ar
Feedback
Ethiopian Police University Official Page

Ethiopian Police University Official Page

الذهاب إلى القناة على Telegram

Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethiopian Police University Official Page

تُعد قناة Ethiopian Police University Official Page (@epupage) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 17 009 مشتركاً، محتلاً المرتبة 11 938 في فئة التعليم والمرتبة 1 971 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 17 009 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 10 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -99، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -3، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 41.16‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.26‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 7 001 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 765 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 47.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 11 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

17 009
المشتركون
-324 ساعات
-117 أيام
-9930 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለፍርድ ቤት ዳኞች፣ አባገዳዎች፣ ለሀደስንቄዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ሰጠ **, ​ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨ
+9
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለፍርድ ቤት ዳኞች፣ አባገዳዎች፣ ለሀደስንቄዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ሰጠ **, ​ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር ጋር በመተባበር ለፍርድ ቤት ዳኞች፣ ለአባገዳዎች፣ ለሀደስንቄዎች እና ለሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል። የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የማማከርና ማህበረሰብ አገልግሎት መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደስታ ጫላ እንደገለጹት ፣ ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ አጋር ተቋማትና ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለአካባቢው ማህበረሰብ ተከታታይ ስልጠናዎችን ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰዋል። ዛሬ የተሰጠው ስልጠናም የዚሁ ቀጣይ አካል መሆኑን በመጠቆም ፣ ስልጠናው ከበረህ እና ከአሌልቱ ወረዳ ፍርድ ቤቶች ለመጡ ዳኞች፣ እንዲሁም የሰንዳፋ በኬ ከተማ አባገዳዎች፣ ሀደስንቄዎችና የሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ አጠባበቅ ዙሪያ ትኩረት አድርጎ መሰጠቱን አብራርተዋል። በሌላ በኩል የአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አበራ አዴባ በበኩላቸው የሀገርን ሰላምና የዜጎችን ደህንነት በዘላቂነት ለመጠበቅ የሁሉም አካላት የተቀናጀ ርብርብና ቁርጠኝነት የሚያስፈልግበት ወቅት መሆኑን ተናግረው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለጋራና ለትብብር ስራው ላሳየው ዝግጁነትና መልካም ፍላጎት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም የአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር በቀጣይም ከዩኒቨርሲቲው ጋር በሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ስራዎች ላይ በትብብርና በቅንጅት መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክትን ገመገሙ:: ** ግንቦት 28/2018 ዓ/ም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ
+7
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክትን ገመገሙ:: ** ግንቦት 28/2018 ዓ/ም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ እየተገነባ የሚገኘውን የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት የስራ አፈጻጸም ሒደትን ገምግመዋል ። በዚሁ የግምገማ መድረክ ላይ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላት ፣ የህንጻው ተቋራጭ የሆነው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን እና የአማካሪ ድርጅቱ መሀንዲሶችና አመራሮች በተገኙበት በፕሮጀክቱ ወቅታዊ የስራ ሂደት ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። ክቡር የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በውይይቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት "ይህ የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ግንባታ ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካና ለዓለም አቀፍ የፖሊስ አመራሮች ብቁና ተወዳዳሪ የልህቀት ማዕከል እንዲሆን ታስቦ የሚከናወን ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸው ግንባታው በተቀመጠለት አጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ በፍጥነት ወደ ሥራ መግባት ይኖርበታል" በማለት ጥብቅ መመሪያና ማሳሰቢያ ሰጥተዋል። የእቅዱ አስፈጻሚና የህንጻው ተቋራጭ የሆነው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን (ECWC) ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ሮቤል ፀጋዬ በበኩላቸው ፣ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት የተሰጠውን አቅጣጫና ማሳሰቢያ መሰረት በማድረግ፣ ግንባታውን በተቀመጠለት ጊዜና ጥራት አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የዕጩ መኮንኖች ስልጠና ለሚወስዱ የህክምና ዶክተሮች እና የጤና ስፔሻሊስቶች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደረገላቸው ******* ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳ
+7
የዕጩ መኮንኖች ስልጠና ለሚወስዱ የህክምና ዶክተሮች እና የጤና ስፔሻሊስቶች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደረገላቸው ******* ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የዕጩ መኮንኖች ስልጠና ለሚወስዱ የህክምና ዶክተሮች እና የጤና ስፔሻሊስቶች በዛሬው ዕለት የእንኳን ደህና መጣችሁ የአቀባበል ስነ-ስርዓት ተደርጎላቸዋል። በአቀባበል ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮማንደር ዶክተር አቤል ገ/መድን ለሰልጣኞቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ምክትል ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው  ሰልጣኞቹ 80ኛ ዓመቱን ለማክበር በዝግጅት ላይ ወደሚገኘውና በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚና አንጋፋ ወደሆነው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መቀላቀላቸው ለራሳቸውም ሆነ ለተቋሙ ትልቅ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። ወደ ተቋሙ የሚገባ ማንኛውም ሰልጣኝ የተመረጠና የሀገር ፍቅር ያለው መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ ሰልጣኞቹ የሚያገኙት የፖሊስ ፕሮፌሽን በአላቸው ሙያ ላይ ተጨማሪ አቅም የሚሆናቸው እና እንደ ፖሊስ የሀገር ሰላምና ደህንነትን የማስጠበቅ ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት ያለውን ተቋም የማገልገል ብቃታቸውን የሚያሳድግ  ስልጠና ወስደው ድርብ ሀላፊነት የሚጣልባቸው መሆኑን ገልጸዋል። በሌላ በኩል የህክምና ባለሙያዎቹ በዩኒቨርሲቲው በሚቆዩባቸው ጊዜያት ከጤና ሙያቸው በተጨማሪ አቅምንና ቁርጠኝነትን የሚጠይቁ የፖሊስ ሳይንስ ትምህርት፣ የፖሊሳዊ ጨዋነትና ስነ-ምግባር እንዲሁም ተጨማሪ ሙያዊ ስልጠናዎችን እንደሚወስዱ በዩኒቨርሲቲው የፖሊሳዊ ስልቶችና አካል ብቃት ስልጠና ማዕከል መምሪያ ሀላፊ እንዲሁም የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካይ የሆኑት ኮማንደር ዋለልኝ ገስጥ ተናግረዋል።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች ኦሬንቴሽን ተሰጠ ** ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ
+9
7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች ኦሬንቴሽን ተሰጠ ** ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ኦሬንቴሽን ለአመራርና ሰራተኞች ሰጥቷል። ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ የተዘጋጀው ለዩኒቨርሲቲው የፖሊስ አመራሮች፣ አባላት እና ለሲቪል ሰራተኞች ሲሆን፤ በምርጫ ወቅት ሊኖር ስለሚገባው ዝግጁነት እና ሙያዊ ስነ-ምግባር ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል። የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ማብራሪያዎችን በመስጠት እያንዳንዱ የፖሊስ አመራርና አባል የምርጫውን ሂደት ደህንነት ከማስከበር ባሻገር፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ በሆነ መልኩ ህግና ስርዓትን ብቻ ተከትሎ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። በሌላ በኩል የምርጫ ኦሬንቴሽኑን የሰጡት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የትምህረት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮማንደር ዶ/ር አቤል ገ/መድን ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የጸጥታ አካላት የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል። በተመሳሳይ ከዩኒቨርሲቲው ዋናው ካምፓስ ባሻገር በአፖስቶ ፣ በፖሊስ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በአዋሽ 7 የኢትዮጵያ ፖሊስ አካዳሚ ለሚገኙ አመራሮች እና አባላት እንዲሁም ሲቪል ሰራተኞች ምርጫውን አስመልክቶ ኦሬንቴሽን ተሰጥቷቸዋል።

