ch
Feedback
📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

📚📚ቤተ__መፅሀፍት📖📗🧾📜

前往频道在 Telegram

📚📚እንኳን በደህና መጡ📖📗🧾 ➥ እዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ የ አማርኛ እና እንጊሊዘኛ ..... መፅሀፍትን በ 📙 Pdf እና ትረካዎችን እና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮችን ያገኛሉ። 📖 ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል‼️ B-) :-መረዳዳት ቢኖር ሁሉም ቢተባበር 100K ይደርስ ነበር ። For any comment @Meki3

显示更多
2 159
订阅者
+324 小时
+197 夊
+3530 夊
帖子存档
    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣5⃣ ........በንዴትም ስሜታዊ ሆኜ በጣም ተናድጄ ነበረ። የበለጠ ያናደደኝ ደግሞ መልሱ ዝምታ መሆኑ ነው ። በእሱ ጉዳዬ እንባዬ አሽቃባጭ ናት መቆጣጠርም አልችልም ዝም ብሎ ነው የሚፈሰው !!!! የዛኔም የድሮ ፍቅራችን ትዝ አለኝና አመለጠኝ ። ግን ድክመቴ መሆኑን ለሱ ማሳየት አልፈለኩኝም !!! የመጨረሻዬ ነው ብዬ ወስኜ ፊቴን አዙሬ ልሄድ ፊቴን ሳዞር " የኔ እናት ያላንቺ መኖር አልችልም እኮ " ብሎ እጄን ይዞ ወደራሱ ጎተተኝና እቅፉ ግንባሬን ጉንጬን እያገላበጠ ይስመኝ ጀመር ። የመጨረሻ ነው ብዬ ወስኜ የነበርኩ ልጅ እሱ እቅፍ ውስጥ ስገባ ሁሉንም ነገር ረሳሁት ከእቅፉ ሳልወጣ በቀረሁ ብዬ ተሐኘሁ!!!! ለምን እሺ ቆይ ለምን ??? አትወደኝም ??? ያሁላ ቃል ተግባር ውሸት ነበር ??? አልኩት እዛው እቅፉ ውስጥ እየሞኩኝ ። " አቡ ከእራሴ በላይ እንደማፈቅርሽ ለኔ ህይወቴ እንደሆንሽ ታቂያለሽ እኮ " አለኝ ። አውቅ ነበር እኮ ግን ደግሞ ጥለከኝ ሄድክ በጣም ጎድተከኝ ነበረ ለምን ጥለከኝ ሄድክ ?? አልኩት እንባዬን እየጠራረኩና ከእቅፉ እየወጣሁኝ ። " እባክሽ ተረጂኝ አዎ ጥፋት ነው ግን አንድም ላንቺ ብዬ ነው አንድም ደግሞ አባቴን መስማት ነበረብኝ !!" አለኝ ። ለኛ ፍቅር ያ በቂ ምክንያት አይሆንም ሊሆንም አይችልም !!!! ለአንቺ ብዬ ማለት ??? አልኩት በእልህ እንባዬን እያፈሰስኩኝ ። " በቃ አባቴ የኔና አንቺን ግንኙነት አልፈቀደልኝም ነበር እሱ ደግሞ ማንንም አይሰማም ካስታወሺ የመጀመሪያ የፍቅር ጊዚያችን ቀን ቤት መተሽ ስሸኝሽ በመኪና  ወደኛ የመጣው ሰው አባቴ ነበር !!! እናም በአንቺ አስፈራራኝ እኔም አሁን ነው የተረዳሁት አዎ ስህተት መሆኑ ገብቶኛል እንደዛ ማረግ አልነበረብኝም !!!" አለኝ ። በርግጥ ለኔ በቂ አልነበረም !!! እኔ ማንም ባይደግፈኝ እንኳን እሱን አምነውም እደግፈውም ነበር !!! " በቃ በስርአት እንዳስረዳሽ ፍቀጂልኝ ትንሽ ጊዜ ስጪኝ አንቺን ይቅርታ ለመጠየቅ ብዬ ምንም ነገር ባደርግም አይቆጨኝም አደርገዋለሁኝም !!" አለኝና ምላሼን ሳይጠብቅ ጎትቶ አቀፈኝ ። " እመኚኝ እናቴ አንቺን ልጠላሽ አልችልሞ " ብሎ አይኔን ግንባሬን ጉንጬን እየሳመ ፀጉሬን ያሻሸኛል !! ከዛ በላይ ውጪ ተቃቅፈን መቆም አልቻልንም እናቴና  አለምዬ  ተከታትለው ከቤት ወጡ ። አለምዬ በአንዴ ፊቷ በደስታ በራ እናቴ ግን እኔን ጎድቶባታል ይቅርታ ለማድረግ ቀላል አይሆንም !!! ይልቁንም የበለጠ ተናደደች ። " ልጄ ሰዎች ሲመጡ መቀበል ከሆነ ትናቂያለሽ !!" አለችኝ ተኮሳትራ ። በሰአቱ ምንም ልላት አልቻልኩኝም ። እማዬ ብቻ ብዬ በአሳዛኝ ፊት አየዋት  ። " መስኪ ይቅርታ በጣም " አላት እኔን ለቆ እሷን እየተመለከተ " ተው ልጄ እኔ ጠልቼክ አደለም ግን አንዳንዴ ይቅርታ የማያስተካክላቸው ብዙ ነገሮች አሉ "  አለችው በቁጭት ። " አቃለሁ ግን ለሷ ብዬ ነው እኮ " አላት ። " አይ ልጄ ነው ብለክ ነው .......ለማንኛውም ኑ ግቡና ቁጭ በሉ ደክሟችዋል "" አለችውና ወደ ቤት ገባች ። ገብተን ተቀምጠን በደከመ መንፈስ ምግብ ለመብላት ተዘገጃጅተን ቁጭ ስንል በራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ማለት በሚቻል ሁኔታ  በጣም በከባዱ በሩ ተንኳኳ ።??? እናቴ ክው ብላ ከተቀመጠችበት ተነስታ ብድግ ብላ አየችን ። " ቆይ ቆይ እኔ ልክፈት " ብሎ ቤኪ ተነስቶ በሩን ከፈተ ......... . . . ይቀጥላል #ክፍል_2⃣6⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣4⃣ ........ከቤት ሲወጡ ተገጣጠምን ። አለምዬ እናቴ ብቸኝነት እንዳይሰማት ስለምታስብላት ሁሌ እየመጣች አብራት እንደምትውል ሁሌ እናቴ ትነግረኛለች ይሄው ዛሬም አብረው ናቸው !! ወደ ዋናው ወሬ ስገባ በረከትን ከስንት ጊዜያት ቡሀላ ማየት ለኔ በጣም ከባድ ነገር ነበር !!!!!! ሳየው ድርቅ ብዬ ነው የቀረውት ። ልክ እንደኔ ደግሞ እናቴና አለምዬም ድርቅ ብለው አንዴ እኔን አንዴ ቤኪን ማለቴ በረከትን እያፈራረቁ ያዩናል ። አለምዬ ቀድማን ባነነችና ሮጣ ቤኪን አገላብጣ አቅፋ ሳመችውና ቀጥታ ወደኔ መታ እንደ እናት ያለ ስስት ሳመችኝ ። ቀጥላ እናቴም መታ በየተራ ሳሙኝ ። እኔ አይኔን ከበረከት ላይ መንቀል አልቻልኩም እሱ ደግሞ አይኔን ላለማየት መሬት ላይ እይታውን አድርጎ ጥፋቱን ማመኑን ለማሳየት እየሞከረ ይመስላል !!! " መች ነው የመጣችሁት ሁለታችሁም ሳደውሉ መጣችሁ እኮ " አለች አለምዬ ወደ ሁለታችንም እየተመለከተች ። እኛ ለመመለስ አቅሙ አልነበረንም ። በዛን ሰአት ትንሽ ቃል ማውጣት ለኔ ከባድ ሆኖብኝ ነበር !!!! እውነት ለመናገር በጣም ናፍቆኛል እጄን እያስቆምኩት እንጂ እህኔ የማገኘው የሱ አንገት ላይ ነበረ ። አዎ በጣም ተናድጄበታለሁ ግን እኔ ከሱ ይቅርታ የምትል አራት ፊደል ብሰማ  ለማቀፍ ዝግጁ ሆኜ እየጠበኩት ነው ። እናቴ በቤኪ በጣም እንደተናደደች እናውቃለን ፊቷም ይናገራል !!! ታዲያ ያ ጠልታው ሳይሆን እንደ ማንኛዋም እናት ለልጇ ስለምታስብ ነው !!!!, አለምዬም ሁለታችንንም እኩል መጠየቅ ልክ እንዳልሆነ ቢገባት ወደ ቤኪ ቀርባ " ልጄ መች መተክ ነው ሳትነግረኝ ለምን ?? ግን ደስብሎኛል ስላየሁክ " አለችው ። " የሆነች .." ሲል ከንፈሮቼ መንቀጥቀጥ ጀመሩ ድምፁን ከሰማሁኝ በጣም ቆየሁ !!! ገና የሆነች ብሎ ሲል ስሰማው ከንፈሬ መንቀጥቀጥና ምላሴ መንቀጥቀጥ ጀመረ ። ትርፍ ቃል እንዳላወጣ ፈርቼ በእጄ አፌን ሸፈንኩኝ ። አለምዬ ነገሮች የመረዳት አቅም አላት!!! እማዬ ቆማ ለመስማት ስትዘገጅ አለምዬ "ፐየድሽው ነገስ " ብላ አሯሮይዛልኝ ገባች ። እንድናዘራ ብላ እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ የኔና የሱ መፋጠጥ ሆኖ  ነው  እንጂ ለኛ ብላ ነው ። እሱም ዝም ኤኔም ዝም ሆነ ነገሩ ። አንዳንዴ እኔን ስለሰጠው ማመስገን ነበረበት እላለሁኝ !!! ከድሮም ጀምሮ በራሱ ጥፋትም ብንደባበር እኔ ካላወራሁት አያወራኝም ነበር ። ቤኪ የሚል ቃል ብቻም ብትሆን ከኔ ከሰማ ይቅርታ ጠይቆ አባብሎ ምናም ይታረቀኝ ነበረ ። አሁንም እኔን እየጨበቀ መስሎ ስለተሰማኝ ደህና ነህ ? አልኩት እንደምንም ሀይሌን  አሰባስቤ ። በአሁኑ ግን ያን ያህል ቀላል አልነበረም ቀና ብሎ አይኔን ተመለከተና መልሶ አቀረቀረ ።??!! ያቺን ቃል ለማውጣት ለፍቼ ነው ። ክብሬን ትቼ ነው መጎዳቴን የደረሰብኝት በደል ያስለቀሰኝን እንባ መልሼ እካስበታለሁኝ ብዬ አስቤ ነበር !!!! ዝም ስላለ ከዛ በላይ እሱን መጠበቅ ሰልችቶኛልም መንገድ ቀይሬ ቀጥ ወደ ቤት ልገባ ስል " በማርያም ይቅርታ !!" አለኝ በአጭሩ ። ስጠብቀው የነበረ ቃል ነው !!!! ኡፍ እንዴት ደስ እንዳለኝኝኝኝ !!!!! ነገር ግን ይቅርታውን ፈለኩ እንጂ ለኔ በቂ አልነበረም ። ፊቴን አጨማድጄ እጅ በደረት እያደረኩ ወደሱ ቀረብኩኝ ። ላልጨክንበት ነገር አጉል እን አክተር ሲያረገኝ እኮ ነው !!!!!🙄🙄 ልክ ወደሱ ስቀርብ ቆፍጠን ያልኩበት እየከዳኝ መጣ ። እንደምንም ራሴን አሳምኜ ከሁሉም በፊት ነገሮችን ሊያስተካክልልንም ሊቋጨውም የሚችለው አንድ ነገር ብቻ ነው !! አልኩት "እሺ ምን ምን ላድርግልሽ " አለኝ ። ለምን አደረከው ??? ለምን ጥለከኝ ሄድክ ላንቺ ብዬ እንዳትለኝ እውነተኛ ምክንያትህን ንገረኝ ........ አልኩት በንዴትም ስሜታዊ ሆኜ ነበር ?????... . . . ይቀጥላል #ክፍል_2⃣5⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣3⃣ ......... አይኗን ተክላ ቀረች ። ለምን እንደሆነ ባላቅም ልጅቷን ለማየት በጣም ጓጉቼ ነበር። ቀጥታ ሄጄ ካሜራውን ከጄሪ እጅ ላይ ወሰድኩት ። ያለመከራከር ካሜራውን ለቃልኝ ከቦታው ለቃ ሄደች ። ጭራሽ ባላሰብኩትና ባልጠበኩት መንገድ  ካሜራውን የሞላው የኔ ፎቶ ነበር ። ራሴን እስከምጠራጠር ድረስ እየቀያየርኩ ማየት ጀመርኩኝ ። ፎቶዎቹ ታስበውበት ተዘጋጅተውበት የተነሳዋቸው  ይመስላሉ !!!!! የገረመኝ ደግሞ ያን ያህል ቆንጆ ነኝ እንዴ ያስባሉኝ ፎቶዎች አሉ አብዛኞቹ ግን ላይብረሪ ካፌና ቤተ ክርስቲያን ናቸው ። የመአት ፎቶዎች ናቸው ሁሉንም አይቼ ስጨርስ ቀና ብዬ ምንድነው በሚል አስተያየት አየውት ። " ምነው ? ቆንጅዬዋ " ብሎ  ፍጥጥ ብሎ አየኝ ። በሰአቱ ካሜራውን ከስክሼ ብሰብረው ደስ ይለኝ ነበር ወዲያው ግን ቤኪ ምን ያህል ውድ እንደሆነ ነግሮኝ ስለነበር ተረጋግቼ አስቀመጥኩትና እየሮጥኩ ወደ ዶርም ሄድኩኝ ። ዶርም ላይብረሪ መናፈሻ ወክ ማድረጊያችን ጋር ብቻ ሁሉም ቦታ ጋ ፈለኳት ጄሪን ማግኘት አልቻልኩም ። ብዙ ነገሮችን እንደምታገናኛቸው እርግጠኛ ስለነበርኩኝ ነው!! ምክንያቱም ደግሞ ከዚ በፊት ታይው ስላትም ስለነበር ተቀራርበንም ስላየች መጠርጠሯ አይቀርም  !! እኔም በሷ ቦታ  ብሆን የማስበው ነገር ስለሆነ ፈርቻለሁ የት እንደማገኛት