አቡቀለምሲስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
前往频道在 Telegram
አቡቀለምሲስ ማለት ረአየ ኅቡኣት አበ ራዕይ አበ ትንቢት ማለት ሲሆን የተሰወረውን የተደበቀውን የተከደነውን የሚገልጥ ማለት ነው። መሠራታዊ ዓለማው በሀገረ ስብከታችን ብሎም በመላ ቤተ ክርስቲያናችን የተሰወሩ ገዳማትን የተደበቁ ሊቃውንትን የተከደኑ ታሪኮችን የተሸሸጉ ቅርሶችን ማውጣት እና የተንሸዋረረ ታሪክ ማስተካከልና የጎበጠውን አዲሱን ትውልድ ማነጽ ነው መረጃ t.me/AbukelemsisSMSbot
显示更多2 437
订阅者
-224 小时
-97 天
-3430 天
帖子存档
#ከፍተኛው_ድጋፍ_ወደ_ግሸን_አቅንቷል!!
የ5.5 ሚሊዮን ብር እህልና ቁሳቁስ በ14 የጭነት መኪናዎች ወደ ገዳሙ መጓጓዝ ጀመረ፤ ለዘላቂ ድጋፍ የሚሆን ሁለገብ ሕንጻ ሊገነባ ነው።
የግሸን ደብረ ከርቤ ጽዮን ማርያም “የሸዋ ማኅበር” በገዳሙ ለሚገኙ መናንያን ከ5.5 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የምግብ እህል እና ቁሳቁስ ድጋፍ መጓጓዝ ጃመረ!!
ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ሚዲያ፥ ደብረ ብርሃን)
+++++ ++++ +++++ +++++ ++++
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኘው አንጋፋው “የግሼን ደብረ ከርቤ ጽዮን ማርያም የሸዋ ማኅበር” በታሪኩ ከፍተኛ የሆነውንና የማጓጓዣ እና የጉልበት ወጪን ሳይጨምር በገንዘብ ሲሰላ 5ሚሊዮን 5 መቶ ሺህ ብር ግምት የሚያወጣ ዓመታዊ የምግብ እህል አይነትና እና ቁሳቁስ ድጋፍ ለግሸን መነነኮሳት ማጓጓዝ ጀምሯል።
ከተመሠረተ 80 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ማኅበር፣ በ1992 ዓ.ም በመነኮሳቱ ላይ ተከስቶ በነበረው የረሀብ አደጋ ምክንያት የጀመረውን ይህንኑ ዓመታዊ የበጎ አድራጎት ሥራ ከቅድስት አርሴማ የጉዞና ጽዋ ማኅበር እና ከተለያዩ በጎ አድራጊ ኦርቶዶክሳዊያንና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በየዓመቱ በሰፊው እያከናወነ 26 ዓመታትን አስቆጥሯል።
በዚህ ዓመት የተሰበሰበውና በ14 የጭነት መኪናዎች የሚጓጓዘው ግዙፍ ድጋፍ 2 መቶ 80 ኩንታል ስንዴ ፣2 መቶ 10 ኩንታል ሽምብራ፣ 60 ኩንታል የዳቦ ዱቄት፣ 22 ኩንታል ጨው ፣ 22 ካርቶን ሳሙና፣ 22 ካርቶን ክብሪት ፣ ለ2019 ዓ.ም ለመስከረም ማርያም ዝክር ግብዓት የሚሆን 80 ኩንትል የእንጀራና የጠላ እህል እንዲሁም 1 መቶ 40 ሺህ ብር የማስፈጫ በጥሬ ገንዘብ ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ ዕርዳታ በመረጃ ለተያዙ 460 መነኮሳት፣ ባህታውያንና ነዳያን ለእያንዳንዳቸው በዕቅዱ መሠረት የሚከፋፈል ሲሆን፣ በመረጃ ላልተያዙ ደጅ ጠኝዎች፣ ለአብነት ተማሪዎችና ለ7 አብያተ ክርስቲያናትም ድጋፍ እንደሚደረግ ተጠቅሷል።
በሌላ በኩል፣ ማኅበሩ ለዘመናት አገልግሎት ሲሰጥበት የነበረው አዳራሽ ለቤተ ክርስቲያን ሙዚየም ግንባታ በመፍረሱ ምክንያት፣ ቦታውን የሚመጥን አዲስ ዘመናዊ ሕንጻ ለመገንባት መስከረም 20 ቀን 2018 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ መቃርዮስ አማካኝነት የመሠረት ድንጋይ መጣሉንና አሁን ላይ ወደ ግንባታ ለመግባት ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን በሪፖርቱ ተገልጿል።
ሕንጻው ሲጠናቀቅ ቋሚ ገቢ በማመንጨት መነኮሳቱንና የአብነት ተማሪዎቹን በዘላቂነት ለመደገፍ ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተመላክቷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የጠበሴ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የ4ቱ ጉባኤያት መምህር መራኄ ሊቃውንት ያዕቆብ ተክለ አረጋይ “ቸር አገልጋይ ማነው?” በሚል ርእስ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።
መምህሩ ባስተላለፉት መልእክት አፄ ዘርዐ ያዕቆብ ያስቀመጡበትን የመስቀል ቅርፅ ታሪኩ ሳይነካ ለትውልድ እንዲቀጥል ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
