Ethiopian Police University Official Page
前往频道在 Telegram
Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice
显示更多📈 Telegram 频道 Ethiopian Police University Official Page 的分析概览
频道 Ethiopian Police University Official Page (@epupage) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 17 009 名订阅者,在 教育 类别中位列第 11 938,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 971 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 17 009 名订阅者。
根据 10 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -99,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.16%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.26% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 7 001 次浏览,首日通常累积 2 765 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 47。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Protect with courage ;Serve with Compassion!
EPU Social Media link
@https://www.facebook.com/ethiopianpolice”
凭借高频更新(最新数据采集于 11 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。
17 009
订阅者
-324 小时
-117 天
-9930 天
帖子存档
+9
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለፍርድ ቤት ዳኞች፣ አባገዳዎች፣ ለሀደስንቄዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ሰጠ
**,
ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር ጋር በመተባበር ለፍርድ ቤት ዳኞች፣ ለአባገዳዎች፣ ለሀደስንቄዎች እና ለሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የማማከርና ማህበረሰብ አገልግሎት መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደስታ ጫላ እንደገለጹት ፣ ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ አጋር ተቋማትና ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለአካባቢው ማህበረሰብ ተከታታይ ስልጠናዎችን ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰዋል። ዛሬ የተሰጠው ስልጠናም የዚሁ ቀጣይ አካል መሆኑን በመጠቆም ፣ ስልጠናው ከበረህ እና ከአሌልቱ ወረዳ ፍርድ ቤቶች ለመጡ ዳኞች፣ እንዲሁም የሰንዳፋ በኬ ከተማ አባገዳዎች፣ ሀደስንቄዎችና የሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ አጠባበቅ ዙሪያ ትኩረት አድርጎ መሰጠቱን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል የአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አበራ አዴባ በበኩላቸው የሀገርን ሰላምና የዜጎችን ደህንነት በዘላቂነት ለመጠበቅ የሁሉም አካላት የተቀናጀ ርብርብና ቁርጠኝነት የሚያስፈልግበት ወቅት መሆኑን ተናግረው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለጋራና ለትብብር ስራው ላሳየው ዝግጁነትና መልካም ፍላጎት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም የአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር በቀጣይም ከዩኒቨርሲቲው ጋር በሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ስራዎች ላይ በትብብርና በቅንጅት መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
+7
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክትን ገመገሙ::
**
ግንቦት 28/2018 ዓ/ም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ እየተገነባ የሚገኘውን የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት የስራ አፈጻጸም ሒደትን ገምግመዋል ።
በዚሁ የግምገማ መድረክ ላይ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላት ፣ የህንጻው ተቋራጭ የሆነው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን እና የአማካሪ ድርጅቱ መሀንዲሶችና አመራሮች በተገኙበት በፕሮጀክቱ ወቅታዊ የስራ ሂደት ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ክቡር የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በውይይቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት "ይህ የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ግንባታ ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካና ለዓለም አቀፍ የፖሊስ አመራሮች ብቁና ተወዳዳሪ የልህቀት ማዕከል እንዲሆን ታስቦ የሚከናወን ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸው ግንባታው በተቀመጠለት አጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ በፍጥነት ወደ ሥራ መግባት ይኖርበታል" በማለት ጥብቅ መመሪያና ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