አላውቅምም ! ሙሉ ቀኑን ጠፍታብኝ ውላ ከስንት ፍለጋና ዙረት ቡሀላ ወንበሮቹ ጋር ተቀምጣ አገኘዋት ። ሮጬ ሄጄ እግሯ ስር ቁጭ ብዬ ጄሪ እኔ እንደዛ አስቤ አላቅም አንቺ እንዳሰብሽው አይደለም !!! አልኳት ። ዝም ብላ ተመለከቸችኝና " እውነት ነው አቡ ወንድሜ አንቺን ይወድሻል እኔ በረከትን እወደዋለሁ አንቺ ደሞ እሱን ትወጂዋለሽ  እንደዛ ነው አይደለ !!!!! በጣም የተወሳሰበ ነገር ነው !!!!" አለችኝ እንባ እየተናነቃት ። ከእራሴ በተማርኩት መሠረት በረከትትን እንደምትወደው ያስታውቅባታል ግልፅ ነገር ነው የሚሆነውም !!!! ከጄሪ ጋር ጓደኛሞች ብንሆንም ጎበዝ ተማሪ ስለሆንኩኝ ፍቅር የማውቅ አይመስላትም ጠይቃኝ አታቅም እንጂ ቤኪን ምን ያህል እንደምወደው ብታውቅ እንዲ ባላለችኝ ነበር !!!! በሰአቱ ምን ብዬ ለሷ እንደማስረዳም አላወኩኝም ግራ የተጋቡ ቃላቶች አንደበቴን ይዘውት ማውራት አቃተኝ ። ዝምታዬ ደግሞ ሽንፈት መሠለት ። እሷ ልክ እንደሆነች ስላሰበች በረጅሙ ተንፍሳ ከተቀመጠበችበት ተነሳችና " አታስቢ ጓደኝነታችን አይፋቅም ። የጎዳኝ ልብሽ እንጂ አንቺ አደለሽም ብድሬን ብመለስም ለልብሽ እንጂ ለአንቺ አይደለም እሺ "" ብላ በከባዱ አስፈራርታኝ ሄደች ።??? በሰአቱ ተከትዬ ላብራራላትም አልፈለኩኝም !! የተነሳችበት ቦታ ላይ ተክዤ ተቀምጬ እያለ በረከት ከፊት ለፊቴ ቆሞ መልእክቱና ትርጉሙ ያልገባኝ የሆነ ቅኔያዊ አስተያየት አይቶኝ ሄደ ። ከዛ ቀን ቡሀላ ጄሪን ብለምናት እንኳን አብራኝ ልትሆን አልቻለችም ኢዩኤል እኔን መከተል .....ጄሪ በረከትን መከተል .... በረከት እኔን መከታተል ተያያዝናት  በመጣን ቁጥር ራሳችን አደከምን ።እንደምንም እየተማርን ግማሽ  አመት ሆነን ። የፋሲካ በአል ደረሰ ። ወደ ቤት መሄድ ባልፈልግም እዛ ሆኜ የተበረዘ  ጭንቅላቴን ፈታ ለማድረግ ብዬ ወደቤት ለመሄድ ፍቃድ አፃፍኩኝ። ጄረ ይቅር ማይባል ቂም ይዛብኛለች ። ከሁሉም እየሸሸሁ የቀሩትን ቀናት አሳለፍኩኝና ወደ ቤት ለመሄድ እቃዬን ቆላልፌ የምፈልገውን ይዤ ወጣሁኝ ። ቤት እስክደርስ በጣም ቸኩዬ ነበር ከወራት ቡሀላ እናቴን ላያት ስለሆነ በጣም ደስ ብሎኛል ። ብር ያን ያህል ስለማላጠፋ ከላከችልኝ ብር ላይ አውጥቼ የሆነ የሆነ ነገር ገዝቼ ይዤ ሄድኩኝ ። ውስጥ እስከምገባ አላደርስ ብሎኝ እማ እማዬ እያልኩ ወደ በሩ ስጠጋ በረከት ከፊት ለፊቴ ድቅን ሲል እናቴና አለምዬ ከቤት ውጥት ሲሉ ተገጣጠምን ......... . . . ይቀጥላል #ክፍል_2⃣4⃣

10 like or emoji I will send at next part 23 🫠

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣2⃣ ............ስትለው ዞር አለ ። ክው ነው ያልኩት ምክንያቱም  ከማይሆን ጢባራም ሰው ነው ፍቅር የያዛት ። ለእራሴ እኔ ከሱ ራኩ ብዬ ስደሰት የበለጠ አቀረበችብኝ ። ደግሞ ለሷ የማይሆን ሰው እንደሆነ ተሰማኝ ። እሱም ሲያየኝ ደንግጧል እኔም እያፈጠጥኩበት ስታየን ነገሮች ያልገቧት ጄሪ ሁለታችንንም በደንብ አቀባብላ አየችንና " ትተዋወቃላችሁ ??" አለችን በእጇቿ ወደ ሁለታችንሞ እየጠቆመች። እኩል እንደመባነን አልንና  እሷ ላይ አፈጠጥን ። እኔ ከመናደዷ በፊት ምን ብዬ ላረጋጋት ብዬ እየተጨነኩ እያለ " ጠራችሁኝ " አለን ከተቀመጠበት ተነስቶ ። ደስ የሚለው ጄሪ ነገር አታረዝምም ቶሎ ነው የምትረሳው ወዲያው ወደ ፍቅሯ ተመለሰች ። " አ አ አዎ ፈልገንህ ነበር " አለችው  ከመፍራቷ ብዛት እጆቿን እያፋተገች። እንደዛ ስትሆን አይቻት አላቅም ነበረ እና ምን ያህል እንደወደደችው ግልፅ ነው !!! " እሺ አቤት " አለ ወደኛ እየቀረበ ። በረከት ተብዬው ከሁለታችንም መልስ እየጠበቀ በየተራ ያየናል ጄሪ እኔን ታየኛለች ሁለቱም ሲያፈጡብኝ ግራ ገብቶኝ እንዴ እኔ ምን ላድርግ አልኳቸው ። ቀስ ብላ ወደኔ ተጠጋችና ... " በእናትሽ እኔ ልሂድ አንቺ ምን ያህል እንደምወደው አጋነሽ ንገሪልኝ አደራ "" ብላኝ ምላሼንም ሳትጠብቅ እየሮጠች ሄደች ። ምን ብዬ ልንገረው ካልነገርኩት ደግሞ ታኮርፈኛለች በዛ ላይ ይከፋታል እያልኩ ብቻዬን ሳወራ " በጣሞ ቆንጆ ነሽ " ብሎ የመናገር ፍላጎቴንም በአንዴ ነጠቀኝ ። እ ?? አልኩ ደንግጬ ወደዃላ እየሸሸሁ " በጣም ነው የምታምሪው እንደምታቂ እርግጠኛ ነኝ " አለ ትንሽ ፈገግ ብሎ ። ከሱ በፊት የለመድኩት ንግግር ነው የኔ ቤኪ እንደዛ ሲለኝ ብቻ ነው የሚያስደስቸኝ !!! ግን አልዋሽም ደንግጫለሁኝ ። ያምሀል እንዴ ለቁም ነገር ፈልገንህ ነው አትጃጃል አልኩት በጣም ተኮሳትሬ " ምን አልኩ ታዲያ እኔ  ልብ የሚያቀልጥ ውበት እንዳለሽ ነው የነገርኩሽ ተሳሳትኩ ቆንጆ " አለኝ ። ሲታይ እንደዛ ጅል አይመስልም !!! መጀመሪያ የፈራውላት ኮስታራ ስለነበረ እንቢ ይላታል ይኮራባታል ብዬ ነበር !!!!! በሰአቱ ተናድጄ ስታስጠላ ጅል አትሁን እንደ ወንድ አክት አድርግ ብዬ በቆመበት ጥዬው ሄድኩኝ ። ወደ ዶርም ሄይኩኝ ገና በሩን ከፍቼ ስገባ ከአልጋ ላይ ተወርውራ መጣችና " እ ምን አለ ? እሺ አለ?? አወቀኝ ??? ስከተለው እንደነበር ያቃል አ??? ምን አለ ቶሎ ንገሪኝ ....." በደቂቃዎች ውስጥ በጣም ብዙ ቃላትን አወጣች !!!!! በዛ ላይ ስፍስፍ ያለ የጓጓ ፊት እያሳየችኝ ነበር !!!! የሷን ፊት አይቼ ላስከፋት አልችልም መዋሸት ሳልፈልግ ለሷ ብዬ አላቅም ላስብበት አለኝ አልኳት ምን ለማለት እንጀፉኩም ግልፅ አልሆነልኝም !!!!! " ያ ማለት እኮ 90% እሺ ሊሆን ይችላል በቃ እሱም አይቶኛል ብላ ፍንድቅድቅ አለች !!! በደስታ የምትሆነውን አሳጣት ጉዷን አልሰማች !!!! የዛ ቀን እሷን ላለማስከፋት ብዬ በዋሸዋት ውሸት እኔንም እሷንም ማይሆን ነገር ውስጥ አስገባሁኝ !!! ከዛ ቀን ቡሀላ ጄሪ መቶ እስኪያወራት መጠበቅ ጀመረች ቀን በቀን እሱ ዙሪያ እየጎተተች ታዞረኛለች ። ለተከታታይ ሁለት ሳምንት አካባቢ ያለመሠልቸት ፈለገችው !!!! የሆነ ቀን ግን ተስፋ ቆረጠች መሠለች በጣም ከፍቷት ሙሉ ቀን ተኝታ ዋለች ። አጠገቧ ቁጭ ብዬ እያባበልኳት እያለ ብድግ አለችና " አቡ እህትሽ አይደለሁ ትወጂኝ የለ ሄደሽ አንዴ ብቻ ደግመሽ አውሪው  እባክሽ በእናትሽ ...." ብላ ለመነችኝ ። መጨከን አልቻልኩኝም ከእናቴ እና ከአለምዬ ጋ ካወራን ሁለት ቀን ስለሆነን መጀመሪያ እነሱ ጋ ደውዬ አወራዋቸውና ቀጥታ ወደሚቀመጥበት ቦታ ሄድኩኝ ። ገና እንዳየኝ እኔን ማናደድ ያስደስተዋል መሠለኝ " ስጠብቅሽ ነበር ቆንጅዬዋ ጠፋሽ እኮ ? " አለኝ መቀመጫ ወንበሩ ላይ በእጁ የያዘውን ካሜራ እየያስቀመጠ ። ከቻልክ አታውራ አዳምጠኝ አልኩት ግንፍል ግንፍል እያልኩኝ " እሺ አንቺ እንዳልሽ " አለኝ ። አንድ ሀሳብ ብልጭ አለልኝ ቀጥታ ምን አስጠየቀኝ አልኩና ነገሩንም እንዳይቀይረው ፈርቼ ቀጥተኛ መልስ ብቻ መልስልኝለማወቅ ነው ፍቅረኛ አለክ ??? አልኩት ። " ይሄን ጥያቄ ካንቺ መሥማት አስደሳች ነገር ነው !!!! " አለ ማይገናኝ ነገር !!?? ኤጭ ቀጥታ መልስ ብዬ ጮኩበት " ፍቅረኛ ሳይሆን ማፈቅራት ሴት አለች " አለኝ ካሜራውን በእጁ እያነሳ ። ማናት ከይቅርታ ጋር ማወቅ እችላለሁ ?? አልኩት ። በዝምታ  ቀርቀር ብሎ ፈለግ ፈለግ አደረገና ይቻት ብሎ ከርቀት ወደኔ አዞረው ። ለማየት ጠጋ ስል እጁን ከፍ አደረገው ። " በውበት የጊቢውን ሴቾች እንዳለ ትቦንሳለች ማንም አይደርስባትም ንግስት ናት !!" አለኝ ። የበለጠ የማየት ፍላጎት አደረብኝና ስጠኝ ልያት ብዬ ከእጁ ልቀማ ስሞክር ቆሞ እጁን ወደ ላይ አደረገብኝ በጣም ረጅም ነው እንዲሁም እንኳን ከፍ አድርጎብኝ !!!! ስጠኝ ስጠኝ እያየሁ ስንታገለ " አብላካት "" አለች ጄሪ ጮክ ብላ ። እኔ ያላስተዋልኩት ነገር እጁን ወገቤ ላይ አድርጎት ነበር ??? የሷ አይንም ያረፈው እጁ ላይ ነበር !!! ቶሎ ብዬ ወደ ዃላ ሸሸሁኝና ያምሀል ብዬ ጮኩበት ። ምንም ሳትሰማ ጥላኝ መንገዷን ስትጀምር ሮጬ ከፊቷ ቀደምኩኝና ላንቺ ብዬ እኮ ነው ጄሪ ተረጋጊ እንደምታስቢው አደለም ?? አልኳት " ምንድነው ያሰብኩት ??? እየተላፋችሁ እንደነበር ነው ??" አለችኝ በንዴት ተሞልታ ። እንደዛ አይደለም አረ ወይኔ ማፈቅራት ሴት አለች ብሎኝ እሷን ላጣራልሽ እየሞከርኩ ነው ብዬ ላረጋጋት ሞከርኩኝ ። ቀጥታ እሱን ቸመለከተችና ሄዳ ከእጁ ላይ ካሜራውን ወሰደችው እሷ ስትወስደው ዝም ነው ያለው?? ካሜራው ላይ አይኗን ተክላ በጣም ተመለከተችው......??? . . . ይቀጥላል #ክፍል_2⃣3⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣1⃣ ...... ስትንተባተብ ግራ ገብቶኝ ምንድነው አልኳት ጮክ ብዬ " እንዳትስቂብኝ ግን ከማላቀው ልጅ ፍቅር ያዘኝ " አለችኝ ። በሰአቱ ትልቅ ቁም ነገር ልታወራኝ ስለመሰለኝ ሳላስበው ጮክ ብዬ ሳኩኝ ። ውስጥ እያነበቡ የነበሩት ተማሪዎች ቀና ብለው ሲያዩኝ ሳቄን መቆጣጠር አልቻልኩኝም  እቃዬን ሰብስቤ እየሮጥኩ ወጣሁ ። ከድብርት ውሎ ቡሀላ ትንሽ ፈገግ አስደረገችኝ ። እሷ ግን አፍራ ነው መሠለኝ አኮረፈችኝ ። አጠገቤ ቆማ በተናደደ ፊት አየችኝና " ባልነግርሽ ይሻለኝ ነበር " ብላ ጥላኝ ልትሄድ ስትል ትንፋሼን ሰብስቤ መሳቅ አቆምኩና እሺ ልጁ ማነው እንዴት ነው የማታቂው ?? አልኳት ። ለመመለስ አልዘገየችም ኩርፊያውን ረሳችና ቶሎ ዞራ "  አላቅምም ብታይ እንዴት እንደሚያምር ሳየው ልቤን ንዝር አደረገኝ ይሄ ፍቅር ማለት አይደል ??" አለችኝ። ያፈቀረ ልቤ ይሄ አይጠፋውም ማንም ወንድ ምንም ቢል ምንም ቢያረግ ግድ አይሰጠኝም ቤኪ ግን ሲጠጋኝ ሲያወራኝ ሲያየኝ ....