ሪፖርተር ET
🔖 ይህ የሪፖርተር ET የቴሌግራም ገፅ ነው ®️ ☆ በቻናሉ 📌 ፈጣን 📌 ትኩስ 📌 ወቅታዊ እና 📌 ወሳኝ መረጃዎችን እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል ! 🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ሪፖርተር ET
تُعد قناة ሪፖርተር ET (@reportereth) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 19 864 مشتركاً، محتلاً المرتبة 11 568 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 1 699 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 19 864 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 03 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -292، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -3، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 15.66%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً N/A% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 110 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 0 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 19.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“🔖 ይህ የሪፖርተር ET የቴሌግራም ገፅ ነው ®️
☆ በቻናሉ
📌 ፈጣን
📌 ትኩስ
📌 ወቅታዊ እና
📌 ወሳኝ መረጃዎችን እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !
🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 04 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 04 يوليو | +2 | |||
| 03 يوليو | 0 | |||
| 02 يوليو | 0 | |||
| 01 يوليو | +2 |
| 2 | መሬታቸው ለሚኒሻ‼
ከኦሮሚያ የተፈናቀሉ ወገኖች መሬታቸው ለሚሊሻ ሊሰጥ ነው ተባለ‼
ከምስራቅ ወለጋ ኪራሙ ወረዳ ተፈናቅለው በወሎ ጃራ መጠለያ የሚገኙ ዜጎች፣ ወደ ቀደመ ይዞታቸው በአካል ተመልሰው ካልገቡ መሬታቸው ለሚሊሻ፣ ለጸጥታ ኃይሎችና ለሥራ አጥ ወጣቶች እንደሚታደል ማስጠንቀቂያ እንደደረሳቸው ገልፀዋል።
ተፈናቃዮቹ መሬታቸውን ላለማጣት ሲሉ ከመጠለያ ጣቢያ ሆነው የተከማቸና ዓመታዊ ከፍተኛ ግብር እየከፈሉ መሆናቸውን በመጥቀስ፣ ይህ አዲስ መመሪያ ከፍተኛ የስነ-ልቦና ጫና እንደፈጠረባቸውና መንግሥት ጣልቃ ገብቶ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
በጉዳዩ ላይ በአካባቢው አመራሮች መካከል የሃሳብ ክፍፍል መኖሩ የተገለጠ ሲሆን፣ አንዳንዶቹ "ግብር እየከፈሉ በመሆኑ ይዞታቸው ሊነካ አይገባም" ሲሉ፣ የቀሩት ደግሞ "በአካል በቦታው የሌሉ በመሆኑ መሬቱ መተላለፍ አለበት" የሚል አቋም ይዘዋል ሲል የዘገበው አዲስ ማለዳ ከአካባቢው የዞንና የወረዳ ኃላፊዎች ምላሽ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም ብሏል።
#WasuMohammed
video 👇Like + Follow👇
https://www.facebook.com/share/18ZGvgBVhp/?mibextid=wwXIfr
====================
ወቅታዊ እና የታመኑ መረጃዎች እንዲደርሱዎ የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 | 2 770 |
| 3 | ‹‹በ4 አቅጣጫ የከበበንን ጠላት ብቻውን አስቀርተንዋል›› ጀነራል ጆን መዲድ
የሕወሓት ጀነራሎች እና ወታደራዊ መኮንኖች የሚያሰሙት ዛቻ እና ፉክራ ቀጥሏል፡፡ የትግራይ ሕዝብ ለጦርነት ድቤ ድለቃቸው ጆሮውን ቢነፍጋቸውም በግድ በጦር ሜዳ ሊማግዱት በየአደባባዩ የ‹እናሸንፋለን› ፉከራ እያሰሙ ነው፡፡
