📖 የተቀደደው ማስታወሻ ©ሶፊ
前往频道在 Telegram
🗒️ እንኳን ወደ «የተቀደደው ማስታወሻ» በደህና መጡ! ይህ ቻናል በፈጠራ ታሪኮች እና ልብ-ወለዶች የታጀበ፣ በግጥም ስንኞች የደመቀ፣ እና የዕለት ተዕለት ውሎዎችን እንዲሁም እውነተኛ ስሜቶችን በደብዳቤ እንዲሁም postcard story መልክ የምናጋራበት የግል ማስታወሻችን ነው። ከቃላት በስተጀርባ ራስን ፍለጋ...
显示更多7 297
订阅者
+524 小时
+127 天
+9130 天
帖子存档
7 297
#Dark_humor
ጀለስ ፦ ይኸው ዛሬ ደግሞ ምን ሰማው ፤ ስሟን እንኳን የማላውቀው የስራ ባልደረባዬ ይወደኛል እያለች ታሶራለች አሉ ። ይጠጣል እያሉ እንደሚያሶሩብኝ ታውቃለህ ? አሁን ደግሞ ይዘሙታል ብለው ሊያሶሩብኝ እኮ ነው አለ ። ጓደኛዬ በሰው ወሬ እጅግ ተማሮ ።
ይሄኔ አንዱ ጠላቱ አሶርቶበት ነው።
እኔ ፦ አንተ ስለሰው ወሬ ለምን ትጨነቃለህ ፤ ስለሆንከው እና ስለምትሆነው ተጨነቅ ። አስቱ ምን አለች መሰለህ ስለሰው ስለሰው ቀድጄ ልልበሰው ።
ጀለስ ፦ የቷ አስቴር ? አስቴር ፋይናንሷ ?
እኔ ፦ አቦ አንተ ከቢሮ ውጣ እንጂ አሁን የምሳ ሰዓት ነው።
አደረቀኝ እኮ
©ሶፊ
7 297
የሆስፒታል ግድግዳ ከእምነት ቦታዎች ግድግዳ የበለጠ የጭንቅ ፀሎት ተሰምቶባቸዋል የሚል ፅሁፍ አየሁ ፤ እውነትም የሆነ ጭንቅ ካልገጠመን እኮ አምላክ እንዳለን እራሱ ትዝ አይለንም ።
7 297
Elements የሚል ፀዴ series book ጀምሬያለኹ። Especially የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ትወዱታላችሁ አንብቡት ። ማንበብ እያሳሳኝ በቀን 10 page ነው የማነበው እንዳያልቅብኝ።
በፈጠራችሁ የPdf እንዳትጠይቁኝ።
©ሶፊ
7 297
Real story #101
ዛሬም በስራ ጉዳይ መሸብኝ እና ታክሲ አጥቼ አጎቴ ጋር አሳድረኝ ልለው ደወልኹ...
...ስልኩ ጠራ...
አጎቴ አነሳው (አጎቴ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ነው...) : "ልጅ ሶፎንያስ የጌታ ሰላም ይብዛልህ እንደምን አለህ?" መልሴን አልጠበቀም "ምነው በዚህ ሰዓት ደወልኽ በሰላም ነው?"
እኔ : "አዎ አጎቴ በሰላም ነው መሸብኝና ለእናንተ አካባቢ ቅርብ ስለኾንኹ መጥቼ ለማደር ላስፈቅድህ ነው..."
አጎቴ : "ቤትህ አይደለም ምን ታስፈቅደኛለህ ? በጌታ ሰላም ና ።"
መልሱ ፈገግ እያሰኘኝ ስልኩን ዘጋውት እና ወደቤታቸው ሄድኹ።
ቤታቸው ስደርስ ቤቱን ደመቅመቅ አድርጎት ጠበቀኝ...ደስ አለኝ...አጎቴም ሲያየኝ ደስ አለው "ሸምግለህ የለ እንዴ ልጅ ሶፎንያስ ሃሃሃ በጌታ መንፈስ ተመርተህ እቤቴ መጣህ..."
"ታክሲ አጥቼ ነው አጎቴ " አለኹት ከፈገግታ ጋር ድንገት መምጣቴን ለመንገር..."ቢኾንም ጌታ ካልፈቀደው የሚኾን የለም..." አለኝ ንግግሬን አቋርጦ እንድቀመጥ እየጋበዘኝ...
ቡና ተፈልቶ ቴሌቪዥን መመልኽት እንደጀመርን አስታውሳለሁ...በቴሌቪዥን መስኮት የጦር አውሮፕራኖች እየታዩም ነበር...አጎቴ ወሬውን ትክዝ ብሎ "አለም ላይ ያሉት ኃያላን ሀገራት ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ እናሸንፈዋለን ብለው ነው ጦራቸውን የሚያደራጁት ..." ብሎ እንደዠመረ አስታውሳለሁ...ነገር ግን በየት በኩል መፅሐፍ ቅዱስ ገልጦ ከዘፍጥረት ዠምሮ መተንተን እንደዠመረ አላስታውስም...አኹን የእስራኤላውያን ታሪክ ላይ ደርሰናል...እስከ ነገ ጌታ ከፈቀደ አዲስ ኪዳን እንደርሳለን...አጎቴ ደስ በሚል Energy እያብራራ ነው...እኔ እንቅልፍ እያማለለኝ ነው በዚህ ሰዓት ምንም ቢለኝ እስማማለሁ...ሲነጋ ግን የሐይማኖት አቋሜን አስቀምጬ ነው የምወጣው...