የእቅዱ አስፈጻሚና የህንጻው ተቋራጭ የሆነው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን (ECWC) ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ሮቤል ፀጋዬ በበኩላቸው ፣ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት የተሰጠውን አቅጣጫና ማሳሰቢያ መሰረት በማድረግ፣ ግንባታውን በተቀመጠለት ጊዜና ጥራት አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
+7
የዕጩ መኮንኖች ስልጠና ለሚወስዱ የህክምና ዶክተሮች እና የጤና ስፔሻሊስቶች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደረገላቸው
*******
ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የዕጩ መኮንኖች ስልጠና ለሚወስዱ የህክምና ዶክተሮች እና የጤና ስፔሻሊስቶች በዛሬው ዕለት የእንኳን ደህና መጣችሁ የአቀባበል ስነ-ስርዓት ተደርጎላቸዋል።
በአቀባበል ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮማንደር ዶክተር አቤል ገ/መድን ለሰልጣኞቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ምክትል ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው ሰልጣኞቹ 80ኛ ዓመቱን ለማክበር በዝግጅት ላይ ወደሚገኘውና በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚና አንጋፋ ወደሆነው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መቀላቀላቸው ለራሳቸውም ሆነ ለተቋሙ ትልቅ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል።
ወደ ተቋሙ የሚገባ ማንኛውም ሰልጣኝ የተመረጠና የሀገር ፍቅር ያለው መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ ሰልጣኞቹ የሚያገኙት የፖሊስ ፕሮፌሽን በአላቸው ሙያ ላይ ተጨማሪ አቅም የሚሆናቸው እና እንደ ፖሊስ የሀገር ሰላምና ደህንነትን የማስጠበቅ ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት ያለውን ተቋም የማገልገል ብቃታቸውን የሚያሳድግ ስልጠና ወስደው ድርብ ሀላፊነት የሚጣልባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል የህክምና ባለሙያዎቹ በዩኒቨርሲቲው በሚቆዩባቸው ጊዜያት ከጤና ሙያቸው በተጨማሪ አቅምንና ቁርጠኝነትን የሚጠይቁ የፖሊስ ሳይንስ ትምህርት፣ የፖሊሳዊ ጨዋነትና ስነ-ምግባር እንዲሁም ተጨማሪ ሙያዊ ስልጠናዎችን እንደሚወስዱ በዩኒቨርሲቲው የፖሊሳዊ ስልቶችና አካል ብቃት ስልጠና ማዕከል መምሪያ ሀላፊ እንዲሁም የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካይ የሆኑት ኮማንደር ዋለልኝ ገስጥ ተናግረዋል።
+9
7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች ኦሬንቴሽን ተሰጠ
**
ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ኦሬንቴሽን ለአመራርና ሰራተኞች ሰጥቷል። ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ የተዘጋጀው ለዩኒቨርሲቲው የፖሊስ አመራሮች፣ አባላት እና ለሲቪል ሰራተኞች ሲሆን፤ በምርጫ ወቅት ሊኖር ስለሚገባው ዝግጁነት እና ሙያዊ ስነ-ምግባር ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ማብራሪያዎችን በመስጠት እያንዳንዱ የፖሊስ አመራርና አባል የምርጫውን ሂደት ደህንነት ከማስከበር ባሻገር፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ በሆነ መልኩ ህግና ስርዓትን ብቻ ተከትሎ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።
በሌላ በኩል የምርጫ ኦሬንቴሽኑን የሰጡት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የትምህረት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮማንደር ዶ/ር አቤል ገ/መድን ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የጸጥታ አካላት የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።
በተመሳሳይ ከዩኒቨርሲቲው ዋናው ካምፓስ ባሻገር በአፖስቶ ፣ በፖሊስ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በአዋሽ 7 የኢትዮጵያ ፖሊስ አካዳሚ ለሚገኙ አመራሮች እና አባላት እንዲሁም ሲቪል ሰራተኞች ምርጫውን አስመልክቶ ኦሬንቴሽን ተሰጥቷቸዋል።
+2
7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች ኦሬንቴሽን ተሰጠ
**
ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ኦሬንቴሽን ለአመራርና ሰራተኞች ሰጥቷል። ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ የተዘጋጀው ለዩኒቨርሲቲው የፖሊስ አመራሮች፣ አባላት እና ለሲቪል ሰራተኞች ሲሆን፤ በምርጫ ወቅት ሊኖር ስለሚገባው ዝግጁነት እና ሙያዊ ስነ-ምግባር ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ማብራሪያዎችን በመስጠት እያንዳንዱ የፖሊስ አመራርና አባል የምርጫውን ሂደት ደህንነት ከማስከበር ባሻገር፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ በሆነት ስሜት ለመደገፍ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ገልጸዋል።
በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ አባላትና ሲቪል ሰራተኞች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዲካሄድና በሰላም እንዲጠናቀቅ የተጣለባቸውን ሀገራዊ አደራ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በተመሳሳይ ከዩኒቨርሲቲው ዋናው ካምፓስ ባሻገር በአፖስቶ ፣ በፖሊስ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በአዋሽ 7 የኢትዮጵያ ፖሊስ አካዳሚ ለሚገኙ አመራሮች እና አባላት እንዲሁም ሲቪል ሰራተኞች ምርጫውን አስመልክቶ ኦሬንቴሽን ተሰጥቷቸዋል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ::
**
ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ጋር ተቋማዊ ግንኙነቱን ይበልጥ የሚያጠናክር የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ፊርማ ተፈራረመ።
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ ክቡር የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ እንደገለጹት፤ በዕለቱ የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት በሁለቱ ተቋማት መካከል ለዓመታት የቆየውን መልካም ግንኙነት ወደ ሕጋዊና ስትራቴጂካዊ ግንኙነትን ይበልጥ ወደተቀናጀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም ክቡር ፕሬዝዳንቱ ይህ ስምምነት በወረቀት ላይ የሚሰፍር ፊርማ ብቻ አለመሆኑን ጠቅሰው፣ በአሁኑ ወቅት እንደ ሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር እና የተለያዩ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች በአይነታቸውና በስልታቸው እጅግ ውስብስብ እየሆኑ መምጣታቸውን በማስገንዘብ እነዚህን ውስብስብ ወንጀሎች በአስተማማኝ ሁኔታ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ይቻል ዘንድ፤ በቴክኖሎጂ የዳበረ፣ በዓለም አቀፍ ሕጎች ላይ በቂ ዕውቀት ያለው እና በዘመናዊ የወንጀል ምርመራ ጥበብ የሰለጠነ የፖሊስ ኃይል ማፍራት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) የፕሮግራም ኃላፊ ሳሻ ፓትሪክ ንላቡ በበኩላቸው፤ የዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከልና የሕግ አስከባሪ አካላትን አቅም ለመገንባት ከዩኒቨርሲቲው ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
+6
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራና በትብብር የመስራት አቅሙን ይበልጥ እያጠናከረ ይገኛል
**
ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት የዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራና በትብብር የመስራት ባህሉን ይበልጥ በማሳደግ፣ ለጸጥታ ኃይሉ መጠናከርና ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ ስኬት ከፍተኛ ድርሻ እየተወጣ ይገኛል።
ዩኒቨርሲቲው ተቋማዊ ሪፎርሙንና የልህቀት ማዕከል የመሆን ራዕዩን ለማሳካት ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በስፋት እያጠናከረ የመጣ ሲሆን፣ ይህም በተግባር የሚታዩ ውጤቶችን እያሰገኘ ይገኛል።
በዚሁ የትብብርና አጋርነት ተግባር መሰረት ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደህንነት እና ጥበቃ መምሪያ (UNDSS Ethiopia) ለዩኒቨርሲቲ ለትራንስፖርት አገልግሎት የሚውል የተሽከርካሪ ድጋፍ አድርጓል።
ዩኒቨርሲቲው ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር የሚፈጥራቸው መሰል ጠንካራ ትስስሮች የሎጂስቲክስና የቴክኖሎጂ አቅምን ለማሳደግ ብቻ ሳይሆን፣ የጸጥታና ደህንነት ዘርፉን በዕውቀትና በክህሎት የበለጸገ ለማድረግ የሚደረገውን ጉዞ የሚያፋጥኑ መሆናቸው ተመላክቷል።
+5
ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከኮሪያው አምባሳደር ካንግ ጁንግ ( Kang Jung ) ጋር ውይይት አደረጉ።
****
ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አበባ
ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከኮሪያው አምባሳደር ካንግ ጁንግ ( Kang Jung ) ጋር ውይይት አደረጉ ። በአዲስ አበባ የኮሪያ ኤምባሲ በተደረገው ውይይት፥ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ስለ ዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ ገለጻ በማድረግ፥ዩኒቨርሲቲው እና የኮሪያ ተቋማት በቴክኖሎጂና ልምድ ልውውጥ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ተወያይተዋል። እንደዚሁም አምባሳደር ካንግ ጁንግ ( Kang Jung ) የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲን ከኮሪያ ተቋማት ጋር ለማስተሳሰር ዝግጁ መሆናቸውን ለፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
