ch
Feedback
AASTU_OFFICIAL

AASTU_OFFICIAL

前往频道在 Telegram

Addis Ababa Science and Technology University Official Telegram

显示更多

📈 Telegram 频道 AASTU_OFFICIAL 的分析概览

频道 AASTU_OFFICIAL (@pir2011) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 21 436 名订阅者,在 教育 类别中位列第 9 256,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 566

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 21 436 名订阅者。

根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 802,过去 24 小时变化为 -19,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.73%。内容发布后 24 小时内通常能获得 13.93% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 300 次浏览,首日通常累积 2 985 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0
  • 主题关注点: 内容集中在 aastu, addis, ዩኒቨርሲቲ, ababa, አበባ 等核心主题上。

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Addis Ababa Science and Technology University Official Telegram

凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

21 436
订阅者
-1924 小时
-777
+80230
帖子存档
የ2018 ዓ.ም አራተኛው ሩብ ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ እያካሄደ ይገኛል ሰኔ 26/ 2018 ዓ.ም ++++++++++++++++++++++++++++ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ2
+6
የ2018 ዓ.ም አራተኛው ሩብ ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ እያካሄደ ይገኛል ሰኔ 26/ 2018 ዓ.ም ++++++++++++++++++++++++++++ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ2018 በጀት ዓመት አራተኛውን እና የመጨረሻውን ሩብ ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እየገመገመ ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት በዩኒቨርሲቲው እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ የክንውን ግምገማ መድረክ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች በአራተኛው ሩብ አመት ያከናወኗቸውን ተግባራት በዝርዝር እያቀረቡ ይገኛሉ። በግምገማው ሂደትም በመማር ማስተማር ፤በምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ፤አስተዳደራዊ እና ማህበረሰብ ተኮር ስራዎች በሰፊው እየታዩ ይገኛሉ፡፡ የሪፖርት አቀራረብ ሂደቱ የሚከተሉትን ነጥቦች ማዕከል ያደረገ ነው፡፡ እስካሁን የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶችን መለየት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ፤በስራ ሂደቱ ውስጥ የታዩ ማነቆዎችን በግልፅ በማስቀመጥ መፍትሄዎችን መፈለግ እንዲሁም የወደፊት የትኩረት አቅጣጫዎች ለቀጣዩ በጀት ዓመት (2019 ዓ.ም) ስትራቴጂካዊ ዕቅድ የሚሆኑ ግብዓቶችን መሰብሰብ ነው፡፡ የግምገማ ሂደቱ በዩኒቨርሲቲው አመራሮች እና የስራ ክፍል ሃላፊዎች ንቁ ተሳትፎ እየቀጠለ ሲሆን ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች የሚቀርቡት እነዚህ ሪፖርቶች ተቋሙ ለቀጣዩ ዓመት የሚያስቀምጠውን አቅጣጫ ለመቅረጽ ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል።

Advancing Cyber Resilience and AI Governance Across East Africa: EACA Summit 2026 Underway at AASTU, July 2 2026 Addis Ababa,
+5
Advancing Cyber Resilience and AI Governance Across East Africa: EACA Summit 2026 Underway at AASTU, July 2 2026 Addis Ababa, Ethiopia. The East African Cyber & AI (EACA) Summit 2026 is underway at Addis Ababa Science and Technology University (AASTU) under the theme, "Advancing Cyber Resilience and AI Governance Across East Africa."Co-hosted by AASTU in collaboration with the Ethiopian Information Network Security Administration (INSA), KG Cyber, the University of Gondar, Bahir Dar University, and other partners, the two-day summit brings together Chief Information Security Officers (CISOs), policymakers, researchers, industry leaders, innovators, and cybersecurity professionals to advance regional cooperation on AI governance, cyber resilience, digital trust, and cyber sovereignty. For more information about AASTU, reach us: Website: https://www.aastu.edu.et Facebook: http://facebook.com/aastu.edu.et Telegram: t.me/pir2011 Email: pr@aastu.edu.et | pir@aastu.edu.et Linkedin: https://bit.ly/aastu_officialin