null
null

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች ኦሬንቴሽን ተሰጠ ** ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ
+2
7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች ኦሬንቴሽን ተሰጠ ** ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ኦሬንቴሽን ለአመራርና ሰራተኞች ሰጥቷል። ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ የተዘጋጀው ለዩኒቨርሲቲው የፖሊስ አመራሮች፣ አባላት እና ለሲቪል ሰራተኞች ሲሆን፤ በምርጫ ወቅት ሊኖር ስለሚገባው ዝግጁነት እና ሙያዊ ስነ-ምግባር ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል። የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ማብራሪያዎችን በመስጠት እያንዳንዱ የፖሊስ አመራርና አባል የምርጫውን ሂደት ደህንነት ከማስከበር ባሻገር፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ በሆነት ስሜት ለመደገፍ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ገልጸዋል። በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ አባላትና ሲቪል ሰራተኞች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዲካሄድና በሰላም እንዲጠናቀቅ የተጣለባቸውን ሀገራዊ አደራ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በተመሳሳይ ከዩኒቨርሲቲው ዋናው ካምፓስ ባሻገር በአፖስቶ ፣ በፖሊስ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በአዋሽ 7 የኢትዮጵያ ፖሊስ አካዳሚ ለሚገኙ አመራሮች እና አባላት እንዲሁም ሲቪል ሰራተኞች ምርጫውን አስመልክቶ ኦሬንቴሽን ተሰጥቷቸዋል።