ብቻ በማንኛውም አጋጣሚ  ከተያየን ራሱ ልቤን ንዝረት ነው የሚሰማኝ ነበር  !!!! ወዲያው ሳሳቄቅ ከኔ እስከሚርቅ ድረስ ስሜቷን ተጋራዋት በዛን ሰአት ስለ ፍቅር ከኔ በላይ ላረዳት የሚችል አንድም ሰው የለም !!!! አዎ ልክ ነሽ እና ምን ተሻለ ትነግሪዋለሽ ? አልኳት ቀስ ብዬ "  አይይይ አይሆንም መጀመሪያ ትኩረቱን ማግኘት መቻል አለብኝ  ከዛ ነው የምነግረው " አለችኝ ፍንድቅድቅ እያለች ። የሆነ ጎኔ ደስ ይላል እድሜሽ ነው ቀጥይበት ሊላት ቢፈልግም ከራሱ ያልተማረ ሞኝ ነው ይላልና እንደኔ እንዳትጎዳ ፈርቼ ዝም አልኳት ። " ደሞ አሁን አላሳይሽም እሺ እወቂ " አለችኝ ። እህ ለምን ?? አልኳት ንግግሯ ግራ ገብቶኝ " በቃ አይን የበዛበት ነገር ጥሩ አደለም " አለች ። እርግጥ እኔም የማየት ፍላጎት ስላልነበረኝ እሺ ብዬ ዝም አልኩኝ ። ከዛ ቀን ቡሀላ ጄሪ ጠዋት ወታ ክላስ ትንሽ ቆይታ ማታ ነው የምትገባው ። ምን ስታደርግ እንደምትውል አላውቅም ። ?? ስራዋ ግን ልጁን መከታተል ነው ድንገት ሳልተኛ ከደረሰች ዛሬ እንዲ ለበሰ እንዲ አረገ እንዲ ጓደኛ አለው ...... አረ በስመአብ ምን ማትለኝ ነገር አለ !!!! ልክፍት መጥፎ ነው ጄሪ በማይሆን ፍቅር ተለከፈች ትምህርት ሙሉ በሙሉ ማለት በሚቻል ሁኔታ ተወችው ረስታዋለች ማለት ይቻላል ። እኔም ሴቶች ከሚጋደሉበት ወንድ ከኢዮኤል ድብብቆሼን ቀጥዬ ትምህርቴንም ሳልተው በኪን እያሰብኩ ቀጥያለሁ ። አንዳንዴ ጄሪን አያትና ፈጣሪን ማማረሬን አቆማለሁ !!!! ምክንያቱም  ምን አልባት እሱ ቢኖር ነገሮች እንደማስባቸውና አሁን እንዳሉት ባይቀጥሉስ ኖሮ እላለሁ ።!!!! በተመሣሣይ ትንሽ የሰለቸ ህይወት ቀጠለ ። ነገሮች እንዳለ ድግግሞሽ ናቸው ትነሻለሽ ትበያለሽ ክላስ ላይብረሪ ዶርም እንቅልፍ በቃ ቀን በቀን አንድ አይነት ነገር ነው የሚሆነው ። በዛ ላይ ጄሪ ጥላኝ መውጣት ከጀመረች ቆየች ። ከሌሎቹ ጋር እንብዛም አንግባባም ስለዛ ላይብረሪ ሄጄ መቀመጥን መርጣለሁ ። ደስ የሚለው ግን ያኛውን ልጄ ነፍቅሬን ሞክሼ ካየሁት ራሱ ስንት ጊዜዬ እሱን ቀን በቀን ባይ ቤኪ ትዝ እያለኝ እንደምጎዳ እርግጠኛ ነኝ !!!! የሆነ ቀን ላይ እንደለመድኩት ላይብረሪ ቁጭ ብዬ እያለ ጄሪ እየሮጠች መጣች ። ምነው አልኳት ግራ ገብቶኝ " ሰለቸኝ እሱን መከታተልና እንዲያየኝ መሞከር ኤጭ " አለች ። እንደተማረረች ፊቷ ያስታውቃል ። ምን አሰብሽ ታዲያ ? አልኳት " አብረሽኝ ሁኚ ድፍረቱን እንዳገኝ እ ከዛ ነግረዋለሁ አለቀ ምክንያቱም እያጣሁት እንደሆነ እየተሰማኝ ነው ከእጁ ካሜራ አይጠፋም ማንን እንደሆነ አላቅም ግን ፎቶ የሚያነሳት ሴት እንዳለች ገምቻለሁ " አለችኝ ። ንግግሯ ቢያስቀኝም ላለማናደድ እሺ ብዬ ከዛ ወጣን ። ቆይ አሁን የት እናገኘዋለን አልኳት ። ስልኳን አውጥታ ሰአት አየችና " አሁን ስምንት ሰአት አ ዛሬ ክላስ የለውም ዛፉ ስር ነው የሚቀመጠው ትንሽ መፅሀፍ ያነብና ካሜራው ላይ ፎቶ እያየ ፈገግ ይላል ከዛ ተነስቶ ወደ ዶርም ይሄዳል " አለችኝ ። ምን ያህል እንዳጠናችው አስቤ እየተገረምኩኝ እንሂድ እሺ አልኳት ። አብረን ሄድን ። እንዳለችውም ግማሽ ፀሀይ ግማሽ ጥላ መሀል ቁጭ ብሎ ካሜራውን እያገላበጠ ከጀርባ አየነው ። አየር ሰብስቢ ደሞ ምንም ቢልሽ እንዳትናደጂ ግን ስሙን እንኳን ሳናቀው እንዴት ልናወራው ነው ?? አልኳት " አቀዋለሁ " አለችና በረጅሙ ተንፍሳ " በረከት " ስትለው ዞር አለ ...........?????🙄🙄 . . . ይቀጥላል #ክፍል_2⃣2

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 2⃣0⃣ ...... ከፊቱ ቀድሜ ቆምኩኝ ። ምን አይነት እብደት እንደተጠናወተኝ ለኔም አልገባኝም ከደቂቃዎች በፊት ቤት ውስጥ በቪዲዮ ያነሳልኝ ልጅ እዚህ ምን ያደርጋል ብዬ አስቤ ነው ወይ ጉድ !!!!!.. " አቤት " አለኝ ልጁ ቅንድቡን ከፍ ዝቅ እያረገ። ይቅርታ አባት ተሳስቼ ነው አልኩት በእጄ የጎተትኩትን ጃኬቱን ለቅቄ ወደ ዃላ እየሸሸሁ ። " በስሜ ስጠሪኝ ነበር ካልተሳሳትኩ " አለኝ ። ድምፁ በጣም ወፍራም ነው ቅላፄው ምናምን ግን ቁጭ የኔን ቤኪ ድምፅ ነው የሚመስለው !!! የሚገርማችሁ እኮ ስማቸውን ጨምሮ ሁሉ ነገራቸው ሲመሳሰልብኝ ቤኪ እኔን ፍለጋ መቶ ግን ራሱን ለመቀየር ፊቱን አስተካክሎት ነው ብዬ ሳስብ ነበር 😂😂😂 አይ ፍቅር ......!!!! በሀሳቤ ትንሽ ፈገግ እያልኩ እሱ ባለመሆን ትንሽ አዘን እያልኩኝ ግራ በተጋባ ስሜት ተውጬ ይቅርታ ብዬ ወደ ዶርም ገባሁኝ ። ገብቼ ቁጭ ከማለቴ ጄሪ ደወለችልኝ ።  " አቡ ቶሎ ነይ ክላስ መምጣት አለብሽ " አለችኝ ። ጄሪ ደብሮኛል መውጣት አልፈልግም አልኳት እሷ ግን ቶሎ ነይ ፍጠኚ ብላ ስልኩን ዘጋችብኝ ። አስፈላጊ ነገር ሆኖ ነው ብዬ ልብስ እንኳን ሳልቀይር ጃኬት ደርቤ እንደ ጎበዝ ተማሪዎች መነፅር አድርጌ ደብተሬን በእጄ አቅፌ ወደ ክላስ ሄድኩኝ ። ውስጥ ያለ እረፍት ያስባል !!!! ልቤ በብዙ ጥያቄዎች ተሞልቷል !!!! አፌ ሊያወራው ቢፈልግም ለማን ብሎ ዝም ብሏል!!!!!! አይኔን ወደ መሬት ተክዬ ያዳምጠኝ ይመስል በውስጤ እያወራሁ ከሱ መልስ እየጠበኩ  ስሄድ ሳላስበው ከአንድ ሰው ጋ ሄጄ ተላተምኩ ። ክው ነው ያልኩት  ። ደንግጬ ወደ ዃላ ሸሸሁኝና ቀና ስል የቅድሙ ልጅ ነው ። የቤኪ ሞክሼ ማለቴ ነው ። እሱ ያወቀኝ አይመስለኝም እኔ በአንዴ ስላወኩት ይቅርታ ብዬ እየሮጥኩኝ ወደ ክፍል ገባሁኝ ። የሚያናድደው ነገር አስተማሪ ቀርቶ ተማሪም አልነበረም ። ትንሽጰተማሪዎች በየ ቦታው ጣል ጣል ብለው ግማሹ ያወራል ግማሹ ከስልካቸው ጋ ናቸው ። የኔዋ ጉድ ደግሞ ከኢዩኤል ጋር ተቀምጣ ስታየኝ " አቡ አቡ ነይ እዚጋ " ብላጮከች ። ተማሪዎቹ እንዳለ ቀና ብለው ሲያዩኝ ደንግጬ ፈጥኜ ሄጄ ተቀመጥኩኝ ። " እዚሁ ጠብቁኝ ይዤ ልምጣ " ብላ እያበደች ከክላስ ወጣች የማትረባ ። በሷ ቤት እኔን ከሰው ጋ ለማጀናጀን እየሞከረች ነው ልቤ መያዙን አላወቀች !!! " ሰላም አብላካት " አለኝ ኢዩኤል እጁን እየዘረጋ  ላሳፍረው እና ራሴን ሰው እንደሚንቁት አይነት ሴቶች ላስቆጥር አልፈለኩኝም !!! ስለዚህ እጁን እየጨበጥኩኝ ሰላም አልኩት ። " ፈሪ ነሽ ልበል ?" አለኝ ። ምክንያቱን ባላቅም ተናድጄ ነበር ተነስቼ ብሄድ ራሱ ደስታዬ ነው !!!! አይ አትበል ምክንያቱም አደለውም አልኩት እንደለመድኩት ግንባሬን እየቋጠርኩኝ ። ቤኪ አጠገቤ እያለ በጭራሽ ማልችለው ነገር ነበር !!!!!😣 እሱ ስኮሳተር ደስ ስለማይለው ሲጀመርም ገና አጠገቡ ስደርስ ውስጤ ደስታ በደስታ ስለሚሆን ማኩረፍና መኮሳተር አልችልም !!!!! " የቆንጆ  ሴቶች ባህሪ ነው ብዬ ነው " እያለ ፈገግ አለ ። የሚያናደው ቀልዱ አያስቅም ውስጤ ቅጥል እያለ ነው ። ለምን እንደሆነ አላቅም ያን የመሠለ ቆንጅዬ ልጅ በጣም አስጠላኝ ።!!!! እኔን  ለመጀንጀን እየሞከረ መስሎ ተሰማኝና በጣም ተናደድኩኝ ።!!!!!! ከዛ በላይ በሼም ከሱ ጋር መቀመጥ አልቻልኩም ይቅርታ መሄድ አለብኝ ! ብዬ ተነስቼ ወደ ዶርም ገባሁኝ ። ከዛ ቀን ቡሀላ ራሴ ላይ የማይሆን ችግር ጠመጠምኩኝ ። ወንዶች እንደዚህ ናቸው ከፍቅር በላይ እልህ ያጠቃቸዋል!!!! ኢዩኤል በጣም እልህ ውስጥ ከተትኩት ። የዛኔ ጥዬው መሄዴ ፊት አለመስጠቴን ለመኩራት እየሞከርኩ አድርጎ ተረድቶታል ። ከዛ ቀን  ቡሀላ ባገኘው አጋጣሚ ሁላ አለቅም አለኝ ። በሱ ምክንያት ላይብረሪ ስሄድም ተደብቄ መሄድም ጀመርኩኝ ። ክፍል በሱ ምክንያት ስንት ቦታ እንደቀያየርኩኝ እኔ ነኝ የማቀው ። ጄሪ በኔ ምክንያት  ከሱ ጋ ላጋጫት አልፈለኩም ። ከኔ ቀድማ የምታቀው እሱን ነው ወንድሟም እንደሆነ ነግራኛለች ስለዚህ ነገሮችን ከዛ በላይ ላጋግል ስላልፈለኩኝ ለሷ ሁሉንም ልነግራት ወስኜ ደውዬ ላይብረሪ እንድትመጣ ነገርኳት ። ብዙ አልቆየችም ቶሎ መጣች ። እንደደረሰች ሀሳቤን ሰብስቤ ጄሪ አውቃለሁ ለኔ ምርጥ ጓደኛ ሆነሽኛል ብዙ ነገር አስለምደሽኛል አውቃለሉኝ ነገር ግን የምነግርሽ ነገር አለ አልኳት እየተንሾካሾኩ። " አይ አሁን አልችልም መጀመሪያ እኔ የምነግርሽ ትልቅ ነገር አለ አሁን ካልሆነ መቼም ድፍረቱን ላገኝ አልችልም "" አለችኝ እጆቿን እርስ በርስ እየፈተገች ምንድነው እሺ ንገሪኝ እስኪ አልኳት አስፈላጊ ነገር መስሎ ስለተሰማኝ " አቡ እኔ ....... እ.....እ !!! እያለች ስትንተባተብ ......... . . . ይቀጥላል #ክፍል_2⃣1⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣9⃣ ........ ገብቼ ቁጭ ከማለቴ ከየት እንደመጣ አላቅም ኢዩኤል አጠገቤ ተቀምጧል ። ደንግጫለሁ !!!  ግን ፊቴ ላይ ላለማሳየት ስል እዚህ ምን ታደርጋለህ ?? አልኩት ኩስትር ብዬ ። "እህ ክፍሌ ነው እኮ " አለኝ ኮራ የሚል ፊት እያሳየኝ ..... ከዛ በላይ ከሱ ጋር ማውራት ፊት መስጠት መስሎ ስለተሰማኝ አፌን ዘግቼ ተቀመጥኩኝ ። የመጀመሪያ አመት የመጀመሪያ ክላስ ስለሆነ አስተማሪው ብዙ ነገር አልተማርንም ። እንደ ትውውቅና እንደ መግቢያ ትንሽ ነገር አስተምሮን ወጣ። ጄሪ ክላስ ስላልገባች ከሌላ ሰው ጋ ማውራት አልፈለኩኝም ተነስቼ ልወጣ ስል " ጊቢውን ላስጎበኝሽ  ፈልጌ ነበር እኮ " አለኝ ኢዩኤል በፈገግታ ተሞልቶ ፊቴ እየቆመ ። እኔ አጥሬ ይሆን ወንዶቹ ረዝመው አብዛኞቹን ቀና ብዬ ነው የማያቸው !!😂 ቀና ብዬ አይኑን አየውትና አይ አመስግናለሁ አይቼዋለሁ ብዬው ጥዬ ሄድኩኝ ። ጄሪ  ስለ ኢዩኤል ስትነግረኝ አካብዳለት መስሎኝ ነበር ግን እንዳለችው በጣም ቆንጅዬ ነው !! ምንም እንከን አይታይበትም !!!!! ችግሩ አይኔ ላይ የቤኪ ምስል ተቀርፆ ቀረብኝ እንጂ !!!!!!!😣 ከክላስ እንደወጣሁ ቀጥታ ወደ ዶርም ሄጄ ለጥ አልኩኝና የቤኪን ፎቶዎች ማየት ጀመርኩኝ ። አስር ጊዜ እየደጋገምኩኝ ዙም እያደረኩ አየውት !! የሳቀበት ፎቶ ላይ አብሬ እየሳኩኝ ዝም ሲል ዝም እያልኩኝ ሲኮሳተር እየተኮሳተርኩኝ ...... ሙሎ ፎቶውን አየውት ። በዛው እስከዛሬ አብረን የተነሳናቸውን ፎቶዎችና የተነቀሰውን ንቅሳት ፎቶ አየውት ። ያኔ ምን ያህል አምኜው እንደነበር አስቤ ብርድ ልብሴን ሽፋን አድርጌ ወደ ውስጤ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩኝ ። ያሳለፍናቸውን ነገሮችና የፍቅር ጊዜዎች አስታውሼ ከልቤ ናፈቀኝ ድምፁ ፈገግታው አስተያየቱ ..... ብቻ ሁሉም ነገሩ ናፈቀኝ !!!!!!!! አውርተን እንደማናቅ አውቃለሁ ከአርባ ጊዜ በላይ እንደደወልኩለትም አቃለሁ ግን የዛን ሰአት በስሜት ተነሳስቼ ተነስቼ ወደ ላይብረሪ ሄጄ በቪዲዮ ደወልኩለት ። አንዴ ..... ሁለቴ ......