uz
Feedback
Ethiopian Police University Official Page

Ethiopian Police University Official Page

Kanalga Telegram’da o‘tish

Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Ethiopian Police University Official Page analitikasi

Ethiopian Police University Official Page (@epupage) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 17 448 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 11 504-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 941-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 17 448 obunachiga ega bo‘ldi.

26 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 358 ga, so‘nggi 24 soatda esa 8 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 49.29% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.96% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 8 598 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 958 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 51 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 27 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

17 448
Obunachilar
+824 soatlar
+2087 kunlar
+35830 kunlar
Postlar arxiv
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ *** ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም | ሰንዳፋ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሰኔ 23 ቀን 2018
+3
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ *** ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም | ሰንዳፋ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠናቀቂያ ፈተና በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ማዕከል በዛሬው ዕለት በሰላምና በስኬት ተጠናቋል። በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት ከመንግሥትና ከግል የትምህርት ተቋማት በዩኒቨርሲቲው የተመደቡ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን በስኬት አጠናቀዋል። የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሀገራችን ካሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ አንዱ የሀገር አቀፍ የፈተና ማዕከል እንደመሆኑ መጠን በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመንም በተፈጥሮና ማህበራዊ ሳይንስ የተመደቡለትን 1,153 ተማሪዎች በመልካም ሥነ-ምግባር እና በተሟላ ዝግጅት አስተናግዶ አስፈትኗል።

“በየደረጃው የሚገኝ አመራር ምሳሌ በመሆን፣ ቅንጅትና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወን ይገባዋል” - ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ *** ​ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም | ኢትዮጵያ ፖሊስ
+9
“በየደረጃው የሚገኝ አመራር ምሳሌ በመሆን፣ ቅንጅትና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወን ይገባዋል” - ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ *** ​ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም | ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ ​በየደረጃው የሚገኝ አመራር ለሠራተኞች ምሳሌ በመሆን፣ ጠንካራ ቅንጅትና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወን እንደሚጠበቅበት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ ገለጹ። ​ክቡር ፕሬዚዳንቱ ይህንን የገለጹት ከምክትል ፕሬዚዳንቶችና ለፕሬዚዳንቱ ተጠሪ ከሆኑ የሥራ ክፍሎች ጋር የ2019 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ባካሄዱበት ወቅት ነው። ​ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በንግግራቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በ2018 በጀት ዓመት እንደ ተቋምም ሆነ እንደ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ትልቅ መነቃቃትን የፈጠሩና ተቋሙን ሊያሻግሩ የሚችሉ በርካታ ስኬታማ ውጤቶችን ማስመዝገቡን አስታውሰዋል። እነዚህን የተመዘገቡ ስኬቶች ይበልጥ በማጠናከርና በቀጣይም በትኩረት በመሥራት፣ ዩኒቨርሲቲውን በአፍሪካ የፖሊስ ትምህርትና ሥልጠና የልዕቀት ማዕከል ለማድረግ በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። ​በተለይም አመራሩ በሥሩ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲውን ሠራተኞች በምሳሌነት ሊመራና የሥራ ተነሳሽነትን ሊፈጥር እንደሚገባ የገለጹት ክቡር ፕሬዚዳንቱ፤ በሠራተኞች መካከል የሚደረገውን የጋራ ቅንጅት ማጠናከር ለውጤታማነት ቁልፍ መሆኑን ጠቁመዋል። ተቋሙ በትምህርትና ሥልጠና፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም በማኅበረሰብ አቀፍ አገልግሎቶች ላይ የተጣለበትን ራዕይና ተልእኮ ከግብ ለማድረስ፣ አመራሩ በሁሉም ረገድ ተናቦና በትብብር መንፈስ ለዕቅዱ መሳካት በጋራ መተጋት እንዳለበት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ተካሄደ ****** ​ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪ
+5
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ተካሄደ ****** ​ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ያስጀመረውን የ3ኛ ዲግሪ (PhD) መርሃ-ግብር ተማሪዎች የትምህርት ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ያለመ የልምድ ልውውጥና የፓናል ውይይት ተካሄደ። የፓናል ውይይቱ ዋና ዓላማ የፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች የትምህርትና የምርምር ሂደታቸውን በተደራጀ መልኩ እንዲመሩ ለማስቻል ሲሆን ፣ በውይይቱም ላይ በርካታ ገንቢና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች ተነስተዋል። ተማሪዎቹ የይቻላል መንፈስን ሰንቀው፣ በቁርጠኝነት ተግዳሮቶችን እንዴት ማለፍ እንዳለባቸው እንዲሁም ውጤታማ ሊያደርጓቸው የሚችሉ የጥናትና የምርምር ቴክኒኮችን እንዲተገብሩ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ፕሮፌሰሮችና ዶክተሮች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በመጨረሻም ተማሪዎቹ የዚህ ታሪካዊ መርሃ-ግብር የመጀመሪያው ዙር በመሆናቸው ፣ የተሰጠው የተግባር ተሞክሮና ምክረ-ሀሳብ እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት ፣ ለቀጣይ የትምህርትና ምርምር ሂደታቸው ታላቅ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ​

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼዎች ጋር ተወያዩ * ​ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ (ሰንዳፋ) የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳ
+6
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼዎች ጋር ተወያዩ * ​ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ (ሰንዳፋ) የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ በኢትዮጵያ የብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼ ሎሬና ሊማ ናሲሜንቶ እና ምክትል የፖሊስ አታሼ የሆኑት ኢዝራኤል ፔሬራ ቪላግራን በቢሯቸው ተቀብለው የሁለትዮሽ ውይይት አካሔደዋል። በውይይቱ ወቅት ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ የብራዚል ፌደራል ፖሊስ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት እና ጥበቃ በማድረግ ረገድ ያለውን ስኬታማ ተሞክሮ ፣ በተለይም ብራዚል ያስተናገደችውን የኮፕ (COP30) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ልምድ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እንዲያጋሩ ፍላጎታቸውን ገልጸዋል። ይህ ልምድ ኢትዮጵያ በቀጣይ ለምታዘጋጀው የኮፕ (COP32) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እና ለሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከብራዚል ፖሊስ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር በጋራ መስራት በሚችልበት ሁኔታ ላይ ፍላጎታቸውን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼ ሎሬና ሊማ ናሲሜንቶ በበኩላቸው ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው የብራዚል ፌደራል ፖሊስ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና ከዩኒቨርሲቲው ጋር በትምህርትና ስልጠና፣ በአቅም ግንባታ እንዲሁም በጋራ ትብብር ዙሪያ በቅንጅት ለመስራት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።