Ethiopian Police University Official Page
Protect with courage ;Serve with Compassion! EPU Social Media link @https://www.facebook.com/ethiopianpolice
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethiopian Police University Official Page
تُعد قناة Ethiopian Police University Official Page (@epupage) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 17 176 مشتركاً، محتلاً المرتبة 11 667 في فئة التعليم والمرتبة 1 951 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 17 176 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 05 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 176، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -3، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 49.20%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 17.43% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 8 458 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 997 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 65.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“Protect with courage ;Serve with Compassion!
EPU Social Media link
@https://www.facebook.com/ethiopianpolice”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 06 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 06 يوليو | 0 | |||
| 05 يوليو | 0 | |||
| 04 يوليو | +7 | |||
| 03 يوليو | +30 | |||
| 02 يوليو | +18 | |||
| 01 يوليو | +22 |
| 2 | https://www.facebook.com/100077758515468/posts/1043097804958827/?app=fbl | 3 918 |
| 3 | በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ተካሄደ
******
ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ያስጀመረውን የ3ኛ ዲግሪ (PhD) መርሃ-ግብር ተማሪዎች የትምህርት ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ያለመ የልምድ ልውውጥና የፓናል ውይይት ተካሄደ።
የፓናል ውይይቱ ዋና ዓላማ የፒኤችዲ (PhD) ተማሪዎች የትምህርትና የምርምር ሂደታቸውን በተደራጀ መልኩ እንዲመሩ ለማስቻል ሲሆን ፣ በውይይቱም ላይ በርካታ ገንቢና ስትራቴጂካዊ ሀሳቦች ተነስተዋል። ተማሪዎቹ የይቻላል መንፈስን ሰንቀው፣ በቁርጠኝነት ተግዳሮቶችን እንዴት ማለፍ እንዳለባቸው እንዲሁም ውጤታማ ሊያደርጓቸው የሚችሉ የጥናትና የምርምር ቴክኒኮችን እንዲተገብሩ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ ፕሮፌሰሮችና ዶክተሮች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
በመጨረሻም ተማሪዎቹ የዚህ ታሪካዊ መርሃ-ግብር የመጀመሪያው ዙር በመሆናቸው ፣ የተሰጠው የተግባር ተሞክሮና ምክረ-ሀሳብ እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት ፣ ለቀጣይ የትምህርትና ምርምር ሂደታቸው ታላቅ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
| 7 821 |
| 4 | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼዎች ጋር ተወያዩ
*
ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ (ሰንዳፋ)
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ በኢትዮጵያ የብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼ ሎሬና ሊማ ናሲሜንቶ እና ምክትል የፖሊስ አታሼ የሆኑት ኢዝራኤል ፔሬራ ቪላግራን በቢሯቸው ተቀብለው የሁለትዮሽ ውይይት አካሔደዋል።
በውይይቱ ወቅት ክቡር ዶክተር ታምራት ሙሉጌታ የብራዚል ፌደራል ፖሊስ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን በማዘጋጀት እና ጥበቃ በማድረግ ረገድ ያለውን ስኬታማ ተሞክሮ ፣ በተለይም ብራዚል ያስተናገደችውን የኮፕ (COP30) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ልምድ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እንዲያጋሩ ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።
ይህ ልምድ ኢትዮጵያ በቀጣይ ለምታዘጋጀው የኮፕ (COP32) የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ እና ለሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከብራዚል ፖሊስ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር በጋራ መስራት በሚችልበት ሁኔታ ላይ ፍላጎታቸውን አንስተዋል።