ሶስት ጊዜ ...ደወልኩለት አያነሳም !!! ምን ያህል ቢጠላኝ ነው ??? የአራት አመት ፍቅር በአንዴ ተረሳ !???? የምር ጥሎ መሄድ የዚህን ያህል ቀላል ነው ????.... በርካታ ጥያቄዎች እየደረደርኩኝ ሰው እንዳያየኝ አጎንብሼ እንባዬን ስጠርግ ስልኬ ጠራ !! ክው ነው ያልኩት ቤኪ ነበር !! እንዲያወራኝ ብዬ ያ ሁሉ ጊዜ የደወልኩ ልጅ ሲደውል ሀማንሳት ፈራሁኝ !!!! እጄ ማንሳት ራሱ እንቢ አለኝ !! እንደምንም ብዬ አነሳሁት ። ፊቱን ለማየት በጣም ጓጉቼ ነበር !!!! አነሳሁትና ቪዲዮውን አብርቼ እሱን ለማየት ሞከርኩኝ ። እሱ ግን አብርቶት የሚያማምሩ የቤት እቃዎች እንጂ እሱ አይታይም !?? ቃል እስኪያወጣ ስጠብቅ ነበር እኔም እሱን እየጠበኩ ነበር !!!! ብታምኑም ባታምኑም ሁለታችንም እየተጠባበቅን ቪዲዮው እንደበራ ከሰባት ደቂቃ በላይ ቆየን!!!!! ከዛ በላይ ዝም ብል ጥቅም አልባነት ነው ካላወራሁት እንደማያወራኝ ስለገባኝ ደህና ነክ በረከት ? አልኩት ብዬው ማላቀውን በስሙ እየጠራሁኝ ። እውነት ለመናገር ይመልስልኛል ብዬ አልጠበኩኝም ነበር ትንሽ ዝም አለና " እባክሽ ይቅርታ አድርጊልኝ ተረጂኝ " ብሎ ፊቱን እንኳን ሳለየው ስልኩን ዘጋው ። በጣም ነበር የተናደድኩት የበለጠ ስሜታዊ ሆኜ ማልቀስ ጀመርኩኝ !!! ሰው አይን ውስጥ ላለመግባት ቶሎ ወደ ዶርሜ ተመልሼ ለጥ አልኩኝ ። በነጋታው ጠዋት አራት  ሰአት ከእንቅልፌ ነቃሁኝ ። ስነሳ ዶርም ውስጥ ማንም አልነበረም !!! ራስ ምታቴን ለማስታገስ በቀዝቃዛው ሻውር ወሰድኩኝና ልብስ ቀያይሬ ወጣሁ ። የጠዋት ክላስ ስላመለጠኝ ዝም ብዬ ጊቢውን መዞር ጀመርኩኝ ። ሁሉንም ቦታ ዞሬ አይቼ ወደ ሴቶች ድርም ልመለስ መንገድ ስጀምር ከፊት ለፊቴ ጥቁር ሁዲ የለበሰ ኮፍያ ያደረገ ረዘም ያለና የሚያምር አቋም ያለው ሰው ኮፍያውን በደንብ ለብሶ ወደ መንገዱ ሲሄድ አየውት ። ለመጣራት አላንገራገርኩም ቤኪ በረከት  ብዬ ሮጬ ሄጄ ልብሱን እየጎተትኩ ከፊቱ ቀድሜ ቆምኩኝ ......... . . . ይቀጥላል #ክፍል_2⃣0⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣8⃣ ወደ ዃላ ስዞር ከዚ በፊት አይቼ የማላቀው ሰው ነው ። ወደ ድሮ ማንነቴ ስለተመለስኩኝ ግንባሬን ቋጥሬ እንደማይስፈልግ ነግሬው መንገዴን  ቀጠልኩኝ ። ዶርሜን  እንደምንም አፈላልጌ አገኘውት ። ከኔ በቀር ሶስት ልጆች ገብተው ቀድመው ቦታ ይዘዋል ። የስር አልጋ አንድ ትርፍ ነበረች እሷን ወስጄ እንደምፈልገው አድርጌ አስተካከልኳት ። ሰው ካልተግባባኝ በስተቀር እኔ ቀድሜ ሰው መቅረብ አልችልበትምና እስካሁን ቃል አልተነፈስኩኝም ሶስቱም ግን ከመቼ ከመቼ እንደተግባቡም አላቅም እያወሩ እየተሳሳቁ ነው ። ምንም እንኳ የደሀ ልጅ ብሆንም በንፅህና አልደራደርምና ሎከሬን አልጋዬን ሁሉንም ፅድት አደረኩት ። አልጋዬ ጋር የእመቤቴን ከነ ልጇ ምስለ ስእሌን ሰቅዬ ውዳሴ ማርያምና መንፈሳዊ መፅሀፌን አስተካክዬ አስቀመጥኩኝ ። ጠዋት ስነሳም ማታ ስተኛም እሷ ጋር እየፀለይኩ ነው የምተኛው ። ፍሬሽ መሆን በጣም ከባድ ነገር ነበር ። የተቋጠረ ፊቴን መፍታት ስለማልችል ከሰው ጋር መቀራረብ በጣም ከብዶኝ ነበር ። እናቴ ያዘጋጀችልኝን ቆሎና ኩኪስ ስበላ በፌስታል ላይ አድርጌ እንብላ ያዙ እያልኩ በፈጣጣው እንደምንም ከሁለቱ ጋር ተግባባሁኝ ። ከዛ በሳምንት ውስጥ ሁሉም ገቡና  ስድስት ሴቶች ሆንን ። የመጡት የሸገር ልጆች ለመግባባት ጊዜም አልፈጀባቸው ። በአንዴ ከሁላችንም ጋር ፒስ ፈጠሩ ። የዛኔ  የዶርሙ እብድ ከሆነችዎ ከጄሪ ( ኢየሩስ ) ጋር በጣም ተግባባን ። የሴት ጓደኛ ኖሮኝ አያውቅም ነበረ ሐመጀመሪያ ጓደኛ አገኘውኝ ። የሆነ ቀን ላይ ከጄሪ ጋር ወተን ጊቢ ውስጥ ዞር ዞር እያልን እያለ ባለፈው ላግዝሽ ያለኝን ልጄ ከፊት ለፊት አገኘውት ። ይበልጥ ያስገረመኝ ነገር ደግሞ ጄሪ ከየት ከየት እንዳወቀችው አላውቅም ስታየው ሄዳ ተጠመጠመችበት ። ከዛም እብድ እብድ እያለች " ጓደኛዬ ናት ተዋወቃት " አለችው ወደኔ እየጠቆመች ። "ኢዩኤል እባላለሁ " አለ እጁን እየዘረጋ አብላካት አልኩኝ ሰላምቴውን እየመለስኩ " አንቻ ቀውስ ከመቼው ነው ግን ከሁሉም ጋ ምትግባቢው " አላት ። ከዛ ሲያወሩ ማዳመጥ ስለደበረኝ ቀደም ብዬ ሄድኩኝ ። ብዙም ሳትቆይ ተከትላኝ መጣች ። " ኢዩ ማለት አብሮ አደግ ጓደኛዬ ነው ታላቅ ወንድሜ በይው ። የሰፈራችን ቆንጆ መለኪያ እኮ ነው ። ብዙዎች ፍቅረኛው ስለምሠስላየው ይጠሉኛል  " አለች ከትት ብላ እየሳቀች ። የሚገርመው እኔ ልጁንም ልብ ብዬ አላየሁትም እንኳን ቁንጅናውን ላስተውል ። እሷ ግን ማውራቷን ቀጠለች "  ደሞ እኮ በጣም ጎበዝ ተማሪ ነው ደግሞ ለሁሉም ሰው ደግ ነው የሰፈር ሰው ሁላ ሲወደው ብታይ በዛ ላይ ሞዴሊንግ ይማራል ......." ብቻ በጣም ብዙ ነገርችን ነገረችኝ እኔ ትኩረት አልሰጠውትም እንጂ ። ..... ከብዙ ዙረት ቡሀላ ወደ ዶርም ተመለስን ። ገና ትምህርት  ስላልተጀመረ ስልክ ላይ አንዳንድ ነገሮች እያየው እያለ " ደህና አመሸሽ " የሚሎ መልእክት ተላከልኝ ። ማንነቱን ለማወቅ የፕሮፋይል ፎቶዎቹን ሳይ ኢዩኤልን መሠለኝና ለጄሪ ይሄ ልጅ ታቂዋለሽ ብዬ ፎቶ አሳየዋት ። " አንቺ ቀልበ ቢስ ኢዩ እኮ ነው " አለችኝ ። ከዛ ስልኬን ከየት አመጣከው ልለው አልኩኝና ከጄሪ ስለማያልፍ ብዬ ዝም አልኩኝ ። በቀጣይ ሳምንት የመጀመሪያው ሰኞ የመጀመሪያ class ለመማር ተዘጋጅተን ወደ መማሪያ ክፍል ገብቼ ቁጭ ከማለቴ ........ . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣9⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣7⃣ .......... እንደማልፍ ነበር የምናቀው ። ፈጣሪ ይመስገን ተሳክቶልኝ ስንት መከራ አይታ ለፍታ ያሳደገችኝን ሳትማር ያስተማረችኝ እናቴን በትምህርት ቤት አስጠራዋት በተማሪዎችና መምህራን ፊት ከቁሜ የምስክር ወረቀቴንና ሽልማቴን እንድትቀበልልኝ አደረኳት። ከትምህርት ቤቱ አስር ሺ ብር ሽልማት ተሰጠኝ ። ያልጠበኩት ነገር ነበር ። ከፍተኛ ውጤት ላመጣነው አንደኛ ከፍተኛ አስር ሺ ብር ሁለተኛ ለወጣው ስምንት ሺ ሶስተኜ ለወጣው ልጅ አምስት ሺ ብር ተሸለምን !!! በጣም ደስ ይል ነበር !!! የዛኔ እናቴ በደስታ ስታነባ እኔም በደስታ እንባዬን ሳፈስ ነበር !!! ሰፈር ውስጥ ከብዙ ሰው ጋር ባንግባባም የሚያቁን ሁሉ እናቴ ጋር እየመጡ ለቁም ነገር ያብቃልሽ እያሉ አኮራሽን እያሉኝ ነበር የሚሄዱት !!!! ይሄ ደግሞ ለኔ ትልቅ ቁም ነገር ነው በጣም ደስ ብሎኛል ከህልሞቼ አንዱን አሳካሁ ማለት አይደል !!!! እናቴም ሁሉም ለበጎ  ነው እያለች እያፅናናችኝ ነበር ። እኔ ግን ትምህርት ስጨርስና ከትምህርት ስርቅ ቤኪን መናፈቅ ጀመርኩኝ እስከዛሬ ድረስ ቢያንስ ቦታዬ ላይ ስቀመጥ ከአጠገቤ እንዳለ እያሰብኩኝ ነበር የምፅናናው ። እናቴ ለኔ ብላ በሌላት ብር ኬክ አስጋግራ ስሜን አፅፋበት ቄጠማ ጎዝጉዛ  ቡና አቀራርባ ፏ አደረገችኝ ። በራችንን ዘግተን ቡና እያፈላች እያለ በር ተንኳኳ ። ማነው ብዬ ስከፍት አለም ነበረች ። ለምን እንደሆነ አላቅም ደነገጥኩኝ ። " በር እየዘጋሽብኝ ነው ??" አለችኝ ። ምንም ሆነ ምን ለእናቴ እንደ ጓደኛ እንደ እህት ሆናልኛለች!!!! ለኔ ብዙ ነገር አድርጋልኛለች ስልኩም ለኔ ጠቅሞኛል !!! " ማነው ልጄ " ብላ አለምዬም ወደኔ መጣች ። ሁለቱም ሲተያዩ ችክ ብለው ቀሩ " አረ ተይ መስኪ የደስታሽ ተካፋይ አታደርጊኝም ???" አለቻት ። እማዬም መለስ ብላ አስታወሰች መሠለኝ " ቤትሽ ነው አለምዬ ነይ ጊቢ እንጂ ከልጅሽ እንጂ ካንቺ ችግር የለብኝም !" አለቻት ። ቤኪ ላይ በጣም ተናዳበታለች !!!! ለነገሩ መብቷ ነው እንደዐማንኛውም እናት ልጇን የጓዳባትን ሰው የመጥላት መብት አላት !!!!! ከዛ በላይ ብዙ አልተወራም አለምዬ ገብታ ቁጭ አለች ። ከዛ በጣም እንደኮራችብኝ ነግራኝ የአንገት ሀብል ስጦታ ብላ ሰጠችኝ ። በጣም ደስ ብሎኝ ነበር ምክንያቱም ከዛ በፊት ሀብል አድርጌ አላቅም ነበረ ። በወሬ መሀል አምልጦኝ " በረከት ደህና ነው ? " አልኳት ። " አዎ ደህና ነው ማታ እያወራውት ነበር እና ከሄደ ቀን ጀምሮ እንዳላወራችሁ ነገረኝ ። "አለችኝ ። ሲከነክነኝ ስለነበር መሠለኝ ለምን አልሽው ?? አልኳት እንድትነገርኝ ብዬ " አዎ ጠይቄው ነበር ያለኝ ደግሞ ፈተና በደንብ ትኩረት እንድታደርግና እኔን እንድትረሳኝ ፈልጌ ነው አለኝ " አለችኝ ። የሆነ ነገር ደስ አለኝ የሆነ ነገር ደግሞ በጣም አናደደኝ ምክንያቱም ደግሞ እሱ ከጎኔ ቢሆን በጣም የተሻለ ውጤት እንደማመጣ እርግጠኛ ነኝ እሱን በማሰብ ያባከንኩትን ቀናት በማልቀስ ያሳለፍኳቸውን ምሽት ባነብባቸው ከዚ የበለጠ እንደማመጣ አውቀዋለሁ ከዛ በጣም ተናደድኩኝ ። ይቅርታ አለምዬ ልጅሽ እንደሆነ አውቃለሁ ነገር ግን የደደብ አስተሳስብ ነው ያለው እንደዚ ያስባል ብዬ አላስብም ነበር !!!! አልኳትና ተነስቼ ወጣሁኝ ። ሁለቱም ልክ መሆኔን ስለሚያውቁ ሊከተሉኝም ሆነ ሊመልሱኝ አልሞከሩም!!! እንደለመደው ከእናቴ ቀጥሎ በቤኪ ጉዳይ ሲሆን እንባዬ መቆጣጠር አልችልምና እንደወጣሁ ገና አመለጠኝ ። እንደምንም እንባዬን ተቋቁሜ ጠራርጌ አየር ስቤ ወደ ውስጥ ተመልሼ ገባሁኝና ቁጥብ ፈገግታ እያሳየዋቸው አለምዬ የኔ አክስቴ አመሠግናለሁ በጣም እሺ የኔ ባለውለታ  አልኳትኝ የመጀመሪያ ስጦታ ሰጪዬ ስለሆነች ተደስቻለሁ !!!! " የኔ ልጄ ልጄ አጣሽ እንጂ አላጣሽውም እንደ ልጄ ነው የማይሽ " ብላ ተነስታ ግንባሬን ሳመችኝ ። ከዛ ወደ እናቴ ዞረችና " መስኪዬ ልጅሽን ስለጎዳብሽ በልጄ ስም ይቅርታ አድርጊልኝ ግን ከኔ በላይ ሁላ ነው የሚወዳት አባቱ ባያስገድደው አልሄድም ብሎ ነበር። በልጅነቱ ሲመታ የማያለቅስ ልጅ ለአቡ ብሎ ሲያለቅስ ከአንዴም ሶስቴም አይቼዋለሁ እመኚኝ አሁንም በጣም ነው የሚወዳት እንዳትቀየሚው " አለቻት ። የሆነች ስሜት ልቤን ወጋ አደረገችኝና ፈገግ ለማለት ስሞክር እናቴ ቀደም ብላ " ህፃን ልጅ አይደለም እኮ አለምዬ መሄድ ባይፈልግ አይሄድም ነበረ ። በዛ ላይ ደግሞ እሷን እጠቅማለሁ ብሎ ሁለታችንንም ጎድቶናል !!! አቡ ተደብቃ ስታለቅስ ተደብቄ አይቻት ብዙ አልቅሻለሁ !!! ልጄ የማይሆን ሰአትና ሰው ላይ ወደቀችብኝ !!!! ድሮም እኮ ከሀብታም ፍቅር እንዳይዝሽ እላት ነበረ .......!!!" አለች እናቴ የእናቴ የሀብታም ጥላቻ ደግሞ ይለያል ገንዘብ ያለው ሰው የሚያፈቅር የሚያዝን የሚራራ ልብ ያለው ሰው ያለም አይመስላት ለዛም ነው አለምዬን በጣም የምትወዳት ማለቴ ከሌሎቹ ስለተለየችባት ነው !!!! ህይወት ቀጠለች ።............ የማይሆን የለም እኔም እየኖርኩ ነው !!!!! እናቴን እያገዝኳት ክረምቱን ብዙ መቆጠብ ችለናል !!!! በጣም ደስ በሚል ሁኔታ ደግሞ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ደረሰኝ የእናዬ ፀሎት !!!!!! ከእሷ ብዙ ርቄ እንዳልሄድ ስትፀልይ ነበረ!!!! የት እንደምሄድ ቆጥራው እንደሆነ አላቅም ጊቢ ልገባ ከሁለት ሳምንች አስቀድማ ዝግጅቷን ጀመረች ። የመአት የመአት ነገር ማዘጋጀት ጀመረች ። ቆሎ በሶ ዳቦ ቆሎ አንሶላ ብርድ ልብስ ጫማ ቱታ ቀሚስ ብቻ እንደማንኛውም ጊቢ እንደሚገባ ሰው እንደውም ከዛ በላይ አንድ ነገእ ሳይጎልብኝ ብዙ ነገር አዘጋጀችልኝ ። የፈራዋት ቀን ደረሰችና የምሄድበት ቀን ደረሰች። አለምዬና እናቴ ሸኙኝ ። የመጀመሪያ ቀን ስሄዲ ጊቢው ድረስ አድርሰውኝ ነው የተመለሱት ። እውነት ለመናገር ከሆነ በጣም ፈራሁኝ !!!!! ከእናቴ መራቅ አስጠላኝ ። ከሁሉም በላይ ደግሞ እናቴ ቤት ውስጥ ብቻዋን መሆኗ በጣም አሳሰበኝ ።!!!! ብዙ ነገሮችን እያሰብኩኝ ቀጥ ብዬ እየሄድኩ እያለ " ላግዝሽ " የሚል ድምፅ ሰምቼ ወደ ዃላ ስዞር ......... . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣8⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣6⃣ ........ ደወልኩለት ። ወዲያው online ገባ ። መልሼ ደወልኩለት ። በማይታመን ሁኔታ ከአስር ጊዜ በላይ ደጋግሜ ደወልኩለት ። የሚገርም ነው ስልኪ ሊያነሳልኝ ራሱ ዝግጁ አልሆነም !! ከዛ በቃ አይምሮዬ ብዙ ነገር ማሠብ ጀመረ ። ንቅሳቱ ንግግሩ ፍቅሩ ሁሉም የውሸትና የማስመሰል እንደሆነ ተሰማኝ !!!! ምክንያቱም ከዚ በፊት ስልክ አለማንሳት ይቅርና ....... ብቻ በጣም እንደሚጠላኝ ማሰብ ጀመርኩኝ ሁላ!!!! በዛ ላይ ህልሟ እንደሆንኩ እያወኩኝ እናቴን በጣም እያሳዘንኳትና ህልሟን እየነጠኳት መጣሁ ። ቀስ በቀስ ሁሉም ነገር እያስጠላኝ መጣ !!! ለትምህርት ያለኝ ፍቅር ቀነሰ !!! እናቴን በስራ ማገዝ ትቼ እሷን እንደገና በኔ ጭንቀት ውስጥ ከተትኳት ። አለም የጥፋተኝነት ስሜቷ አለቅ ብሏት ቀን በቀን ትደውላለች አላነሳም እንጂ!!!!! ትምህርት ቤት የመጀመሪያዋን አብላካት መመለስ ለኔ ቀላል ሆነ በጣም ኮስራና ቁጡ ማንነቴን መለስኩት ። እውነት ለመናገር እራሴን ከተማሪም ከአስተማሪም እንድደብቅ ነው ያደረግ!!! ሁሉም ቤኪስ ?? ቤካስ??? በረከትስ ....... ሁሉም ይጠይቃሉ ። የተማሪ ፎንቃ እያሉ ..... አራት አመት የጠበቁን ሰዎች ብቻዬን ሲያዩኝ ብዬ ነበር እያሉ ያፌዛሉ .......!!!!!! ይበለኝ የራሴ ጥፋት ነው !!!!!!" የኔ ሁኔታ በጣም ያስጨነቃት እናቴ በገባሁ በወጣሁ ቁጥር በስስት እያየችኝ ሀዘኗን በውስጧ ይዛ ታልፈናለች ። ኬጄ ባልማርም አንደኛ ክፍል ከገባው ጀምሮ አጋጥሞኝ የማያቀውን ለመጀመሪያ ጊዜበመጀመሪያ ሴሚስተር አራተኛ ወጣሁኝ ። ???!! ለነገሩ እሱም በአጋጣሚ የመጣ ነገር እንጂ ፈተና ላይ ራሱ ሳላነብ የሞላውት ነበር ። ስስበው እናቴ ከዛ በላይ ዝም ማለት አልቻለችም መሠለኝ ። የሆነ ቀን ጠበቀችና ቤት ስገባ በቁጣ ጠበቀችኝ ። ምነው እማዬ አልኳት ደንግጬ ። "እኔ ከዚህ በላይ አልታገስም ልጄን መልሽልኝ !!! ለፍቼብሻለሁ ብዙ ያየሁብሽ ልጄ ነሽ እወቂው !!! ከዛ በላይ ደግሞ ብዙ ነገር የምመኝብሽና የማልምብሽ ልጄ ነሽ !!!! ማንም ወንድ ድንገት መቶ ህይወትሽን አበላሽቶ ሲሄድ ዝም አልልም እሺ !!!! ቤቴን እንደበጠበጠው ቤቱን ነው የምበጠብጥለት ካስፈለገ ውለታ አስሮኝ ነው እስካሁንም ዝም ያልኩት !!!! " በጣም እያለቀሰች ነው ከልቧ የምታወራው የሷን እንባ እያየሁ እኔም እሪ አልኩኝ !!!! " ልጄ ማታቂያቸው ነገር ሊኖር  ይችላሉ !!! እኔ ላንቺ የለፋውት ለዚህ አደለም !!! ብዙ ያየሁብሽ ሴትነቴን የተውኩብሽ ልጄ ነሽ !!!! ስንት ፈግቼ ያስተማርኩሽ ለዚህ አይደለም እኮ ልጄ ። ሲጀመር ነግሬሽ ነበር የሀብታም ልጆችን አላምናቸውም !!! በረከት ጥሩ ልጅ ነበር አውቃለሁኝ ነገር ግን ውስጡን ሳላውቅ በፊት ነው!!!! ልጄን የነካ ማንኛውንም ሰው ለመጥላት ዝግጁ ነኝ !!!! ልጄ  እባክሽ ህልሜን አታጨልሚብኝ የኔ ህልም አንቺ በትምህርት  ስትጠሪ ስትሸለሚ መስማት ነው !!! ለዛ ደግሞ ምክነያት አለኝ እባክሽ አትጨክኚብኝ ከኔ እሱን አታስበልጪ እባክሽ ልጄን መልሽልኝ " ብላ ከዚ ቀደም አይቼ በማላቀው ልክ አለቀሰች !!!! ምሽቱን ሙሉ ስንላቀስ አምሽተን ሁለታችንም ራስ ምታት ውስጥ ገባን ። እኔ ከሷ መሻል ግዴታዬ ነበር እና ህመሜን ዋጥ አድርጌ ቡና አፈላላሁላት ምግብ አበላዋት ምናምን ። ደስ የሚለው ቀጣዩ ቀን ቅዳሜ ነው ጥግብ እስከምል እንቅልፌን ተኛሁ ። በዛው ራስምታቱ ለቀቀኝ ። ያቺ ቀን ለኔ የማንቂያ ደውል ሆነች !!!!!! ከዛ ቀን ቡሀላ ለእናቴ የበፊቷን አብላካት መለስኩላት !!!!! ልዋሽ አልችልም እሱን መርሳት አልችልም ነገር ግን ከእናቴ አይበልጥም እያልኩኝ ራሴን እያነቃቃሁ አጠናለሂ እናቴን አግዛለሁ ነገር ግን በቀን ቢያንስ ለአንድ ሰአት ስለሱ እያሰብኩ ፎቶውን እያየው ያሳላፍነውን እያሰብኩ እመሰጣለሁ!!!! የኔ ሱስ ሆኖልኛል !!!! ፈተና ትንሽ ቀናት ቀሩት ። በቻልኩት መጠን ትኩረት ሰጥቼ አነበብኩኝ  ቀስ በቀስ ራሴን ከሱ ማራቅ ጀመርኩኝ ። አንዳንዴ ነሸጥ ሲያደርገኝ ከመሬት ተነስቼ እየተሳደብኩ ያወራነውን ግማሽ እና ፎቶ አጠፋለሁኝ !!!! ፈተና ሁለት ሳምንት ሲቀረው ሙሉ በሙሉ ስልኬን ዘግቼ ለእማ ሰጠዋትና እኔ ትምህርቴ ላይ አቸኮርኩኝ ። የፈተናው ነገር በጣም ያጨናንቅ ነበር በርግጥ !! ግን የእናቴን ምክሮች እያስታወስኩኝ ፈተናዬን ተፈተንኩኝ ። ውጤት እስከሚለቀቅ ክረምቱን በጭኝቀት ነው ያለፍኩት ማለት የይቻላል !!!! እኔም ሆንኩ እናቴ በጣም በከፍተኛ ውጤት እንደማልፍ ነበር የምናቀው !!!! ??? ........ . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣7⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣5⃣ .......... አለች እናቴ ከተቀመጠችበት እየተነሳች ። በዛን ሰአት በጣም ስሜታዊ ሆኜ ነበር መሰለኝ እናቴ እንደማታውቅ ራሱ ረስቼው አዎ አይችልም እንደዛ ካደረገ ረግጦኝ እንደሄደ ነው የምቆጥረው !!!! አልኳቸው ከልቤ በሆነ አነጋገር ። በዛን ሰአት አለምዬ አይኗን ገለጥ አድርጋ ስታየኝ ክው ብዬ እናቴን ተመለከትኳት ። የሆነ አይነት አስተያየት አየችኝና " ማለት እኔ እማላቀው ነገር አለ እንዴ?? " አለችኝ ትኩር ብላ እየተመለከተች ። እናቴን መዋሸትም አልቻልኩም እውነቱን መናገርም አልቻልኩም ዝም እንዳልኩኝ ቀስ ብዬ ቁጭ አልኩኝ ። እናቴን ባህሪዬን ተንቅቃ ነው የምታቀው ዝም አልኩ ማለት ማውራት አልፈለኩም ማለት እንደሆነ ስለምታቅ ወደ አለምዬ ዞራ ምላሽጨመጠበቅ ጀመረች ። ምንም በማታቀው አለምንም እዳ ውስጥ ነው የከተትኳት !!!! ከብዙ የዝምታ መፋጠጥ ቡሀላ በተረጋጋ መንገድ " መስኪዬ ልጅሽና ልጄ ተዋደዋል እኛ ጣልቃ መግባት የምንችለው ነገር አይደለም እሺ !!! " ብላ በአጭሩ ነገረቻት ። እናቴ ክው ብላ ተመለከተችኝ ። እኔም እሷን ላለማየት መሬቱ ላይ አይኔን ተከልኩኝ ። " የምሯን ነው ልጄ " አለችኝ ። ከዛ በላይ ከእናቴ መሸሽ አልችልም !!! አዎ እናቴ ልነግርሽ ፈልጌ ነበር ግን ፈራሁኝ !!! አልኳት እንድትረዳኝ ለማሳመን እየሞከርኩኝ ። "ልጄ አንቺ ለዚ በቅተሽ ከኔ ደበቅሽኝ እ ጓደኛዬም እህቴም እናቴም ነሽ ትይኝ አልነበር እኔ ሳላቅ አክስትሽ ነገረችኝ " አለች አለምዬን እየተመለከተች ። ባለውለታዋ ስለሆነች እንጂ በእርግጠኝነት  የሩቅ ላለማድረግ ስለሆነች እንጂ ብዙ ነገር ታወራ ነበር !!!! " አንቺ አውቀሽ እንዴት ዝም አልሽ አለም " አለች እናቴ መለስ አድርጋ " ምክንያቱም በጣም ነው የሚዋደዱት እሱን ስላስተዋልኩ ነው በዛ ላይ ልጄን ደስተኛ የምታረግልኝ ብቸኛ ሴት ናት !!! ዘጠነኛ ክፍል የመንግስት ትምህርት ቤት እስከሚገባ ድረስ በቅጡ እንኳን አንገናኝም ነበር ከክፍሉም አይወጣም ነበር !! ከአስተማሪው ጋ አለመግባባት ተፈጥሮ አቋርጦ ዘጠኝን ሲደግም እነ አቡ ክፍል ደረሰው ከዛን ጊዜ ቡሀላ የምር መሣቅ መጫወት መደሰት ጀመረ በጣም እንደሚወዳት እኔ ምስክር ነኝ " አለች አለምዬ በኛ ፍቅር መደሰቷን ለማሳመን  ፍልቅልቅ እያለች ። እናቴ ነገሩን መቀበል ከብዷታል ። ፊቷን እንደገሰከሰች ... "  ቢወዳትማ ጥሏት ሊሄድ አይዘጋጅም ነበር በዛ ላይ ......" ብላ ወሬዋን በእንጥልጥል አቆመችው " አይረሳትም አይጠላትምም ሙሉ ስሟን እጁ ላይ ተነቅሶታል እኮ ቃል ገብቶላታል ደግሞስ ምን ለማለት ነው በዛ ላይ ምን ......" አለቻት " አንድ ላይ መሆን የማይችሉ ሰዎች ናቸው አለምዬ አዎ አውቃለሁ ልጅሽም ልጄም ውብ ናቸው ቁንጅናቸውን አልክድም ነገር ግን እሱ የአንቺ ልጅ ነው እኮ " አለቻት ። የዛኔ ተናዳ መሠለኝ " እኔ ምን አይነት ሰው ነኝ መስኪ እ የኔ ልጅ ስለሆነ ጥሩ ባህሪ የፈሊኖረው አይችልም !??" አለቻት " አረ አረ እንጀዛ አደለም አለምዬ ተሞላቆ ነው ያደገው የኛ ኑሮ ይከብደዋል ልልሽ ፈልጌ ነው እኮ " ብላ ኔግግራቸውን አስተካከለችው እናቴ !! ከዛ ደግሞ ትንሽ አስባ መለስ አደረገችና " ከወደዳት ለምን ጥሎ ይሄዳል ???"  