መምህሩ አክለውም ለግሸን ቅድስት ማርያም መነኮሳት የሚደረገውን ድጋፍ ዘላቂ ለማድረግ እየተገነባ ያለው የገቢ ማስገኛ ሁለገብ ሕንጻ እጅግ የሚያስመሰግን ተግባር መሆኑን ገልጸው “ይህ ሥራችሁ ምንጊዜም ታሪክ የማይረሳው፣ እግዚአብሔር አምላክ በሰማያዊ መዝገቡ የሚመዘግበውና ሥራችሁን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ የምትሰንደው ሕያው ምስክር ነው” በማለት አበረታተዋል።
በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መደራጃ ክፍል ሓላፊ መልአከ ፀሐይ ቀሲስ እስጢፋኖስ ሰዕሌ፣ ማኅበሩ እያከናወነ ያለውን ተግባር አድንቀው።“እየሠራችሁት ያለው ሥራ እጅግ የበረከት ሥራ ነው፤ እግዚአብሔር አብርሃምን “በረከት ሁን” ብሎ እንደባረከው ሁሉ፣ እናንተም የሸዋ በረከት ናችሁ” በማለት የሥራውን ታላቅነት ገልጸዋል፤ እያከናወናችሁት ያለው መልካም ተግባር ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለችና የተቀደሰች ሀገር እያስረከባችሁ ነው በማለት መልእክት አስተላልፈዋል።
የሽኝት መርሐ ግብሩ በደብረ ብርሃን ከተማ አጅብ በሚገኘው የግሼን ደብረ ከርቤ ጽዮን ማርያም “የሸዋ ማኅበር” ሕንጻ ላይ የማኅበሩ አባላት እና ጥሪ የተደረግላቸው እንግዶች በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን ድጋፉን ለመነኮሳቱ ለማድረስ 2 መኪና አባላት ጉዞ መጀመራቸው ተገልጿል።
ግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ከአዲስ አበባ በ4 መቶ 81 ፣ ከደብረ ብርሃን በ3 መቶ 51 እንዲሁም ከደሴ ከተማ በ80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ የመስቀል ቅርፅ ያላት ታሪካዊና አስደናቂ ገዳም ናት።
የበረከቱ ተካፋይ መሆን ለምትፈልጉ የማኅበሩ የባንክ አካውንቶች፦ ግሸን ደብረ ከርቤ ጽዮን ማርያም የሸዋ ማኅበር ብላችሁ።
⓵ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦1000 110 205 574
⓶አቢሲኒያ ባንክ፦40 064 338 ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ።
#አቡቀለምሲስ_ሚዲያ #የሸዋ_ማኅበር #ጉዞ_ወደ_ግሸን_ማርያም #ደብረ_ብርሃን_የበጎ_አድራጎት_ድጋፍ #ኦርቶዶክስ #ግሸን_ማርያም_መነኮሳት
በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና።
ሰኔ ፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም(አቡቀለምሲስ ሚዲያ: ደብረ ብርሃን)
++++++++++++++++++++++
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች የተከሰተውን ችግር ተከትሎ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ በሥፍራው በመገኘት ተጎጂዎችን እንዲያጽናና ጊዜያዊ ርዳታም እንዲያደርግ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ማለዳ ወደ አርሲ ዞን አቦምሳ ወረዳ በመጓዝ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጽናንቷል፤ ጊዜያዊ እርዳታም አበርክቷል።
በአቦምሳ ወረዳ የትንሣኤ ብርሃን ደብረ ገነት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በመገኘት ተጎጂ ኦርቶዶክሳዊያንን ያጽናኑት
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ቅድስት ቤተክርስቲያን በበኦርቶዶክሳዊያን ልጆቿ ላይ በደረሰው ጉዳት እጅግ በጣም ማዘኗን ገልጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሞቱት ወገኖቻችን መንግስተሰማያትን እንዲያወርስልን፣ለቤተሰቦቻቸው መጽናናት እንዲያድልልን የዘወትር ጸሎታችን ነው። በርቱ፣ጠንክሩ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን ብለዋል።
