uk
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Відкрити в Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Канал ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 13 323 підписників, посідаючи 1 756 місце в категорії Транспорт та 2 541 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 13 323 підписників.

За останніми даними від 16 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 90, а за останні 24 години на 8, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 40.85%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 15.40% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 439 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 050 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 17.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 17 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Транспорт.

13 323
Підписники
+824 години
+217 днів
+9030 день
Архів дописів
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚከናወኑ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ ሆሳዕና ፣ የካቲት 26 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የሚከናወኑ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እና የጥገና ስራዎች አፈጻጸምን አስመልክቶ ከክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡ በውይይቱ ወቅት የክልሉን ርዕሰ መስተዳደርን ጨምሮ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን እና ሌሎች የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዞን እና የልዩ ወረዳዎች ዋና አስተዳዳሪዎች ተሳትፈዋል። በወቅቱ በክልሉ በተለያየ የግንባታ ደረጃ ላይ የሚገኙ 14 ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ከእነዚህ ፕሮጀክቶች ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች የዘገዩ ፕሮጀክቶች የሚገኙ ሲሆን ፣ በፕሮጀክቶቹ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮቹን በመለየት እና መፍትሄ በመስጠት አፈፃፀማቸውን በማሻሻል ፕሮጀክቶቹን ማጠናቀቅ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡ ከዚህም ባሻገር ከ1.3 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በክልሉ 849 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸው መንገዶች በጥገና ሂደት ላይ እንደሚገኙ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ፣ አፈፃፀሙም መልካም መሆኑ ተገምግሟል፡፡ በተጨማሪም በክልሉ በግንባታ ሂደት ላይ ከሚገኙ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በቀጣይ ወደ ግንባታ የሚሸጋገሩ 10 ፕሮጀክቶች በዲዛይን እና በግዢ ሂደት ላይ ይገኛሉ፡፡ በምክክር መድረኩ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን በክልሉ በትገበራ ሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን በቀሪ ጊዜያት አፋጥኖ በማስቀጠል አፈፃፀማቸዉን በሚጠበቅበት ደረጃ ለማድረስ ይሰራል ብለዋል፡፡ በዚህም ረገድ በመንገድ ፕሮጀክቶቻችን እያጋጠሙ ካሉ ተግዳሮቶች አኳያ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ መድረክ በኋላ ከክልሉ ጋር የጋራ መርሃ-ግብር በመቅረፅ መተግበር እንደሚገባ የገለፁ ሲሆን በዚህ መልኩ መጓዝ ከተቻለ በፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ላይ ተጨባጭ ለዉጥ ማምጣት ይቻላልም ብለዋል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከክልሉ መንግስት ጋር በትብብር ለመስራት እያሳየ ያለውን የላቀ ተነሳሽነት አድንቀዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በክልሉ በመንገድ መሰረተ ልማት የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ ላደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል። በክልሉ በግንባታ ሂደት ያሉ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተገቢዉን ክትትልና ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል፡፡ ከዚህም አኳያ በፕሮጀክቶቹ አፈፃፀም ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን እየለዩ መፍትሄ መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም በክልሉ በግንባታ ሂደት ላይ ከሚገኙት በተጨማሪ አዳዲስ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እንዲጀመሩ ፍላጎቶች ስላሉ በዕቅድ የሚካተቱበትን ሁኔታ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር በቀጣይ በጋራ ዉይይት እንደሚደረግባቸው ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአፖስቶ - ሀገረ ሠላም አስፋልት መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው ሐዋሳ፣ የካቲት 20፣ 2017 (ኢ መ አ):- በሲዳማ ክልል ከአፖስቶ እስከ ሀገረ ሠላም ያለው አስፋልት መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው። መንገዱ በአገልግሎት ብዛት በመጎዳቱ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ባለመኾኑ ነው ጥገናው ያስፈለገው። የመንገድ ጥገናው 106 ሚሊዮን ብር በጀት ተይዞለት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሻሸመኔ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ ኃይል ነው እድሳት እየተደረገለት የሚገኘው። የጥገና ፕሮጀክቱ 48 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ አሁን ላይ የተጎዳውን የመንገዱ ክፍል ሙሉ በሙሉ በማንሳት የሰብቤዝ፣ ቤዝኮርስ እና አስፋልት የማንጠፍ ሥራዎችን እየተከናወኑለት ነው። ይህም በመኾኑ አሸከርካሪዎችን እንዲሁም  ኅብረተሰቡን ለእንግለትና ለትራንስፖርት መጉላላት ይዳርጉ የነበሩ ችግሮችን መቅረፍ ያስችላል። አደጋን በማስቀረት ረገድም አስተዋጾዖው የጎላ ነው። ዲስትሪክቱ በተመሳሳይ ከአለታወንዶ - ዲላ እንዲሁም ከአለታወንዶ - ዳዬ በንሳ ባለው መሥመር ላይ መጠነ ሠፊ የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከመንገድ ግንባታው ጎን ለጎንም በአገልግሎት ብዛት፥ በድንገተኛ ፥ እንዲሁም በተፈጠሯዊ አደጋዎች ሳቢያ እጅግ የተጎዱ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ መንገዶችን፥ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት እንዲጠገኑ እያደረገ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የዲላ - ቡሌ - ሐሮ - ዋጮ መንገድ ፕሮጀክት አፈጻጸም በሚሻሻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ ዲላ፣ የካቲት 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኦሮሚያ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎችን የሚያገናኘው የዲላ - ቡሌ - ሐሮ - ዋጮ 68 ኪሎሜትር መንገድ ፕሮጀክት ያጋጠሙ ችግሮችን በመቅረፍ አፈጻጸሙ በሚሻሻልበት ሁኔታ ላይ በዲላ ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ ላይ በከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አሥራት የተመራ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን እንዲሁም የጌዲዮ ዞን ከፍተኛ አመራር አካላት ተሳትፈዋል። በወቅቱ የመንገድ ፕሮጀክቱ ከአንድ ዓመት ከስድስት ወር በፊት ቢጀመርም አሁንም ድረስ እልባት ያላገኙ የወሰን ማስከበር ሥራዎች እንዲሁም የጠጠር መፍጫ ማሽን (ክሬሸር) መትከያ ቦታ በዞን አስተዳደሩ አለመፈቀዱ ጋር ተያይዞ ፕሮጀክቱ ለከፍተኛ ወጪ እና መጓተት መዳረጉ ተመልክቷል። ለዚህም የባለድርሻ አካላት ትብብር እና ቅንጅት ማነስ ችግሩን በቀላሉ ላለመፈታቱ በመንስኤነት ተነስቷል። በመኾኑም  በአጭር ጊዜ ውስጥ የመንገድ ወሰኑን ከንብረት ነጻ ለማድረግ እና የጠጠር መፍጫ ማሽን (ክሬሸር) መትከያ ቦታ ችግሩን በመቅረፍ የመንገድ ግንባታውን ለማፋጠን እንደሚሠራ መድረኩ ከጋራ መግባባት ላይ ደርሷል። በዚህ ረገድ የመንገድ ግንባታው በታለመለት ጊዜ ተጠናቅቆ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዲችል የአካባቢው ማኅበረሰብ እና በየደረጃው የሚገኙ የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እና ትብብር እንዲያደርጉ ተጠይቋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዲዮ ዞን እና በኦሮሚያ ዞን የጉጂ ዞኖችን ያገናኛል። ለግንባታው 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲኾን፥ ወጪው በአረብ ልማት ባንክ፣ በነዳጅ ላኪ ሀገራት (ኦፔክ) እና በፌደራል መንግስት ይሸፈናል። ዓለም-አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ግንባታውን ያከናውናል። ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ያከናውናል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በሲዳማ ክልል እየተገነቡ በሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ እና ውይይት ተካሄደ ሐዋሳ፣ የካቲት 12፣ 2017 (ኢ መ አ):- በከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አሥራት የተመራ ድጋፋዊ የሱፐርቪዥን ቡድን በሲዳማ ክልል እየተገነቡ በሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ እና ውይይት አካሂዷል። ሚኒስትር ዴኤታው አቶ የትምጌታ አሥራት፤ የድጋፋዊ ሱፐርቪዥኑ ዓላማ ፕሮጀክቶችን በአካል ተገኘቶ ማየት፣ ድጋፍ የሚደረግባቸውን ጉዳዮች መለየት እና ድጋፍ የሚደረግባቸውን ሁኔታዎች ማመቻቸት መኾኑን አስረድተዋል። የመስክ ምልከታ የተደረገባቸው የዳዬ - ጭሪ - ነንሴቦ እና የዳዬ - ግርጃ - መልካደስታ መንገድ ፕሮጀክቶች በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ የሚገኙ መኾኑን የጠቆሙት ሚንስትር ዴኤታው፣ የሃዌላ - ቱላ -ያዬ -ወተራሬሳ - ወራንቼ ፕሮጀክት ጅማሮው ላይ መቀዛቀዝ ቢታይበትም በክልሉ መንግስት እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በተደረገው የጋራ ጥረት አሁን ላይ በጥሩ መነቃቃት ላይ ይገኛል ብለዋል። ለዚህም በሲዳማ ክልል በከፍተኛ አመራር ደረጃ እየተደረገ የሚገኘው ድጋፍ በክልሉ እየተገነቡ የሚገኙ የፌደራል የመንገድ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም እንዲፋጠን ማድረጉን ገልጸዋል። በቀጣይም በሚኒስቴር መ/ቤቱ በኩል የሚደረገው ቴክኒካዊ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ የትምጌታ አሥራት አረጋግጠዋል። የኮንስትራክሽን ዘርፍ በባህሪው ውስብስብ በመኾኑ ኢንዱስትሪውን ውጤታማ ለማድረግ በየመዋቅሩ የሚገኙ የዘርፉ ተዋንያን በመናበብ፣ በመቀናጀት እና በመተባበር መሥራት ይኖርባቸዋልም ብለዋል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው ድጋፋዊ ሱፐርቪዢኑ ያደረገውን ምልከታ አድንቀው፣ በቡድኑ በኩል የተለዩ ክፍተቶች እና ጥያቄዎችን እውቅና በመስጠት በተነሱ ጉዳዮች ላይ በአጭር ጊዜ ምላሽ እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል። ከዚህም ባለፈ በክልሉ መንግስት እየተደረገ የሚገኘው ሁለንተናዊ ድጋፍ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል። በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የደቡብ ሪጅን ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ዳይሬክተር ዳዊት ጥጋቡ (ኢ/ር)፤ በመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ የተመዘገቡ መልካም ውጤቶችን አጠናክሮ ከማስቀጠል እና ያጋጠሙ ችግሮችን በመቅረፍ በኩል ውይይቶቹ እና ምልከታዎቹ ፍሬያማ እንደነበሩ አውስተዋል። ድጋፋዊ ሱፐርቪዢኑ በቀጣይ ጊዜያትም በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎችም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአላባ - አለምገበያ - ውልባረግ መንገድ ከባድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል ሀላባ ፣ የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የሃላባ ዞንን ከስልጤ ዞን ጋር የሚያስተሳስረው የአላባ-አለምገበያ-ውልባረግ መንገድ በሻሸመኔ ዲስትሪክት ከባድ የመንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል። ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰትን የሚያስተናግደው የአላባ-አለምገበያ-ውልባረግ መንገድን ደረጃውን በጠበቀ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ለማድረግ በሻሸመኔ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ከባድ የመንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል። በስካሁኑ የስራ እንቅስቃሴ የአስፋልት ሚክስ ማምረት፣ የቤዝ ኮርስ እና አስፓልት ኮልድሚክስ ማጓጓዝ፣ 450ሜ.ኩ የአስፋልት ፕቺንግ (ኮልድሚክስ)እና የፔቭመንት ሪኮንስትራክሽን ስራዎች የተሰሩ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ክረምት ከመግባቱ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው። የመንገድ ጥገናው 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ከዚህም ውስጥ ወደ 3 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የመንገዱ ክፍል ከባድ ጥገና ተደርጎለታል። የተበላሹ የመንገድ ክፍሎችን በአስፋልት የመሙላት ስራዎችም እየተሰራ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ በራስ ሀይል (ሻሸመኔ ዲስትሪክት ) የከባድ ጥገና ስራው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ነው። የጥራት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተጠገነ የሚገኘው ይህ መንገድ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጥ በትኩረት እየተሰራ ሲሆን በመስመሩ በእጅጉ የተጎዳውን ቅድሚያ ሰጥቶ ጥገናውን በማከናወን የትራፊክ ፍሰቱን ምቹ እንዲሆን ተደርጓል። መንገዱ ካለው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር ከባድ ጥገና እየተደረገለት ነው። የመንገዱ ተጠቃሚዎች እና አሽከርካሪዎች በበኩላቸው የከባድ መንገድ ጥገና ስራው በመካሄድ ላይ መሆኑ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከመቀነሱም ባሻገር በመንገዱ ብልሽት ይደርስባቸው የነበረውን የተሽከርካሪ መለዋወጫ ወጪ ከማስቀረቱም ባለፈ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በእጅጉ ያሳጥረዋል ብለዋል። በየአካባቢዎቹ የሚመረተውን በርበሬን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ መሀል ከተማ በማድረስ ገበያውን በማረጋጋት አምራችና ሸማቾችን በሰፊው ተጠቃሚ ያደርጋል። በተጨማሪም በመስመሩ የሚመላለሱ የድንጋይ ከሰል የጫኑ ተሽከርካሪዎችን በተቀላጠፈ በምቹ መንገድ ያሰቡበት ቦታ ለማድረስ ያስችላል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጎን ለጎን በበርካታ የሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የሚገኙትን ጉዳት የገጠማቸውን መንገዶች በራስ ሀይልና በኮንትራክትሮች የመደበኛ፣ የወቅታዊ እና የከባድ መንገድ ጥገና እያካሄደ ይገኛል ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads