ch
Feedback
Ethiopian Police University Official Page

Ethiopian Police University Official Page

前往频道在 Telegram

Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethiopian Police University Official Page 的分析概览

频道 Ethiopian Police University Official Page (@epupage) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 17 448 名订阅者,在 教育 类别中位列第 11 504,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 941

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 17 448 名订阅者。

根据 26 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 358,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 49.29%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.96% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 8 598 次浏览,首日通常累积 2 958 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 51

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice

凭借高频更新(最新数据采集于 27 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

17 448
订阅者
+824 小时
+2087
+35830
帖子存档
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ *** ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም | ሰንዳፋ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሰኔ 23 ቀን 2018
+3
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በስኬት ተጠናቀቀ *** ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም | ሰንዳፋ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠናቀቂያ ፈተና በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ማዕከል በዛሬው ዕለት በሰላምና በስኬት ተጠናቋል። በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት ከመንግሥትና ከግል የትምህርት ተቋማት በዩኒቨርሲቲው የተመደቡ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን በስኬት አጠናቀዋል። የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሀገራችን ካሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ አንዱ የሀገር አቀፍ የፈተና ማዕከል እንደመሆኑ መጠን በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመንም በተፈጥሮና ማህበራዊ ሳይንስ የተመደቡለትን 1,153 ተማሪዎች በመልካም ሥነ-ምግባር እና በተሟላ ዝግጅት አስተናግዶ አስፈትኗል።

“በየደረጃው የሚገኝ አመራር ምሳሌ በመሆን፣ ቅንጅትና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወን ይገባዋል” - ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ *** ​ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም | ኢትዮጵያ ፖሊስ
+9
“በየደረጃው የሚገኝ አመራር ምሳሌ በመሆን፣ ቅንጅትና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወን ይገባዋል” - ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ *** ​ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም | ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ ​በየደረጃው የሚገኝ አመራር ለሠራተኞች ምሳሌ በመሆን፣ ጠንካራ ቅንጅትና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ ሥራዎችን ማከናወን እንደሚጠበቅበት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ ገለጹ። ​ክቡር ፕሬዚዳንቱ ይህንን የገለጹት ከምክትል ፕሬዚዳንቶችና ለፕሬዚዳንቱ ተጠሪ ከሆኑ የሥራ ክፍሎች ጋር የ2019 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ባካሄዱበት ወቅት ነው። ​ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በንግግራቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በ2018 በጀት ዓመት እንደ ተቋምም ሆነ እንደ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ትልቅ መነቃቃትን የፈጠሩና ተቋሙን ሊያሻግሩ የሚችሉ በርካታ ስኬታማ ውጤቶችን ማስመዝገቡን አስታውሰዋል። እነዚህን የተመዘገቡ ስኬቶች ይበልጥ በማጠናከርና በቀጣይም በትኩረት በመሥራት፣ ዩኒቨርሲቲውን በአፍሪካ የፖሊስ ትምህርትና ሥልጠና የልዕቀት ማዕከል ለማድረግ በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። ​በተለይም አመራሩ በሥሩ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲውን ሠራተኞች በምሳሌነት ሊመራና የሥራ ተነሳሽነትን ሊፈጥር እንደሚገባ የገለጹት ክቡር ፕሬዚዳንቱ፤ በሠራተኞች መካከል የሚደረገውን የጋራ ቅንጅት ማጠናከር ለውጤታማነት ቁልፍ መሆኑን ጠቁመዋል። ተቋሙ በትምህርትና ሥልጠና፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም በማኅበረሰብ አቀፍ አገልግሎቶች ላይ የተጣለበትን ራዕይና ተልእኮ ከግብ ለማድረስ፣ አመራሩ በሁሉም ረገድ ተናቦና በትብብር መንፈስ ለዕቅዱ መሳካት በጋራ መተጋት እንዳለበት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ተካሄደ ****** ​ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪ
+5
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ተካሄደ ****** ​ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ያስጀመረውን የ3ኛ ዲግሪ (PhD) መርሃ-ግብር ተማሪዎች የትምህርት ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ያለመ የልምድ ልውውጥና የፓናል ውይይት ተካሄደ። የፓናል ውይይቱ ዋና ዓላማ የፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች የትምህርትና የምርምር ሂደታቸውን በተደራጀ መልኩ እንዲመሩ ለማስቻል ሲሆን ፣ በውይይቱም ላይ በርካታ ገንቢና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች ተነስተዋል። ተማሪዎቹ የይቻላል መንፈስን ሰንቀው፣ በቁርጠኝነት ተግዳሮቶችን እንዴት ማለፍ እንዳለባቸው እንዲሁም ውጤታማ ሊያደርጓቸው የሚችሉ የጥናትና የምርምር ቴክኒኮችን እንዲተገብሩ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ፕሮፌሰሮችና ዶክተሮች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በመጨረሻም ተማሪዎቹ የዚህ ታሪካዊ መርሃ-ግብር የመጀመሪያው ዙር በመሆናቸው ፣ የተሰጠው የተግባር ተሞክሮና ምክረ-ሀሳብ እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት ፣ ለቀጣይ የትምህርትና ምርምር ሂደታቸው ታላቅ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ ​

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼዎች ጋር ተወያዩ * ​ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ (ሰንዳፋ) የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳ
+6
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼዎች ጋር ተወያዩ * ​ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ (ሰንዳፋ) የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ በኢትዮጵያ የብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼ ሎሬና ሊማ ናሲሜንቶ እና ምክትል የፖሊስ አታሼ የሆኑት ኢዝራኤል ፔሬራ ቪላግራን በቢሯቸው ተቀብለው የሁለትዮሽ ውይይት አካሔደዋል። በውይይቱ ወቅት ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ የብራዚል ፌደራል ፖሊስ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት እና ጥበቃ በማድረግ ረገድ ያለውን ስኬታማ ተሞክሮ ፣ በተለይም ብራዚል ያስተናገደችውን የኮፕ (COP30) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ልምድ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እንዲያጋሩ ፍላጎታቸውን ገልጸዋል። ይህ ልምድ ኢትዮጵያ በቀጣይ ለምታዘጋጀው የኮፕ (COP32) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እና ለሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከብራዚል ፖሊስ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር በጋራ መስራት በሚችልበት ሁኔታ ላይ ፍላጎታቸውን አንስተዋል። በኢትዮጵያ የብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼ ሎሬና ሊማ ናሲሜንቶ በበኩላቸው ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው የብራዚል ፌደራል ፖሊስ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና ከዩኒቨርሲቲው ጋር በትምህርትና ስልጠና፣ በአቅም ግንባታ እንዲሁም በጋራ ትብብር ዙሪያ በቅንጅት ለመስራት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።