በኢትዮጵያ የብራዚል ኤምባሲ የፖሊስ አታሼ ሎሬና ሊማ ናሲሜንቶ በበኩላቸው ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋናቸውን አቅርበው የብራዚል ፌደራል ፖሊስ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና ከዩኒቨርሲቲው ጋር በትምህርትና ስልጠና፣ በአቅም ግንባታ እንዲሁም በጋራ ትብብር ዙሪያ በቅንጅት ለመስራት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። | 7 601 |
| 5 | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከሃይድሮ ሶሉሽንስ ጋር በመተባበር ለባለሙያዎቹ የዘመናዊ ውሃ ማኔጅመንት ስልጠና ሰጠ
*****
ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከሃይድሮ ሶሉሽንስ (Hydro Solutions) ካምፓኒ ጋር በመተባበር ለዩኒቨርሲቲው ባለሙያዎች የተዘጋጀ የውሃ ማኔጅመንት ስልጠና ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ሰጥቷል። ይህ ስልጠና ተቋሙ በቅርቡ የገዛቸውን ዘመናዊ የውሃ ማሽኖች በመደገፍና የሰው ሃይል አቅምን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ታምኖበታል።
በስልጠናው መክፈቻ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በአሁኑ ወቅት ቴክኖሎጂ በከፍተኛ ፍጥነት እየዘመነ መሆኑን ጠቅሰው ተቋማትም ከዚህ የቴክኖሎጂ ማሻሻልና እድገት ጋር እራሳቸውን ማዋሃድ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም ስልጠናው ሰልጣኞችን ከዘመኑ ጋር የሚያዋህድ መሆኑን ገልጸው "ቴክኖሎጂ እየዘመነ ባለበት በዚህ ወቅት ይህ ስልጠና ባለሙያዎቻችንን ከዘመኑ ጋር የሚያዋህድ በመሆኑ ያገኛችሁትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ የገዛቸውን አዳዲስ ዘመናዊ ማሽኖች በአግባቡ ማኔጅ የማድረግና በተገቢው ሁኔታ የመጠቀም አቅማችሁን ማሳደግ ይኖርባችኋል" ሲሉ ለሰልጣኞች መልዕክት አስተላልፈዋል።
በማጠቃለያውም ከተሳታፊዎች በኩል የተገኘውን እውቀትና ክህሎት በመጠቀም የተቋሙን የውሃ መሰረተ-ልማትና አዳዲስ ማሽነሪዎችን በላቀ ሃላፊነት ለመጠበቅና ስራ ላይ ለማዋል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። | 44 |
| 6 | https://www.facebook.com/100077758515468/posts/pfbid024sfcJtbMdQwvjbRmPkVpqNgTfYEUfjcZ2jhh5bzyx2cwFKonagbonBCTCemZf88jl/ | 11 050 |
| 7 | https://www.facebook.com/share/1Df7NWqqtK/ | 10 930 |
| 8 | ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የንብረት አስተዳዳር አመራሮች እና ባለሞያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነዉ
***
ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ጋር በመተባባር ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለንብረት አስተዳዳር አመራሮች እና ባለሞያዎች በመንግስት ንብረት አስተዳደር ዙሪያ የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነዉ፡፡
በስልጠና ማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተዉ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝደት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሀኑ እንደገለፁት ንብረትን በአግባቡ መያዝ አንዱ የአሰራር መዘመንን አመላካች በመሆኑ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሁሉም ካምፓሶቹ ጭምር ሰፊ ሀብት እያፈራ የሚገኝ ትልቅ ተቋም ሲሆን ይህን ሀብት በአግባቡ ለመያዝ የባለሞያዉ ስልጠና መሰጠቱ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
አያይዘዉም ክቡር ኮሚሽነሩ ይህ ስልጠና የመንግስት ንብረት አጠቃቀምንና አያያዝን ለማጠናከር ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን በማንሳት ስልጠናዉን በአግባቡ መከታተል እንዳለባቸዉ ለሰልጣኞች አፅኖት ሰጠዋል፡፡ | 11 992 |
| 9 | በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የከፍተኛ ትምህርት የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ( Exit Exam) እየተሰጠ ነው
********
ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሰኔ 04 እስከ 12/10/2018 ዓ.ም ለ7ኛ ጊዜ እየተሰጠ የሚገኘው የከፍተኛ ትምህርት የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ( Exit Exam) በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ እየተሰጠ ነው።
በዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ የመንግስትና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ትምህርታቸው የተከታተሉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ሲሆኑ ፈተናው ተማሪዎች በቆይታቸው ያገኙትን የንድፈ ሀሳብ እና የተግባር ክህሎት በመገምገም ፣ ለሀገር እና ለሕዝብ በሚሰጡት አገልግሎት ላይ ሙያዊ ብቃታቸው የተረጋገጠ መሆኑን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና የሚጫዎት ይሆናል።
