ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት
前往频道在 Telegram
''ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዛኋችሁንም ሁሉ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው'' contact : 0111 23 99 96 Facebook : @temromastemar YouTube : https://www.youtube.com/channel/UCZI9ztt_MA_dRnqGH6PTCvw
显示更多1 921
订阅者
+424 小时
+147 天
+3730 天
数据加载中...
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+48
在0个频道中
八月 '26
+98
在0个频道中
Get PRO
七月 '26
+87
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+71
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+51
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+41
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+27
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+24
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+35
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+27
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+42
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+33
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+74
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+37
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+37
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+29
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+33
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+41
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+54
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+41
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+79
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+100
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+34
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+62
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+41
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+50
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+44
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+25
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+32
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+32
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+54
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+30
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+53
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+51
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+38
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+42
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+49
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+58
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+49
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+35
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+29
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+1 047
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 20 九月 | +3 | |||
| 19 九月 | +4 | |||
| 18 九月 | +1 | |||
| 17 九月 | +3 | |||
| 16 九月 | +2 | |||
| 15 九月 | +2 | |||
| 14 九月 | +5 | |||
| 13 九月 | +2 | |||
| 12 九月 | +1 | |||
| 11 九月 | +2 | |||
| 10 九月 | 0 | |||
| 09 九月 | +2 | |||
| 08 九月 | +3 | |||
| 07 九月 | +3 | |||
| 06 九月 | +4 | |||
| 05 九月 | 0 | |||
| 04 九月 | +1 | |||
| 03 九月 | +6 | |||
| 02 九月 | +2 | |||
| 01 九月 | +2 |
频道帖子
| 2 | https://youtu.be/5l2YC0RRblE?si=GNwt677YtIapTb5T | 455 |
| 3 | 没有文字... | 460 |
| 4 | ዓመታዊ የወላጆች በዓል እና የሕፃናት ማዕዶት (ከክፍል ክፍል መሸጋገር) ተከበረ
የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት በየሦስት ወሩ የወላጆች ጉባኤን ያከናውናል፤ በ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም ፫(3) ጉባኤያትን አካሂዶ የዛሬው የዓመቱ ማጠቃለያ ልዩ መርሐ ግብርም ተከናውኗል፤ በዕለቱ
በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ ስምሽን ለልጅ ልጅ ያሳስባሉ በሚለው የዳዊት መዝሙር በጸሎተ ወንጌል መርሐ ግብሩ ተጀምሯል።
በመጋቤ ሃይማኖት ዐምደ ጽዮን አድማሱ ሦስቱ ወላጆች የሥጋ እናትና አባት ፣ መምህራን እና ቤተ ክርስቲያን ልጆችን በማሳደግ ያላቸውን ሚና በሚገልጽ ርዕስ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲኾን በመምህር ሲሳይ የሰ/ት/ ቤቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የዕለቱ መልእክት ከክፍል ክፍል የተሸጋገሩ ሕፃናትን አባላትን እና ወላጆችን እንኳን ደስ አላችኁ! በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፤ የሕፃናት እና ማእከላዊያን ክፍል ሰብሳቢ የኾኑት ወ/ሮ ሰራዊት ተሾመ የሕፃናት ክፍሉ በመሪ ቃልነት የሚጠቀመው የጌታችን የመድኃኒታችን የአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ቃል መሠረት በማድረግ "ሕፃናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው፤" ማር. ፲÷፲፬ የሚለውን ቃል መሪ በማድረግ የክፍሉን አገልግሎት የገለጹ ሲኾን አያይዘውም "ከእነርሱ አንዳንዱን አድን እንደ ኾነ አገልግሎቴን አከብራለኁ።" ሮሜ ፲፩ ÷ ፲፬ የሐዋርያውን ቃል መሠረት አድርጋችኁ ታናናሽ እኅት ወንድሞቻችኹን በነፍስ አባትነታችኁ ስትመክሩ የቆያችኁ ቀሳውስት፤ በመምህርነት ስታስተምሩ መዝሙር ስታስጠኑ የቆያችኁ በክፍል እናትነት አባትነት የምታገለግሉ አሠልጣኞ ፤ እንዲኹም ወላጆች እና አሳዳጊዎችም ኹላችሁም የእግዚአብሔር ክብር ያድልልን በማለት አክብሮትን የሰጡ እና ይኼ የኹላችንም የተባበረ የአገልግሎት ውጤት በመኾኑ እንኳን ደስ አላችኁ! ኹላችንም እንኳን ለዚኽ ቀን አደረሰን በማለት ሕፃናት አባላትን ከክፍል ክፍል መሸጋገራቸውን አብሥረው ወደ ዐቢይ ጉባኤ የሚሸጋገሩ አባላትን በዚኽ የሕፃናት እና ማእከላዊያን ክፍል ውስጥ ለ፲፪ ዓመታት በመቆየታቸው ማስታወሻ በእነርሱ ስም የተዘጋጀላቸውን መጽሔት የገዳማችን የስብከተ ወንጌል እና የምግባረ ሠናይ አገልጋይ የኾኑት መ/ር አባ ገብረ ኢየሱስ ቡራኬን ተቀብለው የዕለቱ መርሐ ግብር ፍጻሜ ኾኗል።
ከቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት ክፍልም የሕፃንነት ጊዜያቸውን አጠቃለው ወደ ዐቢይ ጉባኤ ፶፮ አዳጊ አባላት የተሸጋገሩ መኾኑን የሕፃናት ክፍሉ ገልጿል፡፡
የክፍል ደረጃ እና ስያሜ ወንድ ሴት ድምር
፩ኛ ክፍል ቅዱስ ጢሞቴዎስ ፷ ፺፯ ፩፻፶፯
፪ኛ ክፍል ቅዱስ ቲቶ ፴፩ ፴፫ ፷፬
፫ኛ ክፍል ቅዱስ ሉቃስ ፳፮ ፳፬ ፶
፬ኛ ክፍል ቅዱስ ማርቆስ ፷ ፴፯ ፺፯
፭ኛ ክፍል ቅዱስ ጳውሎስ ፷፮ ፵፭ ፩፻፲፩
፮ኛ ክፍል ቅዱስ በርናባስ ፺፭ ፹፰ ፩፻፹፫
፯ኛ ክፍል ቅዱስ እስጢፋኖስ ፵፪ ፶፮ ፺፰
፰ኛ ክፍል ቅዱስ እንድርያስ ፳፯ ፲፰ ፵፭
፱ኛ ክፍል ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊው ፴፬ ፵፪ ፸፮
፲ኛ ክፍል ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት ፳፪ ፴፬ ፶፮
በጠቅላላ ፯፻፹
የሕፃናት መርሐ ግብር
ረቡዕ ከ10:30 - 11:30
ሳምንታዊ የጸሎት መርሐ ግብር
የአስኳላ ትምህርት ድጋፍ
ቅዳሜ ከ8:00 -11:00
ትምህርት
ዝግጅት ክፍል
አብነት ትምህርት
የአስኳላ ትምልርት እገዛ
የምልክት ቋንቋ
እሑድ ከ3:30 - 6:00
ትምህርት
መዝሙር ጥናት
የአስኳላ ትምህርት እገዛ
እንዲኹም ፦ በየዓመቱ ከሰኔ ወር መጨረሻ ጀምሮ እስከ ነሐሴ ዐሥራ አራት ድረስ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከ2:00 -6:00 የክረምት ትምህርት ይሰጣል።
በዓመት ኹለት ጊዜ መንፈሳዊ ጉዞ ያደርጋሉ። | 432 |
| 5 | https://youtu.be/GmORFZ-ZHdQ | 721 |
| 6 | ተምሮ ማስተማር ተማሪዎቹን አስመረቀ!
በምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት የ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. ፩) ከኹለት እስከ ዐሥር ዓመታት ድረስ የተማሩ የማእከላውያን ክፍል ፶፮ ሕፃናትን፣ ፪) ለሦስት ዓመታት የተማሩ ፬ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎችን፣ ፫) ከሰኞ እና ረቡዕ ጉባኤ ፴፫ ተማሪዎችን ፬) ከቅዳሜ እና እሑድ ጉባኤ ፳፱ ተማሪዎችን ፭) ከእሑድ ብቻ ጉባኤ ፰ ተማሪዎችን ፮) ከርቀት ትምህርት ተማሪዎች ፲፮ ተማሪዎችን ፯) ከምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም ገዳም ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጉባኤያት ለአራት እና ሦስት ዓመታት የተማሩ ፸፫ ተማሪዎችን የገዳሙ መምህር (ዋና አስተዳዳሪ) መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ እና አበው መነኰሳት እንዲኹም እንግዶች በተገኙበት በድምቀት አስመርቋል።
የምርቃት መርሐ ግብሩ በጸሎተ ወንጌል የተከፈተ ሲኾን። በመቀጠልም መንፈሳዊ ግጥሞች፣ መዝሙራት እና ወረብ በተመራቂ ተማሪዎች ቀርቧል። በገዳማችን የስብከተ ወንጌል ክፍል አገልጋይ መ/ር አባ ገብርኤል ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ መ/ር ሲሳይ አበበ የመንፈሳዊ ትምህርትና አገልግሎት ማስፋፋት፣ በተማሪዎችም ዘንድ የእምነት፣ የዕውቀት እና የአገልግሎት መንፈስን ማጠናከር የተመራቂዎች ዋና ዓላማ ሊኾን እንደሚገባ ገልጸዋል።
በቆይታቸው ጊዜ ተመራቂዎቹ ያገኙትን መንፈሳዊ ዕውቀት በሕይወታቸው እና በአገልግሎታቸው እንዲተገብሩ የገዳሙ መምህር መጋቤ ኅሩይ አባ ኤልያስ በልሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም ተመራቂዎቹ ሽልማቶችን እና የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለው የመንፈሳዊ ጉዞአቸውን ወደ ቀጣዩ ደረጃ አሸጋግረዋል። | 966 |
| 7 | ቤተ ሳይዳ መጽሔት ኹለተኛ ዕትም የዘመን አቆጣጠር በሚል ዐምድ ይዛ መታለች!
ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ነክተው ሙሉውን ያንብቡ ለወዳጅ ዘመድ ያጋሩልን!!!
https://betesayda.temro.org/ | 772 |
| 8 | የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ምርቃር መርሐ ግብር ጀምሯል | 717 |
| 9 | https://youtu.be/NHXsP2RdfHI | 807 |
| 10 | 没有文字... | 938 |
| 11 | ዜና
የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት የ፳፻፲ወ፱ ዓ.ም. የበጀት ዕቅዱን አጸደቀ!
በነሐሴ ፳፬ /፳፻፲ወ፰ (24/2018) ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቱ ሥራ አመራር ጉባኤ ሰብሳቢ በዲ/ን መስፍን ተ/ዮሐንስ የተጠራው ጠቅላላ ጉባኤ እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ አከናውናቸዋለኁ ያላቸውን የዐሥራ ሰባት ሚሊዮን ብር ዕቅዱን አስጸደቀ።
