fa
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

رفتن به کانال در Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

کانال Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 366 مشترک است و جایگاه 5 631 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 191 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 366 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 20 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -39 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -5 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.39% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.98% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 441 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 226 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 22 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 21 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 366
مشترکین
-524 ساعت
+297 روز
-3930 روز
آرشیو پست ها
++++#ታላቍ_መቃርዮስ_እንዲህ_አሉ#+++++ ጥላቻ የሚመጣው ቂምን ወይም ክፉን ከመሰወር ነው፣ ክፉን መሰወር ደግሞ ከኩራት፣ ኩራት ከግብዝነት፣ ግብዝነት ከእምነት ጉድለት፣ የእምነት ጉድለት ከልብ ድንዛዜ፣ የልብ ድንዛዜ ከቸልተኝነት፣ ቸልተኝኀት ከስንፍና፣ ስንፍና ከተስፋ መቁረጥ፣ ተስፋ መቁረጥ ከትዕግሥት ማጣት፣ ትዕግሥት ማጣት ከትዕቢት ይመጣል። ጸሎት በፍቅር ላይ ይመሠረታል፣ ፍቅር ደግሞ በደስታ፣ ደስታ ደግሞ በቅንነት፣ ቅንነት በትሕትና፣ ትሕትና በአገልግሎት፣ አገልግሎት በተስፋ፣ ተስፋ በእምነት፣ እምነት በመታዘዝ፣ መታዘዝ በግልጸኝነት ወይም ራስን ቀለል በማድረግ ላይ ይመሠረታል። Ven. Macarius the Great https://t.me/phronema

#ምስባክ #መጻጕዕ ዘመጋቢት ፳፪ የምስባኩንና የመዝሙሩን ዜማ በተራኪ አፕ ጣቢያችን ያድምጡ https://terakiapp.page.link/h6JfpJoTT5HgXr9d9
#ምስባክ #መጻጕዕ ዘመጋቢት ፳፪ የምስባኩንና የመዝሙሩን ዜማ በተራኪ አፕ ጣቢያችን ያድምጡ https://terakiapp.page.link/h6JfpJoTT5HgXr9d9

ድንግል ሆይ ! ሰማይ በስፋቱ ብራና ቢሆን ባሕርም ቀለም ቢሆን ምስጋና የተመላውን ክብርሽን ገናንንትሽን ለመጻፍ በዚህም ምስጋናሽን ለመፈጸም አልችልም ፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ #Orthodox_Quo
ድንግል ሆይ ! ሰማይ በስፋቱ ብራና ቢሆን ባሕርም ቀለም ቢሆን ምስጋና የተመላውን ክብርሽን ገናንንትሽን ለመጻፍ በዚህም ምስጋናሽን ለመፈጸም አልችልም ፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ #Orthodox_Quotes

