ch
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

前往频道在 Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

显示更多

📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览

频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 369 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 633,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 187

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 369 名订阅者。

根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -46,过去 24 小时变化为 37,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.37%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.87% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 438 次浏览,首日通常累积 1 210 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 22

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 369
订阅者
+3724 小时
+367
-4630
帖子存档
++++#ታላቍ_መቃርዮስ_እንዲህ_አሉ#+++++ ጥላቻ የሚመጣው ቂምን ወይም ክፉን ከመሰወር ነው፣ ክፉን መሰወር ደግሞ ከኩራት፣ ኩራት ከግብዝነት፣ ግብዝነት ከእምነት ጉድለት፣ የእምነት ጉድለት ከልብ ድንዛዜ፣ የልብ ድንዛዜ ከቸልተኝነት፣ ቸልተኝኀት ከስንፍና፣ ስንፍና ከተስፋ መቁረጥ፣ ተስፋ መቁረጥ ከትዕግሥት ማጣት፣ ትዕግሥት ማጣት ከትዕቢት ይመጣል። ጸሎት በፍቅር ላይ ይመሠረታል፣ ፍቅር ደግሞ በደስታ፣ ደስታ ደግሞ በቅንነት፣ ቅንነት በትሕትና፣ ትሕትና በአገልግሎት፣ አገልግሎት በተስፋ፣ ተስፋ በእምነት፣ እምነት በመታዘዝ፣ መታዘዝ በግልጸኝነት ወይም ራስን ቀለል በማድረግ ላይ ይመሠረታል። Ven. Macarius the Great https://t.me/phronema

#ምስባክ #መጻጕዕ ዘመጋቢት ፳፪ የምስባኩንና የመዝሙሩን ዜማ በተራኪ አፕ ጣቢያችን ያድምጡ https://terakiapp.page.link/h6JfpJoTT5HgXr9d9
#ምስባክ #መጻጕዕ ዘመጋቢት ፳፪ የምስባኩንና የመዝሙሩን ዜማ በተራኪ አፕ ጣቢያችን ያድምጡ https://terakiapp.page.link/h6JfpJoTT5HgXr9d9

ድንግል ሆይ ! ሰማይ በስፋቱ ብራና ቢሆን ባሕርም ቀለም ቢሆን ምስጋና የተመላውን ክብርሽን ገናንንትሽን ለመጻፍ በዚህም ምስጋናሽን ለመፈጸም አልችልም ፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ #Orthodox_Quo
ድንግል ሆይ ! ሰማይ በስፋቱ ብራና ቢሆን ባሕርም ቀለም ቢሆን ምስጋና የተመላውን ክብርሽን ገናንንትሽን ለመጻፍ በዚህም ምስጋናሽን ለመፈጸም አልችልም ፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ #Orthodox_Quotes