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ:: ** ​ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ ፖሊ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ:: ** ​ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ጋር ተቋማዊ ግንኙነቱን ይበልጥ የሚያጠናክር የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ፊርማ ተፈራረመ። በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ ክቡር የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ እንደገለጹት፤ በዕለቱ የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት በሁለቱ ተቋማት መካከል ለዓመታት የቆየውን መልካም ግንኙነት ወደ ሕጋዊና ስትራቴጂካዊ ግንኙነትን ይበልጥ ወደተቀናጀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል። ​ አክለውም ክቡር ፕሬዝዳንቱ ይህ ስምምነት በወረቀት ላይ የሚሰፍር ፊርማ ብቻ አለመሆኑን ጠቅሰው፣ በአሁኑ ወቅት እንደ ሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር እና የተለያዩ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች በአይነታቸውና በስልታቸው እጅግ ውስብስብ እየሆኑ መምጣታቸውን በማስገንዘብ እነዚህን ውስብስብ ወንጀሎች በአስተማማኝ ሁኔታ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ይቻል ዘንድ፤ በቴክኖሎጂ የዳበረ፣ በዓለም አቀፍ ሕጎች ላይ በቂ ዕውቀት ያለው እና በዘመናዊ የወንጀል ምርመራ ጥበብ የሰለጠነ የፖሊስ ኃይል ማፍራት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) የፕሮግራም ኃላፊ ሳሻ ፓትሪክ ንላቡ በበኩላቸው፤ የዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከልና የሕግ አስከባሪ አካላትን አቅም ለመገንባት ከዩኒቨርሲቲው ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

photo content
+9

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራና በትብብር የመስራት አቅሙን ይበልጥ እያጠናከረ ይገኛል ** ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ
+6
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራና በትብብር የመስራት አቅሙን ይበልጥ እያጠናከረ ይገኛል ** ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት የዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራና በትብብር የመስራት ባህሉን ይበልጥ በማሳደግ፣ ለጸጥታ ኃይሉ መጠናከርና ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ ስኬት ከፍተኛ ድርሻ እየተወጣ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው ተቋማዊ ሪፎርሙንና የልህቀት ማዕከል የመሆን ራዕዩን ለማሳካት ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በስፋት እያጠናከረ የመጣ ሲሆን፣ ይህም በተግባር የሚታዩ ውጤቶችን እያሰገኘ ይገኛል። በዚሁ የትብብርና አጋርነት ተግባር መሰረት ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደህንነት እና ጥበቃ መምሪያ (UNDSS Ethiopia) ለዩኒቨርሲቲ ለትራንስፖርት አገልግሎት የሚውል የተሽከርካሪ ድጋፍ አድርጓል። ዩኒቨርሲቲው ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር የሚፈጥራቸው መሰል ጠንካራ ትስስሮች የሎጂስቲክስና የቴክኖሎጂ አቅምን ለማሳደግ ብቻ ሳይሆን፣ የጸጥታና ደህንነት ዘርፉን በዕውቀትና በክህሎት የበለጸገ ለማድረግ የሚደረገውን ጉዞ የሚያፋጥኑ መሆናቸው ተመላክቷል።

photo content
+1

photo content

ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከኮሪያው አምባሳደር ካንግ ጁንግ ( Kang Jung ) ጋር ውይይት አደረጉ። **** ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖ
+5
ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከኮሪያው አምባሳደር ካንግ ጁንግ ( Kang Jung ) ጋር ውይይት አደረጉ። **** ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አበባ ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከኮሪያው አምባሳደር ካንግ ጁንግ ( Kang Jung ) ጋር ውይይት አደረጉ ። በአዲስ አበባ የኮሪያ ኤምባሲ በተደረገው ውይይት፥ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ስለ ዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ ገለጻ በማድረግ፥ዩኒቨርሲቲው እና የኮሪያ ተቋማት በቴክኖሎጂና ልምድ ልውውጥ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ተወያይተዋል። እንደዚሁም አምባሳደር ካንግ ጁንግ ( Kang Jung ) የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲን ከኮሪያ ተቋማት ጋር ለማስተሳሰር ዝግጁ መሆናቸውን ለፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።