አያይዘውም ቋሚ ሲኖዶስ በአካል ተገኝቶ እናንተን ለማጽናናትና ጊዜያዊ ድጋፍ ለማድረግ በመካከላችሁ ተገኝተናል ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታትና የተቃጠለውን ቤተክርስቲያን ለመሥራት የሚያስቼል አቢይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተክህነት ተሰይሞ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ቅድስት ቤተክርስቲያን በተከሰተው ችግር ጥልቅ ኃዘን የተሰማት መሆኑን ገልጸው ምዕመናን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ፣በፈተና ሁሉ እንዲታገሱ አደራ ካሉ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ኃዘንተኞችን እንዲያጽናና ከዳግም ኃዘን እንዲሰውርልን ዘወትር እንጸልያለን በማለት ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ለተፈናቀሉ ወገኖች የተዘጋጀውን ርዳታ ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ አስረክበዋል።በዚሁ ጊዜ የአቦምሳ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች ብፁዓን አባቶችን እንኳን ደህና መጣችሁልን በማለት በሀገሩ ባህል መሰረት የሰንጋ ስጦታ ካበረከቱ በኋላ የደረሰውን ጉዳት በመኮነን ሕዝቡ በስምምነት፣በአንድነትና በመቻል የኖረና ወደፊትም የሚኖር ሕዝበብ መሆኑን ጠቅሰው የተፈጠረውን ችግር ሃይማኖታዊ መልክ ለማስያዝ የሚደረገው ጥረት ተገቢነት የሌለው ነው ብለዋል።ለብፁዓን አባቶች የተበረከተው የሰንጋ ስጦታም ለተፈናቀሉ ወገኖች እንዲደርስ ተደርጎ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።
© የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የሰሜን ሸዋ ሀገረስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቅዐ ጥበብ አባቡ የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ዓምደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት እያስገነባ የሚገኘውን የመማሪያ ሕንጻ ጎበኙ።
ግንቦት ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም(አቡቀለምሲስ ሚዲያ: ደብረ ብርሃን)
++++++++++++++++++
የሰሜን ሸዋ ሀገረስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቅዐ ጥበብ አባቡ የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ዓምደ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት እያስገነባ የሚገኘውን ባለ 5 ወለል የመማሪያ ሕንጻ ጎብኝተዋል።
ክቡር ሥራ አስኪያጁ በጉብኝታቸው ወቅት ይህ ሕንጻ ትውልድ በእውቀት የሚቀረጽበት፣ የቤተክርስቲያን አገልግሎት ከፍ ብሎ የሚታይበት እንደመሆኑ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሥራ አስፈጻሚዎች ሁሉም የሚመለከታቸው የባለ ድርሻ አካላትን በገንዘብ፣ በእውቀት፣ በጉልበት በሀሳብም እንዲያግዙ የማስተባበር ሥራ ይጠበቅባችኋል በማለት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል።
ግንባታውን በገንዘብ ማገዝ ለምትፈልጉ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000423970182
አቢሲንያ ባንክ 73626803
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ለተማሪዎች የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የምዘና ፈተና ተሰጠ።
ግንቦት ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም(አቡቀለምሲስ ሚዲያ:ደብረ ብርሃን)
++++++++++++++++++++++
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች
አዲሱን የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ባደረጉ በ27 ወረዳ ቤተ ክህነት በሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በ4ኛ የ8ኛና 10ኛ ክፍል ለ2919 ተማሪዎች የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የምዘና ፈተና ተሰጥቷል።
