ch
Feedback
Fairway School plc

Fairway School plc

前往频道在 Telegram

A vision that works for all our kids. ሁሌም ስነምግባር እናስተምራለን። Fairway School PLC

显示更多
5 162
订阅者
-324 小时
-57
-1530
帖子存档
photo content

ፌርዌይ ስኩል የአባዶ የመጀመርያ ደረጃ ቅርንጫፍ 👉ውድ ወላጅች ✅ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል  ተፈተኞች መፈተኛ ጣቢያ መድረስ ያለባቸው 2:00 ሰዓት ስለሆነ ሁሉም ተማሪዎች *6ኛ ክፍል ከሰኞ 8/10/2018 ዓ.ም እስከ 10/10/2018 ዓ.ም እንዲሁም *8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከቀን 11/10/2018 እስከ 12/10/2018 ዓ ም ከጠዋቱ 1:40 ደረስ ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት መግባት ያለባቸው መሆኑን እናሳስባለን ፡፡ 👉ስለዚህ ሁሉም ሰርቪስ ተጠቃሚዎች ከተለመደው ሰዓት 20 ደቂቃ ቀደም ተብሎ የሰርቪስ አገልግሎት የምንስጥ መሆኑን እንገልፃለን።

photo content

photo content

photo content

ፌርዌይ ስኩል የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ ➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ ⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን። መልካም ፈተና🙏

photo content

photo content

photo content

📣 ታላቅ የምስራች ለሰሚት ፌርዌይ ስኩል ቤተሰቦች! 🌟 ውድ ወላጆች፣ የልጆቻችንን ምቾት እና የትምህርት ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ለ2019 የትምህርት ዘመን አዲስ እቅድ ይዘን ቀርበናል፦ 1️⃣ ነባሩ የሰሚት ግቢ፦ ሕፃናት ነፃነት እንዲኖራቸው ሙሉ በሙሉ ለቅድመ-መደበኛ (KG ብቻ) ተለይቷል። 2️⃣ አዲስ  ካምፓስ፦ በሰሚት ሥላሴ ወጂ አካባቢ በ4,500 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው፣ እጅግ ዘመናዊና ምቹ ግቢ ከKG እስከ 8ኛ ክፍል አዘጋጅተናል። ይህ አዲስ ማስፋፊያ የትምህርት ቤታችንን ጥራትና ጠንካራ ስነ-ምግባር ይበልጥ ለማስቀጠል የተደረገ ታላቅ ስኬት ነው። ፌርዌይ ስኩል *“ሁሌም ስነ-ምግባር እናስተምራለን!”* 📞

ለፌርዌይ ስኩል ቤተሰቦች ከትምህርት ፅ/ቤት በተገለጸልን መሰረት ከግንቦት 24 እስከ ግንቦት 26  (ከሰኛ_ዕሮብ) ትምህርት ቤት ዝግ በመሆኑ  ተማሪዎች ቤት የሚቆዩ ይሆናል ። ተማሪዎች ወደ ት/ቤት የሚመለሱት ሐሙስ ግንቦት 27 ፣ 2018 ዓ.ም መሆኑን እያሳወቅን ፣ ተማሪዎች ቤት በሚቆዩበት ሰዓት የፈተና ወቅት የቀረበ በመሆኑ ተማሪዎች ራሳቸውን ለፈተና እንዲያዘጋጁ አስፈላጊውን ድጋፍ እና  ክትትል በማድረግ ሃላፊነትዎን እንዲወጡ እንጠይቃለን ። ት/ቤቱ

FOR KOTEBE PRIMARY DIVISION

photo content

photo content

ለመላው እስልምና ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሓ (ዐረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ፤ መልካም ምኞቱን ይገልጻል። ዒድ ሙባረክ! ፌርዌይ ስኩል

photo content

photo content