uk
Feedback
📖 የተቀደደው ማስታወሻ ©ሶፊ

📖 የተቀደደው ማስታወሻ ©ሶፊ

Відкрити в Telegram

ወረቀት እና ብዕር የልብ ጓደኞቼ ናቸው። (የ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ ) "I don't write words; i write sentiments." ©ሶፊ

Показати більше
7 052
Підписники
+624 години
+317 днів
+8030 день
Архів дописів
ከእስካይ ላይት የተሰማው ዜና ምንም ቢሆን እኔ ምን አገባኝ ኮኛክ ጠጥቼ ኩናምኛ እያዜምኩ ነው ።

አምባሩን ያጌጠበት ሌላ... (አሌክስ አብርሃም) አንድ ቀን ከመዝሙርና ከግዜር ቃል ውጭ ምንም የማያውቅ ጴንጤ ጓደኛየ ፊቱ ቅጭም ብሎ መጣና እቤቴ አደረ። ሌሊት ድንገት ተነሳና ተንበርክኮ እያለቀሰ መፀለይ ጀመረ። ለምን ጌታ ሆይ ለምን? እያለ! እና በመሃል በቀስታ ሲዘምር ተመሰጨ ሳዳምጠው መዝሙሩ ለየት አለብኝ።ገርሞኝ በደንብ አዳመጥኩት። አሃ ይሄ ነገር .... ጧት ቁርስ ስንበላ ጠየኩት "ይሄ ዘፈን ጌታን ተቀበለ እንዴ?" "የቱ ዘፈን?" የፀጋየ እሸቱ ... ፀጋ እሸቱ ማነው? ፀጋ አላልኩም ፀጋየ ነው...ሌሊት እየፀለይክ "አምባሩን ያጌጠበት ሌላ ተከሳሽ አምሮት ያጣ ገላ" ስትል ነውኮ ያደርከው። "ጌታ ይገስፅህ" አለና ሳቁ አመለጠው። ለካስ ሚስኪን ወዳጀ አንዲት የቸርች እህት "አባለክ" ተብሎ ከቸርች ታግዶ አንጀቱ እርር ብሎ ነው። ብዙ ጴንጤወች እንደሚሉት "ታክሲ ውስጥ የሰማው ዘፈን" አእምሮውን ተቆጣጥሮት ይሆናል። አሳዛኙ ነገር ትክክለኛው አባላጊና ይሄ ሚስኪን ስማቸው ከነአያት ከመገጣጠሙ ውጭ ምንም ግንኙነት አልነበራቸውም። የልጅቱ የተከበሩ ቤተሰቦች ማርገዟን ሲያውቁ አበዱ። ወደክፍለ ሐገር ላኳትና በስልክ ሲያናዝዟት ስሙን ተናገረች። ሽማግሌወች ደውለው ሲጠይቋትም ደገመችው። ሽማግሌወች "አገኘነው" አሉና ሚስኪን ወዳጀ ሻላላላባ እያለ ሲሄድ የምን ሻላላላባ ነው! ባልተገባ.. ባልተቀደሰ... ባልተፈቀደ...ባልተወደደ.. መንገድ ጌታን በድልሃል... የምዕመኑንም አሳዝነሀል፣ ቤተክርስቲያኗ በመተዳደሪያ ደንቧ አንቀፅ ቀ፣ ንኡስ አንቀፅ ጰ መሠረት ለአንድ ዓመት ከማንኛውም አገልግሎት ታግደህ እየፆምክ እየፀለይክ በንስሃ እንድትቆይ ወስናለች።" ነገሩ ተጣርቶ ወዳጀ ላልሰራው ሀጢያት በፆም ከስቶ ሲመለስ፣ ጉባኤው ፊት በስህተት መታገዱ ተገለፀ። ፓስተሩ የተናገረው ነገር ግን ብስጭት አደረገው ። "ሰይጣን የቅዱሳንን ልብ ለማውረድ በሐሰት ይወነጅላል ነፃ የሚያወጣ አምላክ ግን ስራ ላይ ነው ወገኖቸ.....እና ወንድማችን እህታችንን አላባለገም፤ ጌታ ይረዳዋል ወደፊትም አያባልግም"😁