ዩኒቨርሲቲው ያስተማራቸው ተማሪዎች ጥራቱን የጠበቀ የፖሊስ አመራሮችንና ባለሙያዎችን ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ በመቀጠል፣ የፈተና አሰጣጥ ሂደቱ በታቀደው መሰረት በሰላማዊ መንገድ እየተካሄደ ይገኛል። | 8 664 |
| 10 | በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለሚከፈቱ አዳዲስ የትምህርት መርሀ-ግብሮች ላይ ውይይት ተካሄደ
*****
ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚከፍታቸው አዳዲስ የትምህርት መርሀ-ግብሮች ዙሪያ ከአካዳሚክ አመራሮችና ኮሚቴዎች እንዲሁም መምህራን ጋር ውይይት ተካሔዷል።
በዚሁ መሰረት በ2019 ዓ.ም በሚጀምረው የትምህርት ዘመን በወንጀል መከላከል እና ህዝብ ደህንነት ኮሌጅ ስር "በአቪዬሽን ፖሊስ እና ደህንነት" በመደበኛ ዲፕሎማ ፕሮግራም፣ እንዲሁም በአስተዳደርና ስራ አመራር ኮሌጅ ስር "በፋይናንስና ሎጅስቲክስ ማኔጅመንት" በመጀመሪያ ዲግሪ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች እንደሚከፈቱ በውይይቱ ላይ ተገልጿል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው የትምህርት ምክትል ፕሬዝዳንት ምክትል ኮማንደር ዶክተር አቤል ገ/መድህን እንደገለጹት እነዚህ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች ሊቀረጹ የቻሉት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገ የዳሰሳ ጥናት (Need Assessment) እና ስትራቴጂካዊ ዕቅድ መነሻነት መሆኑን ተናግረዋል።
ምክትል ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ተቋሙ የፖሊስ ሰራዊቱን የመፈጸም አቅም ለማሳደግና ወቅታዊ የጸጥታ ፍላጎቶችን ለማሟላት አዳዲስ የትምህርት መስኮችን ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የተካሄደው ሰፊ ውይይት በዋናነት የተዘጋጁትን ካሪኩለሞች መነሻ ያደረገ ሲሆን፣ የትምህርት ፕሮግራሞቹ የመጨረሻ ውሳኔ ለማግኘት ወደ ዩኒቨርሲቲው ሴኔት አባላት ከመቅረባቸው በፊት መሟላት ስላለባቸው አስፈላጊ ቅድመ-ሁኔታዎች ላይ በዝርዝር ተመክሯል። | 7 598 |
| 11 | https://www.facebook.com/100077758515468/posts/pfbid0vKA7UqRaDRM3rq2mqS467yhTmGxJRQjQhgs5vjpP2EAkBZh5aWtqEZ9yhQ4x1Ffl/ | 6 405 |
| 12 | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ታላላቅ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን ለማስተናገድ ከሚሰራው አብይ ኮሚቴ ጋር ተወያዩ
******,
ሰኔ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ ኢትዮጵያ ለምታዘጋጃቸው ታላላቅ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከተዋቀረው አብይ ኮሚቴ ጋር የሥራ ውይይት አካሄዱ።
ኢትዮጵያ በርካታ ታላላቅና ታሪካዊ ዓለም አቀፍ መድረኮችን በስኬት ለማስተናገድ ሰፊ ዝግጅት እያደረገች የምትገኝ ሲሆን፣ የጸጥታና የደህንነት ሥራዎችን እንዲሁም ተያያዥ ዝግጅቶችን በበላይነት ለመምራትና ለማስተናገድ በፌደራል ፖሊስ በኩል አብይ ኮሚቴ መዋቀሩ ይታወቃል።
ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ ከአብይ ኮሚቴው ጋር ባደረጉት ውይይት ሀገሪቱ የምታስተናግዳቸውን የአፍሪካ ህብረት የፖሊስ ትብብር (AFRIPOL) ጉባኤ ፣ የኢንተርፖል (INTERPOL) የአፍሪካ ቀጣናዊ ጉባኤ ፣ 32ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ (UN General Assembly) ጉባኤዎች በሰላምና በስኬት ለማጠናቀቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡ | 7 495 |
| 13 | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለፍርድ ቤት ዳኞች፣ አባገዳዎች፣ ለሀደስንቄዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ሰጠ
**,
ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር ጋር በመተባበር ለፍርድ ቤት ዳኞች፣ ለአባገዳዎች፣ ለሀደስንቄዎች እና ለሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የማማከርና ማህበረሰብ አገልግሎት መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደስታ ጫላ እንደገለጹት ፣ ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ አጋር ተቋማትና ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለአካባቢው ማህበረሰብ ተከታታይ ስልጠናዎችን ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰዋል። ዛሬ የተሰጠው ስልጠናም የዚሁ ቀጣይ አካል መሆኑን በመጠቆም ፣ ስልጠናው ከበረህ እና ከአሌልቱ ወረዳ ፍርድ ቤቶች ለመጡ ዳኞች፣ እንዲሁም የሰንዳፋ በኬ ከተማ አባገዳዎች፣ ሀደስንቄዎችና የሀገር ሽማግሌዎች በሰላምና ጸጥታ አጠባበቅ ዙሪያ ትኩረት አድርጎ መሰጠቱን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል የአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አበራ አዴባ በበኩላቸው የሀገርን ሰላምና የዜጎችን ደህንነት በዘላቂነት ለመጠበቅ የሁሉም አካላት የተቀናጀ ርብርብና ቁርጠኝነት የሚያስፈልግበት ወቅት መሆኑን ተናግረው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለጋራና ለትብብር ስራው ላሳየው ዝግጁነትና መልካም ፍላጎት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም የአጋር ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር በቀጣይም ከዩኒቨርሲቲው ጋር በሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ስራዎች ላይ በትብብርና በቅንጅት መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። | 7 061 |