አለች እማዬ የኔም ጥያቄ ነው ለአንድ ቀን ሳላይሽ ካደርኩ ....... እያለ እንዳላለኝ አሁን ከነ ጭራሹ ጥሎኝ ሊሄድ ። " ምን መሠለሽ  አቡ በፊት ላይ አባቲ ከአንቺ ጋር አይቶት በጣም ተጣልተው ነበር ። የበረከቴ አባት ትንሽ ቁጡና ስራ ላይ ብቻ እንዲያተኩር የሚፈልግ አባት ነው ። እና የሆነ ቀን በአጋጣሚ ክፍሉ ውስጥ ገብቶ የማይሆን ነገር አየና በጣም ተጣልተው ነበር አልሄድም ብሎ ነገር ግን አባቱ በጣም አከበደው አማራጭ አሳጣው " አለችኝ ። በሁለታችን መለያየት እሷም ያዘነች ትመስል ነበር ። እውነት ለመናገር ወዲያው የኔን መጎዳት ረሳሁትና ለኔ ብሎ መስዋዕትነት እየከፈለ ነው ብዬ ማሰብ ጀመርኩ ። ያው የሀብታም መስዋዕት ወደ ውጪ መላክ ሆነና ቤኪ ጥሎኝ ሊሄድ ነው ። የማትሪክ ፈተና ለመውሰድ ትንሽ ወራት ናቸው የቀሩኝ !! ትኩረቴን ለዛ መስጠት እያለብኝ ሀሳቤን መበታተን አልፈልግም ነበር ነገር ግን በቤኪ መጨከን አልችልም!!!! የበለጠ የሚከብደው ነገር ደግሞ ቤኪ ቻው ሳይለኝ እንኳን በቀጣዩ ሳምንት ወደ ሌላ ሀገር መሄዱን በስልክ ሰማሁኝ ። ለኔ በጣም ከባድ ነገር ነበር !!!!!! ምክንያቱም  እኔ ንዴት አልችልም ሀሳብ ጭንቀት አልችልም !!! እሱ ከሄደ ቀን ጀምሮ አላማዬን የሳትኩ እስከሚመስለኝ ድረስ ከእራሴ ጋር ተጣላሁኝ ። የሆነ ቀን ለሊት ዘጠኝ ሰአት ተነስቼ በቪዲዮ ኮል ደወልኩለት ........... . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣6⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣4⃣ ..............ምነው አለምዬ አልኳት ግራ ገብቶኝ ። ማታ እናቴን ሰላም ብዬ ተኝቼ አይኔን ስገልጥ  አለምዬን ሳያት ከልቤ ደንግጫለሁ  ግራ ገብቶኝ ፍጥጥ ብዬ አየዋት  ። በአንድ እጄ አይኔን እያሸሁ በአንድ እጄ እያማተብኩ ምነው ምን ተፈጠረ ?? አልኳቸው ። የእናቴ ስም መሠረት ቢሆንም አለምዬ መስኪ ነው የምትላት እናም ወደ እናቴ እየተመለከተች  " መስኪ መስኪ " ብላ እናቴን ጠራቻት ። እናቴም ቶሎ ወደኔ መታ " ተነሳሽ ልጄ " ብላ ግንባሬን ሳመችኝ ። ራሴን በራሴ እየዳበስኩኝ ደህና መሆኔን አረጋገጥኩኝ !! ሁኔታቸው የሚመስለው እኮ ለረጅም ጊዜ ኮማ ውስጥ ቆይቼ እየነቃሁ ያለሁ ነው ??? አለምዬ እማ ምን  ተፈጥሮ ነው ??? አልኳቸው ግራ እየገባኝ ። " ተጣጠቢና ነይ ምናወራው ነገር አለ!"  አለችኝ እማ ግራ ገብቶኝ አለምዬን ስመለከታት  ምንም ሳትል ጥለውኝ ወጡ ። ወሬውን ለመስማት ከመጓጓቴ ብዛት ከመቼው እንደታጠብኩም አላቅም ቶሎ ታጥቤ ወጥቼ ለማዳመጥ ዝግጁ ነኝ በሚመስል መልኩ  ቁጭ አልኩኝ ። " አንድ መጥፎ እና ጥሩ ዜናም አለ " አለች አለምዬ እያየችኝ ። እ .... አልኩኝና ከመጥፎ ጀምሪ ምን ተፈጥሮ ነው አልኩኝ በየተራ እየተመለከትኳቸው ። " ልጄ እኔ እስከዚ አድርሼሻለሁ በጭራሽ እንድትከፊብኝ አልፈልግም እኔ ላንቺ አላንስም !!" አለችኝ ። አይምሮዬ ብዙ ነገር ማሰብ ሲጀምርብኝ እናቴ አንቺኮ ለኔ ሁሉ ነገር ነሽ እንደ እናት እንደ አባት እንደ እህትና እንደ ወንድም አድርገሽ እንዳሳደግሽኝ ማንም ያውቃል እኮ ምንድነው መጥፎ ዜናው ??? አልኳት " ተይ አደብቂኝ ልጄ ለአባት ያለሽን ፍቅር አውቃለሁ እኮ ልጄ !!!! አባት ቢኖርሽ ደስ የሚልሽ ምን ያህል እንደሆነም አውቃለሁኝ እኮ ልጄ እኔም የሆነ ቀን .... እያልኩኝ " ብላ ንግግሯን ገታ አደረገችው ። እኔ አባቴን አልወደውም አባትነትን እንጂ አንቺ ደሞ እንደ አባትም ነሽ  ለኔ አልኳት እግሯ ስር በርከክ ብዬ እጇን እየሳምኩኝ ።አሁን ልትነግሪኝ የፈለግሽውን ንገሪኝ አልኳት " ልጄ አባትሽ እኮ ትላንት አረፈ " አለችኝ ። ቀለል አድርጌ የትኛው !?" አልኳት የወለደኝና ትንሽ ያሳደኝ ስለሚለያዩ " ወላጅ አባትሽ " አለችኝ ። በትንሹ ከፍቶኛል ቅር ብሎኛል ነገር ። በጣም የወንድ ጥላቻ አለብኝ አልክድም !!!! ነገር ግን ከልጅነቴ ጀምሮ አባቴ ሲሉ እቀናለሁኝ ። አባቴ እንዲ አደረገ አባቴ እንዲ አደረገ ሲሉኝ ባላገኘውት አባትነት እቀናለሁኝ !!!! ምናለ እኔም አባት ኖሮኝ እንዲህ ብል ብዬ እመኛለሁኝ !!!! አባቴን ባልወደውም አባትነትን እመኘው ነበር !!!! ነገር ግን እነሱ ፊት ነገሩን ቀለል አደረኩትን ፈጣሪ ነብሱን ይማር እማ እኔ አልከፋም አባት የለኝም እኔ !!!! እኔ አድጌ አንቺ ላይ ያደረገውን ሁሉንም ነገር ከምበቀለው ይልቅ ፈጣሪ ወሰደው ጥሩ ነገር ነው እኮ!!! አልኳቸዎ የወሸት ፈገግታ እየለገስኳቸው ። እንደዚህ ትላለች ብለው ያልጠበቁት ሁለቱ እናቶቼ በግርምት ይተያያሉ ። እንባዬ ሊያመልጠኝ ሲል ተናድጄ ቶሎ ብዬ ወደ ውስጥ ሳብኩት ። ምክንያቱም አንደኛ እነሱ ፊት ማልቀስ አልፈልግም በዋናነት ግን ለሱ እንባ አይገባውም  ብዬ ስለማምን ነው !!!!!! ዝምታውን ለመስበር ብዬ  እሺ ጥሩ ዜናው ምንድነው ? አልኳቸው ። አለምዬ ቀና ብላ አየችኝ ። የዛኔ ስለ ቤኪ እንደሆነ ገባኝ !! " ጥሩ ዜና እንኳን አይባልም " አለችኝ አለምዬ ቶሎ ብላ ። እናቴ አንድ ጥሩ አንድ መጥፎ ዜና ስላለች ጥሩ ዜና እየጠበኩ ስለነበር ግራ ገብቶኝ ማለት ምንድነው  አልኳቸው እናቴ ቀበል አድርጋ " እንዴ ተይ እንጂ በጣም ደስ የሚል ዜና ነው "አለች ። የዛኔ የምር ፈራሂ !!!!! ለእናቴ  ጥሩ ለአለምዬ መጥፎ ከሆነ... " አቡ ቤኪ እኮ ወደ ሌላ ሀገር ሊወስደው ነው አባቱ ለማስቆሙ ሞከርኩ ግን አልቻልኩም ልጄም ታሞብኛል " አለችኝ ። ክው ነው ያልኩት ምን ብዬ ከተቀመጥኩበት ተነሳሁኝ !!! " ተረጋጊ ልጄ ተመልሶ ይመጣል ይቆያል እንጂ " አለችኝ ። ምን ማለት ነው አለም መሄድ አይችልም !!!! አይሆንም !!!! አልኳት እየጮኩኝ እናቴ ግራ ተጋብታ ተመለከተችኝና " አስደሳች ዜና አይደል እንዴ ለምንድነው እንደዚ የምትይው " አልኳት ። ለናቴ ጥሩ ዜና ለኔ የሀዘኔ ምንጭ ነው !!!! አይሆንም አለምዬ እኔን ጥሎ መሄድ አይችልም !!!! አንለያይም ብሎ ነገባልኝ ቃልስ እ ???? ብዬ ስጮክ " ቆይ  ማለት ማለት ????" አለች እናቴ ከተቀመጠችበት እየተነሳች ........ . . . . ይቀጥላል #ክፍል_15

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 1⃣3⃣ ..........ከፊት ለፊታችን መቶ ቆመ ። ክው ነበር ያልኩት በጣም ደንግጬ ሁላ ቤኪን ወደ ዃላ እየገፋው እኔ ከፊቱ ሆንኩኝ ። ወይ ፍቅር ተይዞ የማያቅ ሲያዝ እዳ ነው !!!! ለወንድ ልጅ ብዬ ከፊት መቅደም ለኔ ትልቅ ነገር ነው!!!! አሁን ድረስ ሳስበው የሚገርመኝ ነገር ነው !!! ወደ ነጥቡ ስመለስ ግን በጣም የምታምር መኪና ናት ትልቅ ሰው ነበር ውስጥ የነበረው እንጂ ልሳደብ ጀምሬም ነበር ..... መኪናዋ ቀስ እያለች በአጠገባችን አለፈ ። ቤኪ ሰውዬውን ትኩር አድርጎ አየው ??? ከዛ ምነው ስለው በትንሹ ፈገግ እያለ " ምንም የኔ ቆንጆ በቃ ወደቤት ትሄጃለሻ አለምዬ እንዳትጨነቅ ልመለስ " አለኝ ። እያወራን መጣን አይደል ተመለስ በቃ አይዞክ ነገ ክላስ እንዳትቀር ብዬ ተንጠራርቼ ጉንጩን ሳምኩት ። " ጭምቅ አርጌ ብስምሽ  ውስጤ ነበር ግን ሰው ፊት አላደርገውም " አለኝ መንገደኛውን እየተመለከተ ። በፈጣሪ ስም ምን እንደነካኝ አላውቅም ሰዎቹ አይናቸው እኔ ላይ እንዳልሆነ አየሁና ተንጠራርቼ ራሴ ስሜው እየሮጥኩኝ ሄድኩኝ 🤭🤭 ትንሽ ሮጬ ዞር ብዬ ሳየው ቆሞ እየተመለከተኝ ነበር በእጄ እንደምወደው ነግሬው ወደ ቤቴ ሄድኩኝ ። ለንቦጬን ጥዬ የወጣሁ ልጅ ፍልቅልቅ እያልኩኝ ወደ ቤት ተመለስኩኝ ። "  በረከትዬ ተሻለው ?"  አለችኝ የኔ የዋህ እናት ጉዷን አልሰማች!!!! ከዛ ገብቼ ጥቅልል አልኩኝና ሶስት ሰአት አካባቢ ቤኪ ደወለልኝ ። ከዛ እንድናወራ ሲጠይቀኝ ላነብ እንደሆነ ነገርኩት ። በአንዴ ነው የተስማማው ወላ ሁላ በደንብ እንዳነብ ያበረታታኝ ጀመር !!! አምስት ሰአት አካባቢ  ድረስ አነበብኩኝና ስጨርስ online ስገባ እየጠበቀኝ ነበር ። ደክሞኝ ስለነበር ብዙ ላወራው አልቻልኩኝም ትንሽ እንዳወራን እንቅልፍ ወሰደኝ ። ጠዋት ቶሎ ነቅቼ ቤት አፀዳድቼ ቡና አቀራርቤላት ወደ ክላስ ገባሁኝ ። ዛሬ ክፍላችን ደምቃለች ብርሀኗ መቷል ጠፍቶ ነበር ! አልኩት እያቀፍኩት ። ንግግሬ አስቆት ፈገግ ብሎ አጠገቤ ተቀመጠ ። ሴቶቹ ሶስት ቀናት ትምህርት ቤት ባለመምጣቱ ተንገብገበዋል ። እየሮጡ እየመጡ ምን ሆንክብን ምነው ብቻ ብዙ ነገር .... እየቀባጠሩ ሊያቅፉት ይሞክራሉ ምናምን ። ምን እንደሆነች አላውቅም ትንሽ የሆነች ስሜት ተሰማችኝ። ማመን ባልፈልግም ( ቀንቼ ነበር)!!!! አስተያየቴን ያልወደደው ቤኪ እነሱን ትቶ እኔ ጋር መቶ እጄን ይዞ ተቀመጠ። ደስ የሚለው ልክ እሱ ሲጠጋኝ ሁሉንም ረሳዋለሁኝ !!!! ከዛን ቀን ቡሀላ ፍቅራችን በጣም በረታ ። በጣም ከመፋቀራችንና ከመቀራረባችን ብዛት የሆነ ቀን ድንገት የምንለያይ እየመሰለኝ እፈራለሁ !!!!!! በቃ ስንገናኝ እንዴት እንደምሳሳለት ለኔም ግራ ይገባኛል !!!" ለተወለደ ህፃን ልጅ ከምንጠነቀቀው በላይ እጠነቀቃለሁ ። አጥብቄ ከያስኩት ራሱ የሚያመው እስኪመስለኝ ድረስ እሳሳለታለሁኝ !!!! ክንፍ ባለ ፍቅር ግን ከትምህርቴና ከእናቴ ጋር ሳላጋጭ  ቀጠልን ። ህይወትን ጣፋጭ አደረገልኝ !!! ትምህርት ቤት ውስጥ አሁን ይጣላሉ .... የተማሪ ፎንቃ መጨረሻው ጭቃ ..... አሂን ለሚጣሉት ነገር ..... ብቻ ብዙ ነገር እየተባልን አንድ ጊዜም ሳንለያይና የከፋ ጥል ሳንጣላ አስራ ሁለተኛ ክፍል ድረስ ደረስን ። ከአለምዬ ጋር ግንኙነታችንን እያጠነከርን ነበር ። ከዛ ቡሀላ ለቤኪ ያለኝን ፍቅር ተማመንኩበት !! ሙሉ በሙሉ ተማመንኩበት ። ልንለያይ እንደማንችሎ ሳምን ወስኜ ለቤኪ ነግሬው እጄ ላይ በትንሿ ስሙን ተነቀስኩት ?!!!! ለምን እንዳደረኩት አላውቅም ስህተት ልስራ አልስራ እርግጠኛ አልነበረኩም ። ተነቅሼ አንድ ሁለት ሳምንት እንደሆነን ግን ያልጠበኩትን ነገር አየሁ ። የሆነ ቀን ተኝቼ ጠዋት ስነቃ አለምዬ ፊት ለፊቴ በሚያሳዝን እይታ እያየችኝ  ከእንቅልፌ ነቃሁ ። አይኔን እያሸው ተነስቼ ምነው አለምዬ አልኳት ግራ ገብቶኝ ............ . . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣4⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል1⃣2⃣ .......... የምታምር እጀ ሙሉ ሹራቡን አወለቀው ። ምን ያደርገኛል   ብዬ አስቤ እንደሆነ ባላቅም ወደ ዃላ ሸሸሁኝ ። ቤኪ በትንሹ ፈገግ አለና " ይሄን ያህል ነው የማታምኚኝ " አለኝ ። ደግሞ ድጋሜ ከምጣላ ብዬ ያን የሚያህል በስፖርት የጠነከረ እና የሰፋ ደረቱ ላይ ልጥፍ ብዬ አቀፍኩትና  ነኝ !!!! ደንግጬ ነው እኮ አልኩትና ወደ ቀልድ ለመቀየር  መታ እያደረኩት ልብሶችህ ናቸው ለካ ሰውነትህን የደበቁት እንዴ !! አልኩት እየተሽኮረመምኩኝ ። የሚገርማችሁ ያን ያህል ሰአት ሙሉ የሰውነቱን ማማር የደረቱን  ስፋት ስፖርተኛነቱን እንጂ በግራ ደረቱ በኩል ያለውን ንቅሳት አላስተዋልኩትም ነበር ። በትንሹ አብላካት ተብሎ ተፅፍ ከስር ደግሞ  28/01 ተብሎ ተፅፏል ። በጣም  ግራ ገባኝ ማለት ቀኑ  ምንድነው ስለኔ  ምን ያህል እርግጠኛ ቢሆን ሰሜን ይነቀሰዋል ??? ብዬ ግራ በመጋባት አየሁት  ። " ቀኑን አስታወሺው ?" አለኝ ። ቃላት ለማውጣት አቅም ስላጠረኝ  አንገቴን በመነቅነቅ እንዳላስታወስኩት ነገርኩት ። "ታስታውሻለሽ እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ የተያየነው ስማችንን ስንፈልግ በመጀመሪያ እይታ ነው በልቤ ያነገስኩሽ ። ከዛ ልቀርብሽ ስል ስትርቂኝ ይበልጥ ወደድኩሽ ። ይሄ ሳንኮሎጂ እውነታ ነው ወንድ ልጅ ትንሽ ጠበቅ የምትልበትን ሴት ይወዳል ይባላል እኔም ከሌሎቹ ለየት ብለሽ ስለታየሽኝ ወደኩልሽ ። ያ ቀን ደግሞ መስከረም 28 1 ወር እለቱ ሰኞ ቀን ነው ። ከዛ በቃ ፍቅር የጀመርን የመጀመሪያ ቀን ተማመንኩብሽ  እና ተነቀስኩት " አለኝ ። ጭራሽ የማልጠብቀው ነገር ስለነበር በጣም ደንግጫለሁኝ ። እኔ እሱን ሳልወደው ቀርቼ ሳይሆን ስለምፈራ ነው !!!! ለደቂቃዎች ከተፋጠጥን ቡሀላ እንደመባነን ብዬ ቶሎ ልብስክን ልበስ ብዬ ያወለቀውን ሹራብ እንዲለብስ አደረኩት ። " ወደድሽው ?? አለኝ " እ አዎ የሆነ የመፈቀር ስሜትም የፍራያ ስሜትም እየተሰማኝ ነው !!!አልኩት ። ከት ብሎ ሳቀብኝና " አትፍሪ እሺ እኔና አንቺ አንለያይም !!" ብሎ ሳመኝና ይዞኝ ወጣ ። ከዛም ወደ ታችኛው ቤት ወረድንና አለምዬ ቁጭ ብላ እየጠበቀችን ስለነበር ወደሷ ሄጄ በጣም በፍራቻ ደህና እደሩ አለምዬ አልኳት ። እስከዛሬ ወጀሷ ቀርቤ ጉንጯን ስሚያት ምናምን ስለምሰናበታት ቅር ያላት በሚመስል መልኩ እያየችኝ " ገና ሳትጋቡ አማት አደረግሽኝ " አለች እየሳቀች ። አረ እንደዛ አይደለም አልኩኝ አሁንም አንገቴን እንደደፋው ። ወደኔ መታ ግንባሬን ሳመችኝና " ደህና እደሪ ስለ መስኪ አታስቢ እኔ አወራታለሁኝ እሺ ደግሞ ሰላም በይልኝ " አለችኝ ። እሺ ብዬ ከቤት ስወጣ ቤኪ ተከተለኝ ። የት ነክ ? አልኩት ኮስተር ብዬ " ልሸኝሽ ነዋ " አለኝ ። አሞካል ብርድ ሲነካህ ጥሩ አይደለም አልፈልግም !! አልኩት ። " አዎ ህመሙ እንዳይነሳብህ " አለች ከአፌ ተቀብላ " አሁን እኮ ደህና ነኝ እማ መድሀኒቴን አገኘው " ሲላት ፊቴን ዞር አርጌ ከዛ ጊቢ ለቅቄ ወጣሁ ። ቤኪ ተከትሎኝ ሲመጣ ድጋሜ እንዲ አይነት ንግግር አለምዬ ፊት እንዳይጠቀም ነገርኩት ። ከዛ መጓዛችንን ቀጠልንና በመሀል " ለምንድነበር የራቅሽኝ ግን ? " አለኝ ከእማ ጋር ያለኝንና ከትምህርቴ ጋር ያለኝን ግንኙነት እረስቼው ነበር እናቴ አሟት ራሱ ትኩረት ነሳዋት በዛም እንደተቀየመችኝ ነገረችኝና ወደራሴ ለመመለስ እየሞከርኩ ነበር !!! አልኩት። ትንሽ ዝም አለና " ከዚ ቡሀላ ሰአታችንን በእቅድ ነው እሺ የምንመራው የኔ ፍቅር !!  ሶስታችንንም  እኩል ማስኬድ ትችያለሽ " ብሎ የጀስ ደስ እየነገረኝ የተጨነቀ ፊቴን እያበራልኝ እያለ ነበር አንድ መኪና ከፊት ለፊት መቶ ......... . . . ይቀጥላል #ክፍል_13

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል1⃣1⃣ ............ ላሳይሽ ብሎ ወደ መታጠቢያ ክፍል ወሰደኝ ። እዚህ ለምንድነው ያመጣኝ ብዬ ግራ በመጋባት ፊት ተመለከትኩት ። ቀጥታ ግድግዳው ላይ የተለጠፈው ትልቁ መስታወት ጋር ወሰደኝና ከጀርባዬ አቅፎ ይዞኝ ቆመ ። ምንድነው አልኩት መስታወት ውስጥ አይኑን  መመልከት ስለምፈራ ወደታች አጎንብሼ " አንዴ ቀና ብለሽ እይኝ እስኪ " አለኝ  መስታወት ውስት መተያየት ጀመርን ። " እ በምን እንዳወቀችብኝ ገባሽ ?" አለኝ ። እንዴ ምንም አልነገርከኝም በምን አቃለሁ ? አልኩት ። "አይኖቼን ተመልክታ ነው  ! የአይን ብሌኔ ውስጥ ራሱ አንቺ አለሽ እኮ አይኔ ላይ ፍቅር እንዳለ ያስታውቃል እኮ " አለኝ ። አነጋገሩ ትንሽ አሳፈረኝና እፍረቴን ለመሸፈን እሺ የኔ ተፈላሳፊ ይበቃሀል ብዬ ፈገግ አልኩኝ ። ከዛም ወደራሱ አዞረኝና " የሆነ ሚስጢር ልንገርሽ የኔ አለም " አለኝ እሺ ምንድነው አልኩት ትንሽ እየሸሸሁት " ልነቀስሽ አስቢያለሁ ባንቺ ላይ ሙሉ እምነት አለኝ " አለኝ ። ክው ነው ያልኩት እንዴ ለምን አልኩት በቁጣ እሱ ነገሩን በሌላ መንገድ ተረድቶት " እውነቱን ንገሪኝ አትወጂኝም ???" አለኝ !!! የበለጠ ደንግጬ እንደዛ አይደለም ቤኪ ድንገት ባይሆን አንተ ትጎዳብኛለክ አልኩት እናቴን ፈርቼ ። እሷ በአስተሳሰቧ ሀብታምና ደሀ መፋቀር እንደማይችል ነው የምታምነው ። ነገሩን ለሷ ማስረዳት እንደሚከብደኝ ስለማውቅ ነው የፈራሁት ። " ለምን አይሆንም እ አንቺ ከወደድሽኝ ለምን መስኪም ብትሆን እዚ ስትመጣ ምን ያክል እንደምትንከባከበኝ አቃለሁ ። አለምዬ ስትቆጣኝ ራሱ በኔ በኩል ነው የምትቆመው ልዑል ነክ ትለኛለች እኮ !!!! ሲጀመር ለምንድነው ሰሞኑን ከኔ የራቅሽው ???" አለኝ ። ሊያጣላን እና ሊያናደው እንደሚችል ባውቅም ደፈር ብዬ ምክንያቱም የተለያየ ህይወት ነው ያለን እኮ ቤኪ እኔ ሳላውቅ ነው በፍቅር የወደኩት ያለ እቅዴ ተመርቄ ስራ ሳልይዞ እንደዚ አይነት ነገር ውስጥ አልገባም ብዬ ነበር ግን አሸነፍከኝ ። እንደማፈቅርህ ልክድ አልችልም !!! ለወደፊቴ ነው የምመኝክ ማንኛውም ሰው ሊወድቅልህ እንደሚችል ታውቃለህ የወንድ ጥላቻዬን ያሸነፍኩብህ ነህ !!! ለኔ ፍቅረኛ ብቻ ሳይሆን አባት ወንድም እንድትሆንልኝ እመኛለሁ !!!! ግን ደግሞ በሁለታችን መሀል ያለው የኑሮ ደረጃ ጣልቃ ይገባብናል ብዬ እፈራለሁ !!!! ራሴን ከአንተ ማራቅ አልፈልግም ግን የኔና የአንተ ኑሮ ልዩነት ሲገባህ ...... ብዬ እፈራለሁ !!!!! አልኩት በጣም እየፈራሁ ። ደስ የሚለው እሱ እኔ ላይ ከመጮክና ከመቀየሙ ይልቅ በእርጋታ ማውራትን የመረጠ ይመስል ወደኔ ቀርቦ ጉንጮቼን በእጁ አቅፎ " አቡ የኔ ልዕልት ለአሁን እሺ ድጋሜ እንዲህ ካልሽ በጣምምምሞ ነው የምናደደው ( ረዘምምም አድርጎ በንዴት አነጋገር) ግን ደግሞ እኔ በጣምምም ነው የምወድሽሽሽሽ !!!! የወደድኩት ሌላ ነገርሽን አይደለም አንቺነትሽን ነው ። ስርአትሽን ርጋታሽን ውብ አይኖችሽንን ....... እኔ አሁን ስላለሽ አላስብም የመቀየር እቅድሽን አደንቅልሻለሁ !!! እኔ ደሞ ትምህር ቤት ራሱ ብዙ እንድንታይ የማልፈልገው እኮ አፍሬብሽ አይደለም ብዙ እይታ የበዛበት ነገር ጥሩ አደለም ብዬ ነው እሺ!!!! አንቺ የወደፊቴ ነሽ የዛሬ ምናምን አመት ቁጭ ብለን ይቺን ቀን እናስባታለን እሺ !!!" አለኝ ጭምቅቅ አድርጎ እየሳመኝ ። እሺ ግን የማንለያይ ይመስልሀል ?? አልኩት በትንሹ ቀለል ብሎኝ " አለምዬ ትሙት አንለያይም ብቻ አንቺ በኔ ላይ ተስፋ እንዳትቆርጪ ምንም ነገር ባጠፋ መተሽ እኔን ደብድቢኝ እንጂ እንዳትጣይኝ " አለኝ ። የዛኔ በትንሹ ፈገግ አልኩኝና  አየውት ። አንገቴ ስር ውሽቅ ብሎ አቀፈኝ ። ከደቂቃዎች በፊት ስንት  መለያየቶችንና መጨቃጨቆችን ያስተናገድኩ ልጅ እሱ ሲጠጋኝ ሁሉንም ረሳውና ራሴን በጣም  የምታምር ገነት የሞትመስል ቦታ ላይ ራሴን አገኘዋለሁኝ ???? እሱን ማቀፍ ማለት ለኔ ያለማካበድ  ህፃን እያለን እንደምንመኘው  በነጭ ክንፍ መብረር እንደማለት ነው !!!!!! ተቃቅፈን ትንሽ ከቆየን በዃላ እሺ ንቅሳቱ ግን ይቅር !!!ብዬ በአሳዛኝ ፊት አየውት ። " አልችልም እናቴ " ብሎ እዛው አጠገቡ ቆሜ ከላይ የለበሳትን የምታምር እጀ ሙሉ ሹራብ አወለቀው ???? . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣2⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል1⃣0⃣   ........ የምሆነው ጠፋኝ ። ድንጋጤዬን አየና ቤኪ በተረጋጋ መንፈስ ሆኖ አቀፈኝና " ተረጋጊ አናስነቃም ቀስ ብለሽ በሩን ክፈቺ ከዛ ምግብ እያበላሽኝ እንደሆነ ተናገሪ አለቀ " ብሎ ነገሩን አቀለልኝና ተመልሶ አልጋው ውስጥ ገብቶ ጥቅልል አለ ። እጄ እኔን ለማዋረድ ይመስል ይንቀጠቀጣል ቀስ ብዬ በሩን ከፈትኩት ። ፈጣሪ ሲያወጣኝ የመጣችው አለምዬ አደለችም እህቱና ወንድሞቹ ናቸው ። ወንድሜ ቤቢ እያሉ እየተሽቀዳደሙ ሄደው አቀፉት ። ወዲያው አለም መጣችና " እ እንዴት ሆነልሽ " አለችኝ ሊበላ ነው እነሱ እንደወጡ ሙሉ ምግቡን ይበላል ከዛ ወደቤት እሄዳለሁ አልኳት ። ከዛ ልጆቹን ቶሎ አስወጣቻቸውና እዛው መታጠቢያ ክፍል ስላለው ገብቼ እጄን ታጠብኩኝና እያጎረስኩት ምግቡን እንዲበላ አደረኩት ። አለምዬ ቁጭ ብላ እያየችን ነበር ። "እሰይ ልጄ ገላገልሽኝ እኮ አልበላም ብሎኝ ጨንቆኝ ነበር " አለችኝ ። አረ አለምዬ ግዴታዬ አይደል ችግር የለውም አንቺ ስንት ነገር አርገሽልኝ አልኳት መልሼ ። ከዛ ቤኪን አየችውና ሁለቱም ፈገግ አሉ ከዛ ደነግጬ  ቤኪን ተመለከትኩት ። " ለልጄ የምመኝለትን ሴት ትመስያለሽ " አለች አለምዬ ከመሬት ተነስታ በተናገረችው ንግግር ደንግጬ የራሴ ምራቅ አንቆ እስኪደፋኝ ድረስ ትን አለኝ ። ቤኪ ቶሎ ውሀ ሰጠኝ ለሱ ከተቀመጠው ላይ ። ከዛ ጠጥቼ ተረጋጋሁ ።  " ምነው ልጄ አለችኝ " አረ ምንም ትንታ ነው ብዬ ማጉረሴን ቀጠልኩኝ ። " ልጄ እንደ አንቺ አይነት ሰው ይወዳል " አለችኝ ። ጠርጥራ ይሆን እንዴ ብዬ እየፈራሁኝ  እንዴት አልኳት " በጣም ቆንጅዬ ነሽ እኮ የመስኪ ልዕልት ነሽ ( መስኪ የእናቴ ስም ነው ) በጣም ደርባባ ነሽ ስርአት አለሽ የምታወሪበትን ቦታ ጠንቅቀሽ ታውቂያለሽ ጎበዝ ተማሪ ነሽ እናትሽን ታግዣለሽ በዛ ላይ ልጄ አጠር ብላ ጠየም ያለች ሴት ነው ምወደው ይለን ነበር !! ተቃራኒ ህይወት ቢኖረንም ብሎ ይመኝ ነበር ከደሀው ህብረተሰብ የወጣች ንፅህናዋን የምጠብቅ ሴት አገባለሁ ይል ነበር " አለችኝ ፊቷ በፈገግታ ተሞልቶ ። ሙሉ በሙሉ ስለኔ የምታወራ መስሎኝ እየፈራሁ ነበር ። ጥሩ ነው ደስ ይላል ብዬ የመጨረሻ ጉርሻውን ጠቅልዬ አፉ ጋር ሳደርሰው " አይለያችሁ ብያለሁ እኔ መጨረሻችሁን ያሳምረው ብቻ ልጄን እንዳጎጂብኝ " አለችኝ ። በእጄ የያስኩትን ምግብ ለቀኩትና ከመቀመጫዬ ተነስቼ ፎጥጥ ብዬ ቆምኩኝ ። አለም ደንግጣ ምግቡን ከልጇ ደረት ላይ አንስታ ሰሀኑ ላይ አስቀምጣ በሶፍት እየጠራረገች " ምነው ልጄ " አለችኝ ። እንደዛ ስትል ባሰብኝና አፌን ይዤ ከመሬቱ ጋር መፋጠጥ ጀመርኩኝ ። ከዛ ቤት ለመውጣት ተጣድፌ ቶሎ ታጥቤ ተመለስኩኝና ይቅርታ አለም ደህና አምሹ ብዬ ቀና ብዬ ሳላያት እንኳን ልወጣ ስል " ቆይ እንጂ የት ልትሄጂ ነው ደግሞ ተረጋጊ የሚያስደነግጥ ነገር የለም ቆየሁ ካወኩኝ   ፍቅራችሁ ፊታችሁ ላይ ያበራል ! እኔ ለምን በዚ እድሜ ብዬ ልከሳችሁ አልችልም ለእናንተ አሪፍ ነው እድሚያችሁ እስኪደርስ ትጠናናላችሁ በደንብ መተዋወቂያ ይሆናችዃል በዛ ላይ አንድ ላይ ታምራላችሁ በሁለት አመት ብቻ ነው የሚበልጥሽ ደስ ይላል እኔ በፍቃዴ ልጄን ሰጥቼሻለሁ " አለችኝ ። ይሄን ሁሉ ስትናገር ለሰከንድ ራሱ ቀና ብዬ አላየዋትም በጣም ፈርቼ ነበር !!!!! ከዛ ቤኪም ተነስቶ ወደኔ መጣና  " እኔ ለእናቴ ተናግሪያለሁ ከሷ መደበቅ አልችልም የዘመኑ አራዳ በያት ሳልነግራት ነው ያወቀችብኝ እና የወደፊት ህልሜ እንደሆንሽ ነግሪያታለሁ ..." አለኝ ። ከኔ ምላሽ የሚጠብቁ ይመስል ሁለቱም ተክ ብለው ይመለከቱኛል ። ከዛ ሁለቱንም አየዋቸውና ምን እንደምል ግራ ቢገባኝ አመሰግናለሁ  !!! አልኳቸው ። ሁለቱም ከት ብለው ሳቁና አለምዬ እንደ እናት  አቅፋ ስማኝ ጥላን ወጣች ። ለምን ነገርካት ብዬ ጮኩበት እግሯ ወጣ እንዳለ " እራሷ ናት ያወቀችው ምን ላድርግ " አለኝ ። እንዴት ልታውቅ ቻለች እንዴት አልኩት ድንጋጤው አለቀቀኝም " አንደኛ ስልኬን አይታ , ሁለተኛ አንቺ ስመጪ ፊቴ ላይ የሚጨምረውን ፈገግታ አይታ በዋናነት ግን ....." ብሎ ንግግሩን ቋጨው ። በዋናነት ምን ምንድነው ንገረኝ ....???? ስልክህ ምን ወይኔ ጉዴ እንዴት ነው ፊቷን የማየው አልኩት እየተንተባተብኩ " በዋናነት የአንቺ እናት ውሳኔ ብቻ ነው ሌላ ነገር እኛን አይለየንም " አለኝ ። እናቴ ስሰማ ምትለኝን ሳስበው ጭንቀቴ ባሰብኝ እና ቤኪ ልወድቅልህ ነው አልኩት ። ሴት ልጅ ስትፈራ የምታፈቅረው ሰው ብቻ ነው ሊያረጋጋት የሚችለው ብሎ ከንፈሬን በስሱ ነካ አደረገኝ ። ሌሎች ሰዎች ላይ ባየው ብዙ ነገር ልል የምችለው ልጅ በሱ ሲሆን ድርቅ ብዬ እቀራለሁ ክብሬን ረሳዋለሁ ።????? እሺ አለምዬ እንዴት አወቀች የስልኬ መክፈቻም ምንም ሁሉም ነገሬ ሆነሻል በዋናነት ግን ነይ ላሳይሽ ብሎ ወደ መታጠቢያ ክፍል ወሰደኝ  ........... . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣1⃣

    ❤️ሀይስኩል ❤️ ❤️ልብ አንጠልጣይ  ታሪክ ❤️ ✍ፊደል                         ክፍል 9⃣ .........ወደነሱ ቤት ሄድኩኝ ። መንገዱ ቅርብ ነው የምለው ቤት በሩጫ ራሱ ራቀኝ ። ስደርስ በሩን በሀይል ነበር ያንኳኳውት አለምዬ በሩን እንደከፈተችው የት ነው ምን ሆኖ ነው ...? ብዬ ክንፍ እያልኩ ጠየኳት ። " ምነው ልጄ አስደነገጥሽኝ ደህና ነው እኮ እንደው ከአንቺ ጋር ስለምትቀራረቡ ምግብ እንዲበላ ብልሀት አታጪም ብዬ ነው " አለችኝ ። ትዝ ሲለኝ ለካ ከበረከት ጋ ቅርበት እንዳለን አልፎ አልፎ እዚህ ስመጣ እንደተግባባን እና አንድ ትምህርት ቤት እንደሆንን እንጂ ሌላ የምታቀው አንድም ነገር አልነበረም !!! ወዲያው ወደራሴ እየተመለስኩኝ ። አይ ትምህርት ቤት በጣም አሞኛል ብሎኝ ከዛ ሶስቱንም ቀን ሲቀር በጣም አሞት ኘው ብዬ ፈርቼ ነው ብዬ ነገሩን አደባበስኩት ...!! ወደ ውስጥ ይዛኝ ገባች ። የዛሬው ለየት የሚለው ፎቁ ላይ ነው ይዛኝ የወጣችው ። የሌላ ሀብታም ሰው ሌላ ቤት የወሰዱኝ ነው የሚመስለው እንጂ ከስር ያንን የመሠለ ቤት እያለ ሌላ ቤት በጣም ቅንጦት ነው ። የሆነ ልቤ በነሱ እየተናደደ የሆነ ልቤ ደግሞ  የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች ..... እያለ እየሳቀብኝ ከተደረደሩት ክፍሎች ውስጥ ገንጠል ያለውን ክፍል ከፍታ ገባች ። ይበልጥ የሚገርመው ደግሞ የሱ መኝታ ቤት ብቻ ከኛ ቤቶ ሁለት እጥፍ መሆኑ ነው !! በኳስ ተጫዋቾችና በሚያማምሩ ሚስጥራዊ ስእሎች እንዲሁም ቀለም በሚቀያይሩ የሚበሩ ጌጦች የተሞላ ክፍል ነው ። ለትንሽ ደቂቃዎች ያለ ቦታዬ ኘው የተገኘውት ሲጀመር እሱ አይወደኝም ቢወደኝም አንድ ቀን ቤታችንን ሲያይ ፍቅሩ ይወጣለታል እያልኩ ብቻዬን እያወራሁኝ ክፍሉን ስቃኝ ነበር ። ቤኪ ፊቱን ተሸፋፍኖ ተኝቷል ። " በረከቴ ተነስ እስኪ ትንሽ ምግብ ብላልኝ እባክህ " አለችው ። " እናቴ መብላት ስፈልግ በላለሁ አሁን ብቻዬን ተውኝ " አላት ድክም ልዝዝ ባለ ድምፅ ። " እሺ ስትፈልገኝ ደውልልኝ " ብላ የመኝታ ቤቱን በር ዘግታ ወጣች ። ለነገሩ እውነቷን ነው ካልተደዋወሉ ይሄን የሚያክል ቤት ውስጥ በምን ይሰማማሉ ሆ !!! ልክ በሩን ዘግታልኝ ስትወጣ ወደሱ ቀረብ ብዬ ቤኪ አልኩት ። በፈጣሪ ስም የለበሰውን ነጭ የሚያምር ብርድ ልብስ ውርውር አርጎት ሲነሳ ደንግጬ ወደዃላ ሸሸሁኝ ። የሚያየውን አላመነም መሰለኝ በድንጋጤ ተመልሶ ተኝቶ ድጋሜ ተነስቶ አየኝና " አቡ " ብሎ እንደማቀፍ ከአልጋው ወርዶ ሲሄድ ደንግጬ ቆሜ እያየውት ነበር ። ከጠበኩት በተቃራኒ ግን በሩን ከውስጥ ቆለፈና ሩጫ በሚመስል እርምጃ መቶ ጥምጥም አለብኝ ። " እንዳታስነሺኝ እባክሽሽሽሽ !!!" ብሎ በረጅሙ ተማፀነኝና አንገቴን ተደግፎ አቅፎኝ ለረጅም ደቂቃ ቆመ ። ቤኪ ደከመኝ እኮ አልኩት አለቅ ሲለኝ ። " ይቅርታ ይቅርታ እናቴ ነይ ቁጭ በይ ( የአልጋው ጠርዝ ላይ እያስቀመጠኝ ) ምን አጥፍቼ ነው እ ለምንድነው ድንገት የራቅሽኝ እኔኮ ትምህርት ቤት ያልመጣሁት እሄዳለሁ ስል በር እየዘጉብኝ ነው አንቺ ግን እንዴት አስቻለሽ ?? " ብሎ እግሬ ስር ተንበረከከ ። በጣም ረጅም ከመሆኑ የተነሳ እሱ ተንበርክኮ እኔ ተቀምጬ እኩል ነን !! ምን እንደነካኝ አላቅም ቶሎ ሆድ ባሰኝና  እንባዬ መውረድ ጀመረ ። ቶሎ ቶሎ እንባዬን እየጠራረገልኝ " ለምን ታለቅሻለሽ ጠላሽኝ እንዴ ??" አለኝ ። በፍፁም ላደርገው የማልችለው ነገር ነው በፍፁም !!!! አንገቴን አደለም በማለት እየነቀነኩኝ ግንባሩን ሳምኩትና ከደረቴ ለጥፌ አቀፍኩት ። " በኛ አታምኚም አቡ  እ እንኮ አንቺን ልቤ ላይ ፅፌሻለሁ ለአሁን ሳይሆን ለወደፊት ነው የምመኝሽ  የልጆቼ እናት እንድትሆኚ ነው የምመኘው አንቺ ለምን ተስፋ ቆረጥሽብኝ ???" አለኝ ። ሲያወራ ከልቡ ነው እና ንግግሩ አስለቀሰኝ !!! እንደዛ አደለም ቤኪ የተማሪ ነገር አይዘልቅም የሆነ ሰአት ትረሳኛለህ አልኩት እኔ እንደማረሳው ባውቅም .... " አለምዬን አረሳሽም ልረሳሽም አልችልም ራሴን ብረሳ ራሱ አንቺነትሽ እኔን ያስታውሰኛል  " እያለ ውስጤን የሚነካ ንግግር ተናገረኝ። " አትወጂኝም እውነቱን ንገሪኝ " ብሎ አይን አይኔን ተመለከተው ። በሰአቱ አዎ ማለት አልፈለኩም ። ምክንያቱም እሱን በቀረብኩ ቁጥር ራሴን ማንነቴን ረሳዋለሁ ያ ማለት እናቴን አስከፋለሁ ። በሰአቱ ልዋሸውም አልፈለኩኝም ነበር !!!! ስለዚህ በዝምታ ተመለከተኝ ። " እኔ አንቺ እንደምታስቢያቸው አይነት ወንድ አይደለሁም የድሮ አመለካከቴን ቀይረሽዋል ያለ ፍቃድሽ ስለሆነ  " ይቅርታ ብሎ በስሱ ሳመኝ ። ክው ነው ያልኩት ልቤን ውጋት ነው የተሰማኝ ከዛ ምን ሆነክ ነው ቤኪ አልኩት ። " እንደማፈቅርሽ ለመግለፅ ሌላ ተግባር የለኝም " አለኝ ። ከዛ እንድመልስለት ፍጥጥ ብሎ ሲያየኝ ውበቱን ተመለከትኩና በልቤ ተመርቼ አይኑን ሳምኩት ከዛም አንተን አለመውደድ እንዴት ይቻላል ብዬ ንግግሩን በአጭሩ መለስኩት !!!! የኔ እናት ብሎ እንደለመደው አንገቴ ስር ገብቶ ውሽቅ ብሎ የራሳችን አለም ውስጥ ገብተን ሌላውን ነገር ረስተነዋል። ተቃቅፈን ቁጭ ብለን እያለ በሩ ተንኳኳ ። ለምንድነው የቆለፋችሁት ሲባል የምለውን ሳስብ በድንጋጤ የምሆነው ጠፋኝ ....... . . . ይቀጥላል #ክፍል_1⃣0⃣