የሰንበት ትምህርት ቤታችን የዘውትር አገልጋይን ዲ/ን ዮሴፍ ሰውነት #ታስሯል ። ++++++ ወንድማችን ዲያቆን ዮሴፍ ፍሥሓ ሰውነት [Yosef Fiseha Sewunet]፥ በነገረ መለኮት ምሩቅነቱ ፣ በታሪክ መምህርነቱ እና በሚድያ ባለ ሙያነቱ ከሚሰገው አገልግሎት ባሻገር ለቤተ ክርስቲያን አንድነት፣ ለሀገር ዕድገት፣ ለሰዎች ስኬት የሚጨነቅ ቀና ወንድም ነው። ይኼን እውነትም በፌስ ቡክ ገጹ ከሚጽፋቸው መልእክታቱ መረዳት ይቻላል። በተለይም ትውልዱ ቁም ነገር አዘል መጻሕፍትን እንዲያነብ ለማትጋት በሚያደርገው ወደር የለሽ ጥረት ይታወቃል። ለዚኽም ዐዳዲስ መጻሕፍት በታተሙ ቍጥር ይዘታቸውን እያስተዋወቀ፣ አንባብያንን አወዳድሮ እያሸለመ፣ ከፍ ሲልም በሚድያ እያቀረበ የሚሠራው በጎ ሥራ ማስረጃ ነው። ከማንም ምንም ጥቅም ሳያገኝ በነጻ ይኼን ኹሉ ማድረጉ፥ ቅንነቱን ያሳያል። ወንድማችን ዮሴፍ፥ ከዚኽ በጎ አስተዋፅኦው ባለፈ በቤተ ክርስቲያንም በሀገርም ጉዳይ የሚያየውን ክፍተት በምክንያት ይተቻል። ጥሩ ሥራ ተሠርቶ ሲያይ ደግሞ ያደንቃል። በድብቅ ማሤርን እና ነገር መሥራትን ግን ይጸየፋል። ከቅንነቱ በተጨማሪ ይኼ ሰብእናው ይማርከኛል። እንዲኽ ዐይነት ሰው ጠላት እንደሚበዛበት በራሴ ስለ ተማርኹም ሕይወቱ ያሳዝነኛል። ይኼ ቅን ወንድማችን፥ በቅርቡ በፌስ ቡክ በጻፈው ፖለቲካዊ ሒስ ምክንያት ለእስር መዳረጉን ከራሱ አንደበት አረጋግጫለኹ። መታሰሩን ቶሎ ባለ መስማቴ ለመጠየቅ ብዘገይም፥ በዛሬው ዕለት፥ ከኹለት ወንድሞች ጋራ ፖሊስ ጣቢያ ሔጄ ጠይቄዋለኹ። ለብዙ ሰው የሚጠቅም ሐሳብ ያለው ወንድማችን ማንም ሳይጠይቀው በመሰንበቱም አዝኛለኹ። በእርግጥ የእውነት አምላክ እንደማይለየው አምናለኹ። ዛሬ ልንጠይቀው በሔድን ጊዜ ከራሱ አንደበት እንደ ሰማኹት፥ ዲያቆን ዮሴፍ፥ በፌስ ቡክ በጻፈው ፖለቲካ ነክ አስተያየት ምክንያት፥ ከመጋቢት ፱ ቀን ፳፻፲፮ ዐ.ም ጀምሮ፥ ከዐዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አጠገብ [ግቢ ውስጥ] በሚገኘው ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ ሰንብቷል። የሚፈታበትን ቀንም በተስፋ ይጠባበቃል። ፖሊስ ክስ ባይመሠረትበትም ያሰረው በጽሑፉ ምክንያት መኾኑን ግን ነግሮታል። ይኸውም ወቅታዊ ጉዳይ ነው። የታሰረበት ምክንያት ወቅታዊ ጉዳይ እንደ መኾኑ፥ በግልጽ ሳይከሰስ፣ ጉዳዩም ለፍርድ ቤት ሳይቀርብ ያለ ጠያቂ በፖሊስ ጣቢያ ሊቆይ ይችላል። ይኼ ኹኔታ ደግሞ በወንድማችን ላይ ሥነ ልቡናዊ ጕዳት ያመጣል። ከሥራውም ከኑሮውም በከንቱ ይስተጓጐላል። ከዚኽም በላይ የብቸኝነት እና የባይተዋርነት ስሜት ሊሰማው ይችላል። ይኼ ኹሉ ጣጣ በወንድማችን ላይ ከመድረሱ በፊት ኹላችንም ድምፅ ኾነን ልናስፈታው ይገባል። በመጨረሻም በመንግሥትም በግልም ተቋማት የምትሠሩ ኦርቶዶክሳውያን፥ ይልቁንም የሕግ ባለ ሙያዎች፥ ከሚመለከተው አካል ጋራ በመነጋገር ዮሴፍን እንድታስፈቱት፤ የእስር ጊዜው ያጥር ዘንድም እንድትፋጠኑለት፤ በአጠቃላይ መላው ኦርቶዶክሳውያን፥ የዮሴፍ አምላክ በሰላም ያስፈታው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንድንጮኽለት በወንድምነት ስሜት እጠይቃለኹ!! መውጫ ቅኑ ወንድሜ ዮሴፍ ሆዬ፥ መታሰርኽን ከሰማኹባት ሰዓት ጀምሬ ስለ አንተ ተጨንቄአለኹ። እውነትን ይዘኽ የምትሞግት፣ በሰው ስኬት የምትደሰት፣ በሰው ላይ ክፉ ነገር የማትዶልት ቅን ወንድም መኾንክን ዐውቃለኹና። ስለዚኽም እስራትኽ እስራቴ፣ ጭንቀትኽ ጭንቀቴ ነው። ከልቤ የጻፍኹት ይኽ መልእክቴ ፍሬ አፍርቶ በቅርቡ እንደምትፈታ ተስፋ አደርጋለኹ። በተረፈ ስሙ ስምኽ ነውና የዮሴፍ አምላክ እንዳይለይኽ ወንድምኽ እመኝልኻለኹ!! © ኤፍሬም የኔሰው