| 14 | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክትን ገመገሙ::
**
ግንቦት 28/2018 ዓ/ም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ እየተገነባ የሚገኘውን የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት የስራ አፈጻጸም ሒደትን ገምግመዋል ።
በዚሁ የግምገማ መድረክ ላይ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላት ፣ የህንጻው ተቋራጭ የሆነው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን እና የአማካሪ ድርጅቱ መሀንዲሶችና አመራሮች በተገኙበት በፕሮጀክቱ ወቅታዊ የስራ ሂደት ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ክቡር የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ በውይይቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት "ይህ የዓለም አቀፍ የፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ግንባታ ለሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካና ለዓለም አቀፍ የፖሊስ አመራሮች ብቁና ተወዳዳሪ የልህቀት ማዕከል እንዲሆን ታስቦ የሚከናወን ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸው ግንባታው በተቀመጠለት አጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ በፍጥነት ወደ ሥራ መግባት ይኖርበታል" በማለት ጥብቅ መመሪያና ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
የእቅዱ አስፈጻሚና የህንጻው ተቋራጭ የሆነው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን (ECWC) ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ሮቤል ፀጋዬ በበኩላቸው ፣ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት የተሰጠውን አቅጣጫና ማሳሰቢያ መሰረት በማድረግ፣ ግንባታውን በተቀመጠለት ጊዜና ጥራት አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። | 9 033 |
| 15 | የዕጩ መኮንኖች ስልጠና ለሚወስዱ የህክምና ዶክተሮች እና የጤና ስፔሻሊስቶች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደረገላቸው
*******
ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የዕጩ መኮንኖች ስልጠና ለሚወስዱ የህክምና ዶክተሮች እና የጤና ስፔሻሊስቶች በዛሬው ዕለት የእንኳን ደህና መጣችሁ የአቀባበል ስነ-ስርዓት ተደርጎላቸዋል።
በአቀባበል ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮማንደር ዶክተር አቤል ገ/መድን ለሰልጣኞቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ምክትል ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው ሰልጣኞቹ 80ኛ ዓመቱን ለማክበር በዝግጅት ላይ ወደሚገኘውና በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚና አንጋፋ ወደሆነው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መቀላቀላቸው ለራሳቸውም ሆነ ለተቋሙ ትልቅ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል።
ወደ ተቋሙ የሚገባ ማንኛውም ሰልጣኝ የተመረጠና የሀገር ፍቅር ያለው መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ ሰልጣኞቹ የሚያገኙት የፖሊስ ፕሮፌሽን በአላቸው ሙያ ላይ ተጨማሪ አቅም የሚሆናቸው እና እንደ ፖሊስ የሀገር ሰላምና ደህንነትን የማስጠበቅ ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት ያለውን ተቋም የማገልገል ብቃታቸውን የሚያሳድግ ስልጠና ወስደው ድርብ ሀላፊነት የሚጣልባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል የህክምና ባለሙያዎቹ በዩኒቨርሲቲው በሚቆዩባቸው ጊዜያት ከጤና ሙያቸው በተጨማሪ አቅምንና ቁርጠኝነትን የሚጠይቁ የፖሊስ ሳይንስ ትምህርት፣ የፖሊሳዊ ጨዋነትና ስነ-ምግባር እንዲሁም ተጨማሪ ሙያዊ ስልጠናዎችን እንደሚወስዱ በዩኒቨርሲቲው የፖሊሳዊ ስልቶችና አካል ብቃት ስልጠና ማዕከል መምሪያ ሀላፊ እንዲሁም የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካይ የሆኑት ኮማንደር ዋለልኝ ገስጥ ተናግረዋል። | 10 031 |
| 16 | 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች ኦሬንቴሽን ተሰጠ
