም በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎችም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የአላባ - አለምገበያ - ውልባረግ መንገድ
ከባድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል
ሀላባ ፣ የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የሃላባ ዞንን ከስልጤ ዞን ጋር የሚያስተሳስረው የአላባ-አለምገበያ-ውልባረግ መንገድ በሻሸመኔ ዲስትሪክት ከባድ የመንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል።
ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰትን የሚያስተናግደው የአላባ-አለምገበያ-ውልባረግ መንገድን ደረጃውን በጠበቀ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ለማድረግ በሻሸመኔ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ከባድ የመንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል።
በስካሁኑ የስራ እንቅስቃሴ የአስፋልት ሚክስ ማምረት፣ የቤዝ ኮርስ እና አስፓልት ኮልድሚክስ ማጓጓዝ፣ 450ሜ.ኩ የአስፋልት ፕቺንግ (ኮልድሚክስ)እና የፔቭመንት ሪኮንስትራክሽን ስራዎች የተሰሩ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ክረምት ከመግባቱ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው።
የመንገድ ጥገናው 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ከዚህም ውስጥ ወደ 3 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የመንገዱ ክፍል ከባድ ጥገና ተደርጎለታል። የተበላሹ የመንገድ ክፍሎችን በአስፋልት የመሙላት ስራዎችም እየተሰራ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ በራስ ሀይል (ሻሸመኔ ዲስትሪክት ) የከባድ ጥገና ስራው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ነው።
የጥራት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተጠገነ የሚገኘው ይህ መንገድ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጥ በትኩረት እየተሰራ ሲሆን በመስመሩ በእጅጉ የተጎዳውን ቅድሚያ ሰጥቶ ጥገናውን በማከናወን የትራፊክ ፍሰቱን ምቹ እንዲሆን ተደርጓል።
መንገዱ ካለው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር ከባድ ጥገና እየተደረገለት ነው።
የመንገዱ ተጠቃሚዎች እና አሽከርካሪዎች በበኩላቸው የከባድ መንገድ ጥገና ስራው በመካሄድ ላይ መሆኑ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከመቀነሱም ባሻገር በመንገዱ ብልሽት ይደርስባቸው የነበረውን የተሽከርካሪ መለዋወጫ ወጪ ከማስቀረቱም ባለፈ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በእጅጉ ያሳጥረዋል ብለዋል።
በየአካባቢዎቹ የሚመረተውን በርበሬን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ መሀል ከተማ በማድረስ ገበያውን በማረጋጋት አምራችና ሸማቾችን በሰፊው ተጠቃሚ ያደርጋል።
በተጨማሪም በመስመሩ የሚመላለሱ የድንጋይ ከሰል የጫኑ ተሽከርካሪዎችን በተቀላጠፈ በምቹ መንገድ ያሰቡበት ቦታ ለማድረስ ያስችላል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጎን ለጎን በበርካታ የሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የሚገኙትን ጉዳት የገጠማቸውን መንገዶች በራስ ሀይልና በኮንትራክትሮች የመደበኛ፣ የወቅታዊ እና የከባድ መንገድ ጥገና እያካሄደ ይገኛል ።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