በጌታ ሰላም- ሰላም እደሩ
©ሶፊ
7 297
በticktok ለሚሰዳደቡ ሰዎችን ETFC እዲዋጣላቸው መድረኩን እንደሚያመቻች ይታወቃል ። ታዲያ ምነው እኔና ex-ሴን ችላ አለን ፤ የኢትዮጵያ ህዝብስ ምነው ዝም አለ ።አላለም አንዱ ታክሲ ውስጥ ፤ አስበኸዋል አስገብታ ብትቀጠቅጠው 😁
7 297
ሴዶ ቢያሸንፍ ብዬ እመኛለሁ ፤ በፊት አይመቸኝም ነበር ግን ይሄ ሁሉ struggle የሚያደርገው ያው attention (ማስታወቂያ ለመስራት ፣ የእንጀራ ነገር ሆኖበት ይመስለኛል።) አሳዝኖኛል። Johnny ደግሞ very skilled man ነው as we know ። የሚሆነው አይታወቅም ። good luck for Sedo 😊
7 297
Repost from Thoughts
አስጠኚ ይፈልጋሉ?
እኛ ጋር ብቁ አስጠኚዎች የእናንተን ፍቃድ ብቻ ይጠብቃሉ። ከእናንተ የሚጠበቀው በተጠቀሱት ስልኮች መደወል ብቻ ነው። ከሚፈልጉት አስጠኚ ጋር እናገናኛችኋለን።
☑️Group: https://t.me/grandtutorss
💬Account: @grandtutors1
🗣️ Phone number: 0980806056
7 297
ከፍ ካለ የሞራል ልሕልና ላይ ቁጭ ብለህ ስትታዘበው ፤ አብዛኛው ሰው የውሸት ማንነቱን ለመሸፈን የሚጋጋጥበት መንገድ ያስቅሃል። እንደ ማህበረሰብ ምን አይነት የማንነት ቀውስ ውስጥ ነን ? እንደ አዲስ አበባ መንገዶች ገፅታችንን ብቻ መገንባት ላይ ተጠምደናል ፣ ማሸብረቅ ብቻ ላይ...
የ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ
7 297
ከህይወቴ የማስወጣህ እነዚህን ቀይ መስመር ከረገጥክ ነው ፤ ድንበሬን ፣ ወሰኔን ጥሰሀል ማለት ነው።
1. በምወዳቸው ሰዎች ከመጣህ (የምኖረው ለነእርሱ ነው ፥ እኔ ህይወቴን እሰጣቸዋለሁ እያልኩ እየሳሳሁላቸው ። አንተ ለእነርሱ ክብር መስጠት ከተሳነህ ፤ ሌላ አልጠየኩህም እንደ ሰው ክብር መስጠት ከከበደህ ።)
2. ስወድህ ወንድሜ ነህ ካልኩህ አልጠራጠርህም ፤ አይኔን ጨፍኜ ነው የማምንህ ። ብልጥ ለመሆን ከሞከርክ ፤ የምልህ ካንተ ያነሰ ጭንቅላት የለኝም ፤ አውቄ ደደብ ሁኜ ነው ብዙ ጊዜ የምሞኝልህ ፤ ብቻ የማታለል ድልህን እድታከብር እድሉን አልሰጥህም ። የተታለልኩ መስዬ አታልልሀለሁ ። አለው እያልኩ ከጎንህ ታጣኛለህ ። ስልህ ታገኘኛለህ እኮ የምታውቀኝ እኔን ግን አይደለም የምታገኘው ። ለአንተ ስል ያለመድኩትን አውሬ የሆነውን እኔን ነው።
ከህይወትህ እወጣለሁ ማለት ግን እንድትጎዳ እመኛለሁ አይደለም ወንድም አለም ክፉ ደግ አብረን አሳልፈናልና መልካሙን እመኝልሀለሁ ። ደግሞ እኔ ከጎንህ ብሆንም ባልሆንም ያን ያህል ጠቃሚ አይደለሁም ፤ ለዚህ አይደል የናቀኝ ? ይሁን ። እነዚህን ቀይመስመሮች ሳትረግጥ እኔ ላይ እንደፈለክ ብትሆን አልቀየምህም ማርያምን ።
7 297
ሩቅ ስትመኝ የቅርቡን አትርሳ ። ያለህን ጠበቅ ነው መጀመሪያ ፤ ከሁለት ያጣ እንዳትሆን ወንድምአለም።
የማወራው ስለርቀት አይደለም።
©ሶፊ