📢 AASTU Newsletter – Volume XIII, Issue IV is Now Available! We are pleased to announce the release of the latest edition of
📢 AASTU Newsletter – Volume XIII, Issue IV is Now Available! We are pleased to announce the release of the latest edition of the AASTU Newsletter (Volume XIII, Issue IV). https://drive.google.com/file/d/1Hs3MMBM_3hk56sqRojFqLoZY2EUj2bE8/view?usp=drive_link

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት https://youtu.be/0GdT1qoAKTw

የመጀመሪ ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና በሰላም እየተሰጠ ይገኛል ሰኔ 23/2018 ዓ.ም +++++++++++++++++++++++++++ የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና በአ
+2
የመጀመሪ ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና በሰላም እየተሰጠ ይገኛል ሰኔ 23/2018 ዓ.ም +++++++++++++++++++++++++++ የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በሰላማዊ መንገድ እተሰጠ ይገኛል፡፡ በመጀመሪያው ዙር ፈተናቸውን እየወሰዱ የሚገኙት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በጠዋት መርሃ-ግብር የእንግሊዘኛ ቋንቋ ፈተናቸውን በበይነ-መረብ (Online) ያጠናቀቁ ሲሆን ተማሪዎቹ ከሰዓት በኋላ ደግሞ የሂሳብ ትምህርትን በተሳካ ሁኔታ መውሰዳቸው ተገልጿል፡፡ ከሰዓት በኋላ የመብራት መቆራረጥ ቢያጋጥምም ዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ፈተና በመብራት ሃይል አቅርቦት ምክንያት እንዳይስተጓጎል የራሱን ጀኔሬተር በመጠቀም ተማሪዎች ፈተናቸውን በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቅቁ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ፈተናው ያለምንም እንከን እንዲከናወን የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ከትምህርት ሚኒስቴር የተወከሉ የፈተና አስተባባሪዎች፣ የአይሲቲ ባለሙያዎች እንዲሁም የፀጥታ አካላት በቅንጅት እየሰሩ ይገኛሉ። ለተፈታኝ ተማሪዎች ሁሉ መልካም ውጤትን እንመኛለን! ስለ ዩኒቨርሲቲያችን ዝርዝር መረጃ ለማግኘት የሚከተሉትን አማራጮች ይጠቀሙ:: ድረ-ገፅ: https://www.aastu.edu.et ፌስቡክ: http://facebook.com/aastu.edu.et ቴሌግራም: t.me/pir2011 ኢሜይል:pr@aastu.edu.et/pir@aastu.edu.et ዩቲዩብ :youtube.com/@aastu_official7418 ኤክስ (ትዊተር): x.com/aastu_addis ሊንክድኢን: https://bit.ly/aastu_officialin

https://ethiopianreporter.com/157359/ ዩኒቨርሲቲዎች ከንድፈ ሐሳብ ባሻገር

Dr. Dereje Engida with the Reporter Newspaper https://www.thereporterethiopia.com/51514/

