ar
Feedback
Ethiopian Police University Official Page

Ethiopian Police University Official Page

الذهاب إلى القناة على Telegram

Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethiopian Police University Official Page

تُعد قناة Ethiopian Police University Official Page (@epupage) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 17 448 مشتركاً، محتلاً المرتبة 11 504 في فئة التعليم والمرتبة 1 941 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 17 448 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 26 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 358، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 49.29‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.96‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 8 598 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 958 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 51.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 27 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

17 448
المشتركون
+824 ساعات
+2087 أيام
+35830 أيام
أرشيف المشاركات
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ *** ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም | ሰንዳፋ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሰኔ 23 ቀን 2018
+3
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ *** ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም | ሰንዳፋ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠናቀቂያ ፈተና በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ማዕከል በዛሬው ዕለት በሰላምና በስኬት ተጠናቋል። በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት ከመንግሥትና ከግል የትምህርት ተቋማት በዩኒቨርሲቲው የተመደቡ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን በስኬት አጠናቀዋል። የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሀገራችን ካሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ አንዱ የሀገር አቀፍ የፈተና ማዕከል እንደመሆኑ መጠን በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመንም በተፈጥሮና ማህበራዊ ሳይንስ የተመደቡለትን 1,153 ተማሪዎች በመልካም ሥነ-ምግባር እና በተሟላ ዝግጅት አስተናግዶ አስፈትኗል።

“በየደረጃው የሚገኝ አመራር ምሳሌ በመሆን፣ ቅንጅትና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወን ይገባዋል” - ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ *** ​ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም | ኢትዮጵያ ፖሊስ
+9
“በየደረጃው የሚገኝ አመራር ምሳሌ በመሆን፣ ቅንጅትና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወን ይገባዋል” - ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ *** ​ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም | ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ ​በየደረጃው የሚገኝ አመራር ለሠራተኞች ምሳሌ በመሆን፣ ጠንካራ ቅንጅትና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወን እንደሚጠበቅበት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ ገለጹ። ​ክቡር ፕሬዚዳንቱ ይህንን የገለጹት ከምክትል ፕሬዚዳንቶችና ለፕሬዚዳንቱ ተጠሪ ከሆኑ የሥራ ክፍሎች ጋር የ2019 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ባካሄዱበት ወቅት ነው። ​ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በንግግራቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በ2018 በጀት ዓመት እንደ ተቋምም ሆነ እንደ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ትልቅ መነቃቃትን የፈጠሩና ተቋሙን ሊያሻግሩ የሚችሉ በርካታ ስኬታማ ውጤቶችን ማስመዝገቡን አስታውሰዋል። እነዚህን የተመዘገቡ ስኬቶች ይበልጥ በማጠናከርና በቀጣይም በትኩረት በመሥራት፣ ዩኒቨርሲቲውን በአፍሪካ የፖሊስ ትምህርትና ሥልጠና የልዕቀት ማዕከል ለማድረግ በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። ​በተለይም አመራሩ በሥሩ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲውን ሠራተኞች በምሳሌነት ሊመራና የሥራ ተነሳሽነትን ሊፈጥር እንደሚገባ የገለጹት ክቡር ፕሬዚዳንቱ፤ በሠራተኞች መካከል የሚደረገውን የጋራ ቅንጅት ማጠናከር ለውጤታማነት ቁልፍ መሆኑን ጠቁመዋል። ተቋሙ በትምህርትና ሥልጠና፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም በማኅበረሰብ አቀፍ አገልግሎቶች ላይ የተጣለበትን ራዕይና ተልእኮ ከግብ ለማድረስ፣ አመራሩ በሁሉም ረገድ ተናቦና በትብብር መንፈስ ለዕቅዱ መሳካት በጋራ መተጋት እንዳለበት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

photo content
+4

በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ተካሄደ ****** ​ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪ
+5
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ተካሄደ ****** ​ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ያስጀመረውን የ3ኛ ዲግሪ (PhD) መርሃ-ግብር ተማሪዎች የትምህርት ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ያለመ የልምድ ልውውጥና የፓናል ውይይት ተካሄደ። የፓናል ውይይቱ ዋና ዓላማ የፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች የትምህርትና የምርምር ሂደታቸውን በተደራጀ መልኩ እንዲመሩ ለማስቻል ሲሆን ፣ በውይይቱም ላይ በርካታ ገንቢና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች ተነስተዋል። ተማሪዎቹ የይቻላል መንፈስን ሰንቀው፣ በቁርጠኝነት ተግዳሮቶችን እንዴት ማለፍ እንዳለባቸው እንዲሁም ውጤታማ ሊያደርጓቸው የሚችሉ የጥናትና የምርምር ቴክኒኮችን እንዲተገብሩ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ፕሮፌሰሮችና ዶክተሮች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በመጨረሻም ተማሪዎቹ የዚህ ታሪካዊ መርሃ-ግብር የመጀመሪያው ዙር በመሆናቸው ፣ የተሰጠው የተግባር ተሞክሮና ምክረ-ሀሳብ እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት ፣ ለቀጣይ የትምህርትና ምርምር ሂደታቸው ታላቅ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ​

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼዎች ጋር ተወያዩ * ​ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ (ሰንዳፋ) የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳ
+6
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼዎች ጋር ተወያዩ * ​ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ (ሰንዳፋ) የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ በኢትዮጵያ የብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼ ሎሬና ሊማ ናሲሜንቶ እና ምክትል የፖሊስ አታሼ የሆኑት ኢዝራኤል ፔሬራ ቪላግራን በቢሯቸው ተቀብለው የሁለትዮሽ ውይይት አካሔደዋል። በውይይቱ ወቅት ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ የብራዚል ፌደራል ፖሊስ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት እና ጥበቃ በማድረግ ረገድ ያለውን ስኬታማ ተሞክሮ ፣ በተለይም ብራዚል ያስተናገደችውን የኮፕ (COP30) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ልምድ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እንዲያጋሩ ፍላጎታቸውን ገልጸዋል። ይህ ልምድ ኢትዮጵያ በቀጣይ ለምታዘጋጀው የኮፕ (COP32) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እና ለሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከብራዚል ፖሊስ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር በጋራ መስራት በሚችልበት ሁኔታ ላይ ፍላጎታቸውን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼ ሎሬና ሊማ ናሲሜንቶ በበኩላቸው ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው የብራዚል ፌደራል ፖሊስ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና ከዩኒቨርሲቲው ጋር በትምህርትና ስልጠና፣ በአቅም ግንባታ እንዲሁም በጋራ ትብብር ዙሪያ በቅንጅት ለመስራት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።