ውሸታም አይደለሁም! እውነቴን ነው ትቼ ነበር ሁሉን ነገር...ፍቅርን ረግሜ ብቸኝነትን አፍቅሬ ነበር...ከዛ እሷ መጣች! ከተቃራኒ ጾታ ጋር ላልቀራረብ ምዬ በተቃራኒ መንገድ እየሄድኩ ነበር...ከዛ
ውሸታም አይደለሁም! እውነቴን ነው ትቼ ነበር ሁሉን ነገር...ፍቅርን ረግሜ ብቸኝነትን አፍቅሬ ነበር...ከዛ እሷ መጣች! ከተቃራኒ ጾታ ጋር ላልቀራረብ ምዬ በተቃራኒ መንገድ እየሄድኩ ነበር...ከዛ እሷ መጣች! ሁሉም እንስቶች ብልጣብልጥነት የሚያጠቃቸው ራሳቸውን ብቻ የሚያስቀድሙ፤ምቾታቸውን የሚከተሉ ፍቅር የማይገባቸው ሞኝ ፍጥረቶች ናቸው ብዬ ደምድሜ ነበር...ከዛ እሷ መጣች! እሷ መጣችና ውሸታም አደረገቺኝ... ሁሉንም እንደ አዲስ ጀመርኩ...መሀላዬን ሻርኩት...ከሷ ጋር አብሬ መሄድ ጀመርኩ...እንስቶች አስተዋይ ፤ የዋህ ፍጥረቶችም ናቸው ብዬ ደመደምኩ። ሐሳቤን ቀየርኩ እንጂ አልዋሸሁም። ውሸታም አይደለሁም! ከተቀደደው ማስታወሻ ©ሶፊ

ሞኝ ነኝ አይደል?! ብዙ ጊዜ ሊደረጉ የማይችሉ ነገሮች ይደረጋሉ፤የማይሆኑ ነገሮች ይሆናሉ ብዬ እጠብቃለሁ። ይሄ የልጅነት ፀባይ መቼ እንደሚለቀኝ አላውቅም...እውነት ቁመቴ ረዘመ፣ሰውነቴ አደገ እንጂ አንዳድ ስራዬ የልጅ ነው። ልጅ እያለኹ የክፍላችን ተማሪዎች በአፍንጫዬ ይቀልዱ እና ያስቁብኝ ነበር፤እኔም ቤት እገባና መስታወት ፊት ቁሜ አፍንጫዬን በእጄ እየተጫንኩ ለማስተካከል ጥረት አደርጋለኹ... ሞኝ ነኝ አይደል? እኮ! ይሄ ሞኝነቴ አሁንም አለቀቀኝም መሰል...ቃል አወጥተሽ ተለያይተናል ካልሺኝ አንድ አመት ከስድስት ወር ከአምስት ቀናት የሆነው ቢሆንም፤ሌላ ህይወት እንደ ጀመርሽ ባረጋግጥም...የእኔ እና የአንቺ ነገር ተስተካክሎ አሁንም ድረስ አንድ ላይ እንሆናለን ብዬ እጠብቃለኹ። ሞኝ ነኝ አይደል?! የ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ ©ሶፊ

የሆነ fancy hotel በስራ ጉዳይ ሄደን ነበር...ሳልፍ ከማየት ውጪ ሆቴሉ እንብዛም ስቦኝ አያውቅም... አንዳንድ ሰዎች ያዳንቁለታል...ማርያምን ምኑም አስደንቆኝ አያውቅም ... የናቁት ጉንዳን ትጥቅ ያስፈታል ነው ያሉት ? 😁 ምሳ ሰዓት ደረሰና ወደ ብፌው ቀረብን... የሀብታም ጥርቅም ሽቶዋቸው አወደኝ ... ደስ የሚል ጠረን ... ውስጤ ዘና ሲል ተሰማኝ ...አዳሜ ሹካ እና ማንኪያውን ደቅኖ ያወራል፤ ሻሞላ ፋይት በለው ከምግብ ጋር ... እርቦኝ ስለነበር አንድ ሁለት ወጥ አይነት አንቼ በፍጥነት ለመቀመጥ በማሰብ ...(የፆም ምግብ ነው ) እንጀራዬን አነጥፌ ልሙጥ ሽሮ ያልኹትን አድርጌ...ወደ ቀጣዮ ወጥ ልሻገር ስል... አሳላፊው እሱ ሾርባ ነው ቆይ ሌላ ሰዓን ላምጣልህ ? አለኝና መልሴን ሳይጠብቅ ተጣድፎ ሄደ። ሽምቅቅ አልኹ ... አለቃዬ እንዳይባንን በወሬ ጠምጄው ሌሎቹን አይነቶች አድርጌ ( ያን ሽሮ መሠል ሾርባ ሸፈንኩት።) ሾርባ በእንጀራ 😭 እና አሁን በመንገድ ላይ ያንን fancy hotel ሳየው ምቾት አይሰማኝም ። ቲሽ ድሮም አይመቸኝም ነበር። ©ሶፊ

ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ ፣ ከግራ ወደቀኝ የሚያማታ ማህበል ... በትንሽ ጀልባ ያንን የሕይወት ሰልፍ የተሻገረ ቀዛፊ ...ዝናቡ ሲያባራ ፣ ወጀቡ ሲረጋጋ ፤ ባሕሩ ሰክኖ ፀጥታ ሲሰፍን ፤ ዝምታ ይረብሸ
ንፋስ የቀላቀለ ዝናብ ፣ ከግራ ወደቀኝ የሚያማታ ማህበል ... በትንሽ ጀልባ ያንን የሕይወት ሰልፍ የተሻገረ ቀዛፊ ...ዝናቡ ሲያባራ ፣ ወጀቡ ሲረጋጋ ፤ ባሕሩ ሰክኖ ፀጥታ ሲሰፍን ፤ ዝምታ ይረብሸው ይጀምራል ። ሁልጊዜም በፍርሃት ይኖራል። የ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ ©ሶፊ

ህይወት እንደ እግር ኳስ ናት...እድል እንደ ኳስ ድቡልቡል (እድል : ጊዜ ነው ፣ እድል ገንዘብ ፣ ጉልበትም ሊሆን ይችላል) ...የሚያስቀው ህይወት ላይ ለቡድን አጋርህ አግባ ፣ ተጫወት ብለህ የሰጠኽውን ኳስ አንተው ላይ ካላገባውት ብለው የሚያስቸግሩ ሰዎች አሉ። የ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ ©ሶፊ

🩵

"I don't fucking trust a single human being anymore." ©ሶፊ
"I don't fucking trust a single human being anymore."
©ሶፊ

ሚስጢረወርቅ
ሚስጢረወርቅ

G.n
G.n

በቁሜ ገለውኝ እርማቸውን ላወጡ ሰዎች እኮ ነው ፤ አሁንም ለመኖር ደፋ ቀና የምለው ። ... ተስካሬን ተካፍለን በላነው...ከመጡበት አላማ ይልቅ የምግቡ ጣዕም፤ያሳሰባቸው ይመስላል። በሞቴ አላዘኑም ፤ ታች አወረዱኝ ፤ ግን አልረኩም (ዳሩ ደግነት እንጂ ክፋት አያረካም።) ... አወረዱኝ ፤ ከዚህ በላይ ዝቅ ማለት ይቻላልን ? የእውነት ስሞት ካላዩ የሚለቁኝ አይመስለኝም ።
 የ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ ©ሶፊ

አበባ ቢነክሷት ማር ነው የምታለቅስ አበባን ቢገርፏት ሽቶ ነው ምታፈስ ለዚህ ነው የምወዳት... ተፈጥሮን አትክድም ፍጥረታት ቢከዷት እኔም ተገርፌ ፤ እኔም ተነክሼ ድርሰት ነው ምላሼ ሰይፈወርቅ 🔥
አበባ ቢነክሷት ማር ነው የምታለቅስ አበባን ቢገርፏት ሽቶ ነው ምታፈስ ለዚህ ነው የምወዳት... ተፈጥሮን አትክድም ፍጥረታት ቢከዷት እኔም ተገርፌ ፤ እኔም ተነክሼ ድርሰት ነው ምላሼ ሰይፈወርቅ 🔥

⚡️
⚡️

ይቅርታ አድርገንላቹሀል ማለት ፤ በእኩይ ተግባራችሁ feel ያደረግነውን ህመም እንረሳዋለን ማለት አይደለም። ቁስሉ ይደርቃል ጠባሳው ግን... ©ሶፊ
ይቅርታ አድርገንላቹሀል ማለት ፤ በእኩይ ተግባራችሁ feel ያደረግነውን ህመም እንረሳዋለን ማለት አይደለም። ቁስሉ ይደርቃል ጠባሳው ግን...
©ሶፊ

ብረት በጥንካሬው ታምቶ አያውቅም ፤ የሚያደክመው እና የሚሰብረው የራሱ ዝገት ነው ። ሰውም እንዲያ ይመስለኛል። ©ሶፊ

Surviving is winning Franklin...