photo content

የዩኒቨርሲቲው ከምንጊዜውም በላይ ተቋማዊ ስኬቶችን፣ የምርምር አቅም እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ማሳጉ ተገለፀ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም +++++++++++++ በአስራ ሁለተኛው ዙር የተማሪዎች ምረቃ
+5
የዩኒቨርሲቲው ከምንጊዜውም በላይ ተቋማዊ ስኬቶችን፣ የምርምር አቅም እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ማሳጉ ተገለፀ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም +++++++++++++ በአስራ ሁለተኛው ዙር የተማሪዎች ምረቃ መርሃ-ግብር ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደረጀ እንግዳ በንግግራቸው እንደገለጹትተቋሙ አሁን ላይ ከዲግሪ ማሰልጠኛነት ባሻገር፣ ሀገራዊ የልማት ግቦችን በመምራት ላይ የሚገኝ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ማዕከል መሆኑን ገልፀዋል ። በዚህም ዩኒቨርሲቲው በኢትዮጵያ ብቸኛው በአፍሪካ የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኔትወርክ (Afritec) 10ኛው አባል ዩኒቨርሲቲ በመሆን መመዝገቡ በዓለም አቀፍ መድረክ ያለውን ተወዳዳሪነት አመላካች ነው። ዶ/ር ደረጀ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከቻይና እና ከፈረንሳይ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር እየሰራ ያለው የጋራ ላቦራቶሪ ግንባታ እና የፈጠራ ስራዎች፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ከወረቀት ወደ መሬት ለማውረድ የሚደረግ ቁርጠኝነት ውጤት መሆኑን አስታውሰዋል። ዩኒቨርሲቲው በዘንድሮው ዓመት ብቻ 5 የአዕምሮ ንብረት ሰርተፍኬቶችን ማግኘቱ፣ 12 የፈጠራ ውጤቶች በምዝገባ ላይ መሆናቸው እና 9 ስታርትአፖች ወደ ኢንዱስትሪ ሽግግር መሸጋገራቸው ዩኒቨርሲቲው ለኢንዱስትሪው ዘርፍ "የእውቀት ማዕከል" መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ አመላክተዋል። ዶ/ር ደረጀ በዕለቱ ለተመራቂ ተማሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲው የሰጣችሁ እውቀት መሰረት እንጂ የመጨረሻ ግብ አለመሆኑን በመግለፅ ፊታችን ያለው ዓለም በተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ እና ባልታሰቡ ፈተናዎች የተሞላ በመሆኑ ተመራቂዎች የዕድሜ ልክ ተማሪ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል። Read More https://www.facebook.com/100068993984600/posts/1329964745979979/?app=fbl

ከተመራቂዎች አንደበት https://www.youtube.com/watch?v=QZGJ6Yd7QT8

ከዲግሪ ወረቀት ባሻገር ለኢትዮጵያ አዲስ የፈጠራ ምዕራፍ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም +++++++++++++++++++++++++++++ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሼቴ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በአዲ
+6
ከዲግሪ ወረቀት ባሻገር ለኢትዮጵያ አዲስ የፈጠራ ምዕራፍ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም +++++++++++++++++++++++++++++ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሼቴ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ መርሃ-ግብር ላይ ተገኝተው በአስተላለፉት መልዕክት ዘመናዊው ዓለም በእውቀት፣ ፈጠራ እና ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጸዋል። ክብርት አየለች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ስራዎች ጥራትን፣ ተጠያቂነትን እና ከኢንዱስትሪ ጋር ያለውን ትስስር ማጠናከራቸውን አስረድተዋል። ተመራቂዎች የዲግሪ ባለቤት ከመሆን ባሻገር የማህበረሰብን ችግር የሚፈቱ ስነ-ምግባር የታከለበት እውቀት ያላቸው እና ለውጥ አምጪዎች እንዲሆኑ አደራ ብለዋል። ክብርት ወ/ሮ አየለች የማህበረሰብን ችግር ሳይፈታ የቀረ እውቀት ለሀገር ብልፅግና ምንም የማይፈይድ መሆኑን በመግለፅ እውቀት ፋይዳ የሚኖረው የማህበረሰብን መሰረታዊ ችግሮች እና የጤና ተግዳሮትን ሲፈታ እንዲሁም አዲስ የኢኮኖሚ ተስፋ ሲፈጥር ብቻ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በመጨረሻም ክብርት ወ/ሮ አየለች በዚህ የምረቃ መድረክ ላይ እውቀት ከስነ-ምግባር ከተነጠለ ከንቱ ልፋት መሆኑን በማስታወስ ተመራቂዎች በቀጣይ የስራ ህይወታቸው እውቀትን ስነ-ምግባር በማጣመር ሃገራቸውን እንዲያገለግሉ ጠይቀዋል፡፡