የሰንበት ትምህርት ቤታችን የዘውትር አገልጋይን ዲ/ን ዮሴፍ ሰውነት #ታስሯል ። ++++++ ወንድማችን ዲያቆን ዮሴፍ ፍሥሓ ሰውነት [Yosef Fiseha Sewunet]፥ በነገረ መለኮት ምሩቅነቱ ፣ በታሪክ መምህርነቱ እና በሚድያ ባለ ሙያነቱ ከሚሰገው አገልግሎት ባሻገር ለቤተ ክርስቲያን አንድነት፣ ለሀገር ዕድገት፣ ለሰዎች ስኬት የሚጨነቅ ቀና ወንድም ነው። ይኼን እውነትም በፌስ ቡክ ገጹ ከሚጽፋቸው መልእክታቱ መረዳት ይቻላል። በተለይም ትውልዱ ቁም ነገር አዘል መጻሕፍትን እንዲያነብ ለማትጋት በሚያደርገው ወደር የለሽ ጥረት ይታወቃል። ለዚኽም ዐዳዲስ መጻሕፍት በታተሙ ቍጥር ይዘታቸውን እያስተዋወቀ፣ አንባብያንን አወዳድሮ እያሸለመ፣ ከፍ ሲልም በሚድያ እያቀረበ የሚሠራው በጎ ሥራ ማስረጃ ነው። ከማንም ምንም ጥቅም ሳያገኝ በነጻ ይኼን ኹሉ ማድረጉ፥ ቅንነቱን ያሳያል። ወንድማችን ዮሴፍ፥ ከዚኽ በጎ አስተዋፅኦው ባለፈ በቤተ ክርስቲያንም በሀገርም ጉዳይ የሚያየውን ክፍተት በምክንያት ይተቻል። ጥሩ ሥራ ተሠርቶ ሲያይ ደግሞ ያደንቃል። በድብቅ ማሤርን እና ነገር መሥራትን ግን ይጸየፋል። ከቅንነቱ በተጨማሪ ይኼ ሰብእናው ይማርከኛል። እንዲኽ ዐይነት ሰው ጠላት እንደሚበዛበት በራሴ ስለ ተማርኹም ሕይወቱ ያሳዝነኛል። ይኼ ቅን ወንድማችን፥ በቅርቡ በፌስ ቡክ በጻፈው ፖለቲካዊ ሒስ ምክንያት ለእስር መዳረጉን ከራሱ አንደበት አረጋግጫለኹ። መታሰሩን ቶሎ ባለ መስማቴ ለመጠየቅ ብዘገይም፥ በዛሬው ዕለት፥ ከኹለት ወንድሞች ጋራ ፖሊስ ጣቢያ ሔጄ ጠይቄዋለኹ። ለብዙ ሰው የሚጠቅም ሐሳብ ያለው ወንድማችን ማንም ሳይጠይቀው በመሰንበቱም አዝኛለኹ። በእርግጥ የእውነት አምላክ እንደማይለየው አምናለኹ። ዛሬ ልንጠይቀው በሔድን ጊዜ ከራሱ አንደበት እንደ ሰማኹት፥ ዲያቆን ዮሴፍ፥ በፌስ ቡክ በጻፈው ፖለቲካ ነክ አስተያየት ምክንያት፥ ከመጋቢት ፱ ቀን ፳፻፲፮ ዐ.ም ጀምሮ፥ ከዐዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አጠገብ [ግቢ ውስጥ] በሚገኘው ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ ሰንብቷል። የሚፈታበትን ቀንም በተስፋ ይጠባበቃል። ፖሊስ ክስ ባይመሠረትበትም ያሰረው በጽሑፉ ምክንያት መኾኑን ግን ነግሮታል። ይኸውም ወቅታዊ ጉዳይ ነው። የታሰረበት ምክንያት ወቅታዊ ጉዳይ እንደ መኾኑ፥ በግልጽ ሳይከሰስ፣ ጉዳዩም ለፍርድ ቤት ሳይቀርብ ያለ ጠያቂ በፖሊስ ጣቢያ ሊቆይ ይችላል። ይኼ ኹኔታ ደግሞ በወንድማችን ላይ ሥነ ልቡናዊ ጕዳት ያመጣል። ከሥራውም ከኑሮውም በከንቱ ይስተጓጐላል። ከዚኽም በላይ የብቸኝነት እና የባይተዋርነት ስሜት ሊሰማው ይችላል። ይኼ ኹሉ ጣጣ በወንድማችን ላይ ከመድረሱ በፊት ኹላችንም ድምፅ ኾነን ልናስፈታው ይገባል። በመጨረሻም በመንግሥትም በግልም ተቋማት የምትሠሩ ኦርቶዶክሳውያን፥ ይልቁንም የሕግ ባለ ሙያዎች፥ ከሚመለከተው አካል ጋራ በመነጋገር ዮሴፍን እንድታስፈቱት፤ የእስር ጊዜው ያጥር ዘንድም እንድትፋጠኑለት፤ በአጠቃላይ መላው ኦርቶዶክሳውያን፥ የዮሴፍ አምላክ በሰላም ያስፈታው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንድንጮኽለት በወንድምነት ስሜት እጠይቃለኹ!! መውጫ ቅኑ ወንድሜ ዮሴፍ ሆዬ፥ መታሰርኽን ከሰማኹባት ሰዓት ጀምሬ ስለ አንተ ተጨንቄአለኹ። እውነትን ይዘኽ የምትሞግት፣ በሰው ስኬት የምትደሰት፣ በሰው ላይ ክፉ ነገር የማትዶልት ቅን ወንድም መኾንክን ዐውቃለኹና። ስለዚኽም እስራትኽ እስራቴ፣ ጭንቀትኽ ጭንቀቴ ነው። ከልቤ የጻፍኹት ይኽ መልእክቴ ፍሬ አፍርቶ በቅርቡ እንደምትፈታ ተስፋ አደርጋለኹ። በተረፈ ስሙ ስምኽ ነውና የዮሴፍ አምላክ እንዳይለይኽ ወንድምኽ እመኝልኻለኹ!! © ኤፍሬም የኔሰው