**
ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ኦሬንቴሽን ለአመራርና ሰራተኞች ሰጥቷል። ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ የተዘጋጀው ለዩኒቨርሲቲው የፖሊስ አመራሮች፣ አባላት እና ለሲቪል ሰራተኞች ሲሆን፤ በምርጫ ወቅት ሊኖር ስለሚገባው ዝግጁነት እና ሙያዊ ስነ-ምግባር ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ማብራሪያዎችን በመስጠት እያንዳንዱ የፖሊስ አመራርና አባል የምርጫውን ሂደት ደህንነት ከማስከበር ባሻገር፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ በሆነ መልኩ ህግና ስርዓትን ብቻ ተከትሎ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።
በሌላ በኩል የምርጫ ኦሬንቴሽኑን የሰጡት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የትምህረት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮማንደር ዶ/ር አቤል ገ/መድን ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የጸጥታ አካላት የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።
በተመሳሳይ ከዩኒቨርሲቲው ዋናው ካምፓስ ባሻገር በአፖስቶ ፣ በፖሊስ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በአዋሽ 7 የኢትዮጵያ ፖሊስ አካዳሚ ለሚገኙ አመራሮች እና አባላት እንዲሁም ሲቪል ሰራተኞች ምርጫውን አስመልክቶ ኦሬንቴሽን ተሰጥቷቸዋል። | 10 065 |
| 17 | null | 1 |
| 18 | 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞች ኦሬንቴሽን ተሰጠ
**
ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ኦሬንቴሽን ለአመራርና ሰራተኞች ሰጥቷል። ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ የተዘጋጀው ለዩኒቨርሲቲው የፖሊስ አመራሮች፣ አባላት እና ለሲቪል ሰራተኞች ሲሆን፤ በምርጫ ወቅት ሊኖር ስለሚገባው ዝግጁነት እና ሙያዊ ስነ-ምግባር ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ማብራሪያዎችን በመስጠት እያንዳንዱ የፖሊስ አመራርና አባል የምርጫውን ሂደት ደህንነት ከማስከበር ባሻገር፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ በሆነት ስሜት ለመደገፍ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ገልጸዋል።
በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ አባላትና ሲቪል ሰራተኞች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዲካሄድና በሰላም እንዲጠናቀቅ የተጣለባቸውን ሀገራዊ አደራ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በተመሳሳይ ከዩኒቨርሲቲው ዋናው ካምፓስ ባሻገር በአፖስቶ ፣ በፖሊስ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በአዋሽ 7 የኢትዮጵያ ፖሊስ አካዳሚ ለሚገኙ አመራሮች እና አባላት እንዲሁም ሲቪል ሰራተኞች ምርጫውን አስመልክቶ ኦሬንቴሽን ተሰጥቷቸዋል። | 1 |
| 19 | የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ::
**
ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ጋር ተቋማዊ ግንኙነቱን ይበልጥ የሚያጠናክር የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ፊርማ ተፈራረመ።
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ ክቡር የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታ እንደገለጹት፤ በዕለቱ የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት በሁለቱ ተቋማት መካከል ለዓመታት የቆየውን መልካም ግንኙነት ወደ ሕጋዊና ስትራቴጂካዊ ግንኙነትን ይበልጥ ወደተቀናጀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም ክቡር ፕሬዝዳንቱ ይህ ስምምነት በወረቀት ላይ የሚሰፍር ፊርማ ብቻ አለመሆኑን ጠቅሰው፣ በአሁኑ ወቅት እንደ ሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር እና የተለያዩ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች በአይነታቸውና በስልታቸው እጅግ ውስብስብ እየሆኑ መምጣታቸውን በማስገንዘብ እነዚህን ውስብስብ ወንጀሎች በአስተማማኝ ሁኔታ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ይቻል ዘንድ፤ በቴክኖሎጂ የዳበረ፣ በዓለም አቀፍ ሕጎች ላይ በቂ ዕውቀት ያለው እና በዘመናዊ የወንጀል ምርመራ ጥበብ የሰለጠነ የፖሊስ ኃይል ማፍራት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) የፕሮግራም ኃላፊ ሳሻ ፓትሪክ ንላቡ በበኩላቸው፤ የዓለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከልና የሕግ አስከባሪ አካላትን አቅም ለመገንባት ከዩኒቨርሲቲው ጋር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጸዋል። | 8 953 |
| 20 | لا يوجد نص... | 7 863 |
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