ሳይንስና ቴክኖሎጂ የሃገራችን ተግዳሮቶች መፍቻ ቁልፍ ነው ሰኔ 21/2018 ዓ.ም +++++++++++++++++++++++++++++ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም የተካሄደው የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ
+6
ሳይንስና ቴክኖሎጂ የሃገራችን ተግዳሮቶች መፍቻ ቁልፍ ነው ሰኔ 21/2018 ዓ.ም +++++++++++++++++++++++++++++ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም የተካሄደው የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ከተለመደው የዲግሪ አሰጣጥ ስነ-ስርዓት በተለየ መልኩ በፈጠራ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳድረው አሸናፊ የሆኑ ተማሪዎች ተሸላሚ የሆኑበት ነበር፡፡ ዩኒቨርሲቲው ያስመረቃቸው ተማሪዎች መፅሐፍ የዘጉ ሳይሆን የችግር መፍቻ ቁልፎችን የያዙ የዘመናችን የቴክኖሎጂ አርበኞች ናቸው። በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ዋና ዳይሬክተር እና የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ እንዳስተላለፉት ምረቃ ማለት "የእውቀት ማህደር መዝጊያ ሳይሆን ለሀገር ግንባታ የሚጠቅም የዲጂታል መሳሪያዎች መክፈቻ ቁልፍ ነው፡፡ ክብርት ወ/ሮ ትዕግስት በንግግራቸው ማሳረጊያ ተመራቂዎች የዓለምን ዲጂታል ሽግግር (በተለይም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና ዳታ ሳይንስን) እንደ መሳሪያ በመጠቀም የኢትዮጵያን ተግዳሮቶች በሃገር በቀል እውቀት መቅረፍ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በመጨረሻም ክብርት ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ለተማሪዎች ከዚህ ቀን በኋላ የምትጠየቁት “ምን ተማራችሁ?' ሳይሆን 'በተማራችሁት ምን ሰራችሁ?” የሚል ነው:: ስለዚህ ተመራቂ ተማሪዎች ሀገራችሁን በፈጠራ እና ቴክኖሎጂ እንዲለውጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

Repost from Tikvah-University
#AASTU የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 1,246 ተማሪዎች አስመርቋል። ዩኒቨርሲቲው በ18ኛ ዙር ያስመረቃቸው፦ ➫
+2
#AASTU የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን 1,246 ተማሪዎች አስመርቋል። ዩኒቨርሲቲው በ18ኛ ዙር ያስመረቃቸው፦ ➫ 1,043 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ➫ 182 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ ➫ 21 ተማሪዎች በሦስተኛ ዲግሪ @tikvahuniversity

photo content
+1

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 12ኛ ዙር ተመራቂዎቹን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም +++++++++++++++++++++++++++ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨ
+9
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 12ኛ ዙር ተመራቂዎቹን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ ሰኔ 20/2018 ዓ.ም +++++++++++++++++++++++++++ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ዛሬ በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመረቀ። በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ዋና ዳይሬክተር እና የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሼቴን ጨምሮ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ፣ የተመራቂ ተማሪዎች ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የዕለቱ የክብር እንግዳ የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት፣ ምረቃ የትምህርት ጉዞ ማጠናቀቂያ ሳይሆን፣ በእውቀት የተደገፈ አዲስ የሙያ ህይወት መጀመሪያ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም ዓለም በከፍተኛ ፍጥነት በዲጂታል ቴክኖሎጂ እየተቀየረች መሆኑን በመጥቀስ ተመራቂዎች በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)፣ በዳታ ሳይንስ እና ተያያዥ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መስኮች እራሳቸውን በየጊዜው ማዘመን እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በተለይም ተመራቂዎች የቀሰሙትን የሳይንስና ቴክኖሎጂ እውቀት በመጠቀም፣ የሀገራችንን ተግዳሮቶች ሃገር በቀል በሆኑ መፍትሄዎች የመፍታት አቅም ሊኖራቸው እንደሚገባ የገለጹት ክብርት ወ/ሮ ትዕግስት፣ ያሉንን ችግሮች እንደ ትልቅ የፈጠራ እድል በመውሰድ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ እድገት ጉልህ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል።

photo content
+7