በጠቅላላ ጉባኤው የ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም የሥራ ክንውን ሥራ አመራሩ ያከናወነውን እና በሥራ አስፈጻሚው የተፈጸሙትን ዘገባዎች እንዲኹም ሳይፈጸሙ የቀሩትን እና ከዕቅድ ውጪ የተከናወኑትን በቅደም ተከተላቸው በሥራ አመራር ጉባኤው ሰብሳቢ በዲ/ን መስፍን ተ/ዮሐንስ እና በዋና ሥራ አስፈጻሚው መ/ር ሲሳይ አበበ ቀርቦ ከዚኹም ጋር የሥራ ግምገማ ግኝቶች እስከ መፍትሔው እና የሒሳብ ዘገባ በሰ/ት/ቤቱ ኦዲት እና ኢንስፔክሽን አገልግሎት ሐላፊ በአቶ አንተነኽ ታረቀኝ እና በሒሳብ ክፍል ሐላፊው አቶ ተረፈ አማረ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የ፳፻፲ወ፱ ዓ.ም. የተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት የሥራ ዕቅድ ቀርቦ ለዚኹ መፈጸሚያ በጀት ዐሥራ ሰባት ሚሊየን ሦስት መቶ ሠላሳ ሁለት ሺሕ ኹለት መቶ ዐሥራ ዘጠኝ ብር ከስድሳ ኹለት ሣንቲም (17,332,219.62) እንደሚያስፈልግ በሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ በመ/ር ምስጋናው ደፋር በኩል ቀርቦ ጸድቋል።
በቀጣይ ሰ/ት/ቤቱ ሊተገብር ካቀዳቸው ዋና ዋና ተግባራትም ከ፲፱፻፴ወ፱ ዓ.ም ጀምሮ እስከ ፳፻፲ወ፱ ዓ.ም የ፹ (80) ዓመት ጉዞ ክብረ በዓል ስለሚከበር በዚኽ ወቅት የሕንጻ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ እንደሚቀመጥ መታቀዱ ተሰምቷል፡፡ ተምሮ ማስተማር ይመራበት የነበረው መመሪያ ዘመኑን በዋጀ መልኩ ተሻሽሎ ዐዲስ መዋቅር በማቅረብ መንፈሳዊ አገልግሎት እና የአስተዳደር ሥራዎችን በመነጠል እንዲሠራ ለጉባኤው ቀርቦ ጸድቋል።
ከዚኽ በተጨማሪም በጠቅላላ ጉባኤው ላይ በተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ የክፍል ደረጃ የተዘጋጀው የሥርዓተ ትምህርት ፍሬም ወርክ (የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ)፣ ኤም ኤል ሲ (አነስተኛ የትምህርት ብቃት ) እና የትምህርት እና የጊዜ ምጣኔ ያሟላ የተሻሻለ ሥርዓተ ትምህርት የጸደቀ ሲኾን ከመጪው ዘመነ ሉቃስ ፳፻፲ወ፱ ዓ.ም. ጀምሮ በሰንበት ት/ቤቱ የሚተገበር ይኾናል።
በመጨረሻም የ፳፻፲ወ፱ ዓ/ም በሰንበት ት/ቤቱ ሊሠሩ የታቀዱት ዕቅዶች ላይ ከጠቅላላ ጉባኤው ጥያቄ ቀርቦ ምላሽ ከተሰጠ በኋላ፤ ከሰባ ዓመታት በላይ ያገለገሉ ነባር አባላት የተምሮ ማስተማር ጉዞ በምን መልኩ እዚኽ እንደ ደረሰ እያስታወሱ ለወደ ፊቱም ከመድኀኔ ዓለም ቸርነት እንድንበረታ እና እንድንጠነክር አሳስበው ጉባኤው በቀሲስ ዮሐንስ ተስፋዬ በጸሎት ተዘግቷል ። | 802 |
| 12 | https://forms.gle/4XYVEi7o4tm6pDQH8 | 849 |
| 13 | አስቸኳይ የሥራ ማስታወቂያ (ዋና ጸሐፊ)
ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት ክፍት የሥራ መደብ ላይ ባለሙያ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ማመልከት ትችላላችኁ!
📋 የሥራ መደብ ዝርዝር
የሥራ መደብ: ዋና ጸሐፊ
ብዛት: አንድ
የቅጥር ኹኔታ: በኮንትራት
ደሞዝ: በስምምነት
የሥራ ቦታ: ተምሮ ማስተማር
🎓 የትምህርት ዝግጅት
የመጀመሪያ ዲግሪ በማኔጅመንት፣ ቢዝነስ ማኔጅመንት፣ ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን
፣ ሰፕላይ/ማቴሪያል/ሎጅስቲክስ ማኔጅመንት
ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት፣ የትምህርት መስክ የተመረቀ/ች።
⏳ የሥራ ልምድ
አራት ዓመታት እና ከዚያ በላይ የሥራ ልምድ ያለው/ላት።
📝 የማመልከቻ መመሪያ
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች፡
ማመልከቻዎን፣
የተሟላ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃ ዋናውን ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር በመያዝ፣
በተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት የሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ በአካል በመቅረብ ወይም በወኪል መመዝገብ ትችላላችኁ።
⚠️ ማስታወሻ፡
፩.መወዳደር የሚችለው የሰ/ት/ቤቱ አባል የኾነ ብቻ ነው።
፪· አመልካቾች ሙሉ ስም፣ የስልክ አድራሻ፣ የሚያመለክቱበትን የሥራ መደብና ደረጃ በተዘጋጀው የማመልከቻ ቅጽ ላይ መሙላትና መፈረም ይኖርባቸዋል።
የፈተና ቀን በውስጥ ማስታወቂያ ይገለጻል።
(እባክዎ ይኽንን መልእክት ለሚያውቋቸው አባላት እንዲደርሳቸው ያድርጉ!) | 1 065 |
| 14 | ለአባላት በሙሉ
በመርሐ ግብር መደራረብ ምክንያት እና ጸሎተ ፍትሐቱ እሑድ ጠዋት በአራት ሰዓት መኾን ስለ አለበት ወደ መስከረም ዐሥር ፳፻፲ወ፱ (2019) ዓ.ም. የተሸጋገረ መኾኑን እናሳስባለን። | 939 |
| 15 | ለአባላት በሙሉ
"ያገለገለኽን ሰው ሞት ቸል አትበል፤ " መ.ሲራክ ፴፰÷፲፮
በየዓመቱ ማጠናቀቂያ በመደበኛ ጉባኤያችን ሰዓት በአጸደ ነፍስ ያሉ አባላትን የምናስብበት የጸሎተ ፍትሐት መርሐ ግብር እንደምናካሂድ ይታወቃል፤ በዚኹ መሠረት የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ ሠላሳ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. ከስምንት ሰዓት እስከ ዐሥር ሰዓት ድረስ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ (በቅኔ ማሕሌት) ጉባኤው እና ጸሎተ ፍትሐቱ በገዳማችን መምህር (አስተዳዳሪ) መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ፣ በአበው መነኮሳት እና አኀው ዲያቆናት መሪነት የሚካሄድ ስለ ኾነ አባላት በዕለቱ እና በሰዓቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንድትሰበሰቡ ይኹን፤
በተጨማሪም ያረፉ አባላትን አንድ አንድ ፎቶ ከዕለቱ በፊት እንድታመጡ ይኹን።
"ይኄይስ: ስም: ሠናይ: እም: ቅብዐ፡ መዓዛ፤ ወዕለተ: ሞት: እም: ዕለተ: ልደት፤ ከመልካም ሽቱ መልካም ስም፤ ከመወለድ ቀንም የሞት ቀን ይበልጣል/ይሻላል።" መ.መክብብ ፯÷፩
"ኦ: ክርስቶስ: ዘትፈትሖሙ: ለሙቁሐን፤ ፍትሓ: ወአግዕዛ: ለነፍሰ: ኲሎሙ: ክርስቶሳውያን: እም፡ ኩሉ፡ ሐዘን፡ ወአንብራ፡ ኀበ፡ ተጋብኡ፡ ቅዱሳን፤ በእንተ፡ ሚካኤል፡ ቃለ፡ አብ፡ ሰማኢ፤ ወገብርኤል፡ መዋዒ፤ ወሩፋኤል፡ እሳት፡ በላኢ፤ ወዑራኤል፡ ማኅፈድ ጽኑዕ፡ ቅድመ፡ ገጸ፡ ጸላኢ፤ ሥረይ፡ ላቲ፡ ኃጢአታ፡ ለነፍሰ፡ ክርስቲያን!" ግብረ ሕማማት ገጽ ፺፭~፺፮÷፵፮~፵፯
የታሰሩትን የምትፈታ ክርስቶስ ሆይ! የአብን ቃል ስለሚሰማ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ብለኽ፣ ድል ስለሚያደርገው ስለ ቅዱስ ገብርኤል ብለኽ፣ የሚባላ እሳት ስለ ኾነው ስለ ቅዱስ ሩፋኤል ብለኽ፣ ከጠላት ፊት የጸና መሸፈኛ ስለ ኾነው ስለ ቅዱስ ዑራኤል ብለኽ የኹሉንም ክርስቲያኖች ነፍስን ከሐዘን ኹሉ ፍታቸው፤ ቅዱሳን በተሰበሰቡበትም አስቀምጣቸው፤ የክርስቲያንንም ኹሉ ነፍስ ኃጢአቷን ደምስስላት!!! | 1 106 |
| 16 | https://youtu.be/-Z0Dgy2eYIc | 811 |
| 17 | https://youtu.be/Bi2J8MJsmEc?si=YYTGks1kJVp-tn7W | 735 |
| 18 | https://www.tiktok.com/@temro.media/video/7676109038400048392 | 981 |
| 19 | https://www.tiktok.com/@temro.media/video/7676109038400048392 | 1 |
| 20 | https://youtu.be/dmxYE7O59T4?si=ZoQ5W9td7n-uUx6B | 1 004 |