በተመሳሳይ በደብረ ብርሃን ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 1ኛ,2ኛ,3ኛ,5ኛ,6ኛ,7ኛ,9ኛ እና 11ኛ ክፍል ከ3745 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።
የሀገረስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቅዐ ጥበብ አባቡ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ማደራጃ ክፍል ኃላፊ መልአከ ፀሐይ ቀሲስ እስጢፋኖስ ስዕሌ በከተማው በሚገኙ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ተገኝተዋል።
"ሞት ሟችን ብቻ ሳይሆን ገዳይንም መግደሉ ስለማይቀር ገዳዮች ሆይ ከክፉ ሰይጣናዊ ድርጊታችሁ ታቀቡ" ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ!!
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በአርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክውያን ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ አስመልክተው የተሰማቸውን ኀዘን ገለጹ።
ግንቦት ፳፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ሚዲያ ፤ ደብረ ብርሃን)
++++ +++++ +++++ ++++++ +++++ ++++
ብፁዕነታቸው በአርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክውያን ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ አስመልክተው የተሰማቸውን ጥልቅ የኀዘን መልክት አስተላልፈዋል።
የ1 መቶ 1 ዓመት ታሪክ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት መጋየቱ፣ የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን መዘረፍና ምእመናን ጽላቱን ይዘው መሰደዳቸውን ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በሰጡት መግለጫ ሰምተናል።
በጨማሪም ከ2 መቶ 80 በላይ ንጹሐን ወገኖቻችን ተወልደው ካደጉበት ቀያቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ መውደቃቸው የሁላችንም ኦርቶዶክሳውያን ሕመም ነው።
በሀገረ ስብከቱ በተደጋጋሚ በሆነውና እየተፈጸመ ያለው የንጹሐን ግድያ በየጊዜው እየተባባሰ በመምጣቱ በእጅጉ አዝነናል።
"ሞት ሟችን ብቻ ሳይሆን ገዳይንም መግደሉ ስለማይቀር ገዳዮች ከክፉ ሰይጣናዊ ድርጊታችሁ ታቀቡ" ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል።
በሃይማኖታቸው ምክንያት ሰማእትነት ለተቀበሉ ወገኖቻችን ነፍሳቸውን በቅዱሳኑ አጠገብ እንዲያሳርፍልን እየተማጸን ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን ሁሉ ፈጣሪ ብርታቱንና መረጋጋቱን እንዲሰጠልን እንማጸናለን!!
አባ ቀሌምንጦስ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ!!
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም
ደብረ ብርሃን ኢትዮጵያ
"የፊቷ መልክ እንደ ፀሐይ ነው" ቅዱስ ያሬድ
የእመቤታችን ዓመታዊ የመገለጥ በዓል በደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ገዳም በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ተከበረ።
ግንቦት ፳ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም(አቡቀለምሲስ ሚዲያ: ደብረ ብርሃን)
++++++++++++++++++
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ የተገለጠችበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በታሪካዊቷ ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ገዳም በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት አባታዊ ቡራኬ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