ከትግራይ ጦር አዛዦች መሀል አንዱ የሆኑት ጀነራል ዩሀንስ ወልደጊዮርጊስ (ጆን መዲድ) በዎይን ሚዲያ በኩል የተለመደ ክስ እና የእናሸንፋለን ፉከራ አሰምቷል፡፡ ጀነራሉ፣ ‹‹በአራት አቅጣጫ የከበበንን ጠላት አሰላለፍ በጣጥሰን፣ ብልጽግናን ብቻውን አስቀርተንዋል›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ትናንት ተባብረው የዘመቱብንን ኃይሎችን በታትንን፣ በቀጠናው አዲስ አሰላለፍ ፈጥረናል የሚሉት የጦር አዛዡ፤ አልተቋጨም ያሉትን ህልውና ለማረጋገጥ እየተዘጋጀን ነው ብለዋል፡፡“ጠላቶቻችን ብዙ ነገር እያሰቡ ነው፤ ብዙ ነገር ደግሞ ይፈርስባቸዋል” ሲሉም አክለዋል፡፡
ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ አዲስ የኃይል አሰላለፍ እንዲፈጠር አድርገናል የሚሉት ጀነራሉ፤ ‹‹በ2013 ከጎረቤት ሀገራት እሰከ ሀገር ውስጥ ኃይሎች አስተባብሮ የዘመተብንን ጠላት ብቻውን አስቀርተን፣ የራሳችን አሰላለፍ ፈጥረናል›› ብለዋል፡፡ “በዚያን ጊዜ ተፈጥሮ የነበረውን እኛን የማጥፋት አሰላለፍ በትነን፣ ከሀገር ውስጥ እና በምስራቅ አፍሪካ አዳዲስ የአሰላለፍ ለውጦች መፍጠር ችለናል›› ነው ያሉት። ጆን መዲድ አዲስ አሰላለፍ ፈጥረናል የሚሉት ጽምዶን ነው፡፡ በትግራይ ሴቶች ገላ ላይ የጦር ወንጀል ከፈጸመው የሻብያ ኃይል ጋር አብረው መሰለፋቸውን እንደ ስኬት መጥቀሳቸው አስተዛዛቢ ሆኗል፡፡
አንዳፍታ ሚዲያ | 2 175 |
| 4 | አቤል ብርሃኑ ከዩኤኢ የ10 ዓመት የጎልደን ቪዛ ተበረከተለት!
ታዋቂው የቪዲዮ ይዘት አዘጋጅ አቤል ብርሃኑ (የወይኗ ልጅ) ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የ10 ዓመት የጎልደን ቪዛ (Golden Visa) ተበርክቶለታል።
በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የረጅም ጊዜ መኖሪያ ፍቃድ ማግኘት፣ በተለይም ደግሞ ሙሉ መብትን የሚያጎናጽፈውን የ10 ዓመት የጎልደን ቪዛ ባለቤት መሆን በአለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ታዋቂ እና ከባድ ከሚባሉ የነዋሪነት እውቅናዎች መካከል አንዱ ነው።
ይህ ታላቅ እድል አብዛኛውን ጊዜ በሀገሪቱ ውስጥ 2 ሚሊዮን ድርሃም ወይም በግምት ከ95 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር በላይ ኢንቨስት ላደረጉ ትልልቅ ባለሀብቶች፣ በከፍተኛ የትምህርት ደረጃቸው እና ማህበራዊ አቅማቸው የወር ገቢያቸው ከ30 ሺህ ድርሃም በላይ ለሆኑ ባለሙያዎች፣ ልዩ ተሰጥኦ ላላቸው ግለሰቦች፣ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እንዲሁም ለሰብአዊ መብት እና ለበጎ አድራጎት ሰራተኞች የሚሰጥ ልዩ ስጦታ ነው።
ይሁን እንጂ ስኬታማውና በብዙ ሚሊዮኖች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈው ኢትዮጵያዊው የዲጂታል ይዘት አዘጋጅ አቤል ብርሃኑ፤ ይህንን ታላቅ ዕድል በማህበራዊ ሚዲያ ባለው ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪነት እና በፈጠራ ስራ አቅራቢነት ዘርፍ ከኤምሬትስ መንግስት ለመቀበል በቅቷል። | 2 645 |
| 5 | “ቤት ያላገኘ ተፈናቃይ ካለ ሥልጣኔን እለቃለሁ” አቶ ግርማ ሰይፉ
የአዲስ አበባ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ በከተማዋ በነበረው የኮሪደር ልማት ምክንያት ተፈናቅሎ ምትክ ቤት ወይም መሬት ያላገኘ አንድም ሕጋዊ ሰው አለመኖሩን አስታወቁ።
ካርታ ወይም የቀበሌ ቤት ኖሮት ምትክ ያጣ ሰው ካለ በገዛ ፈቃዳቸው ከሥልጣን ለመልቀቅ ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው፣ ልማቱ ለሀገር ጥቅም የተሠራ መሆኑን ገልጸው፤ ሆኖም ከአስተዳደራዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በደል የደረሰባቸው ወገኖች መኖራቸውን አልሸሸጉም።
በሌላ በኩል፣ የኮሪደር ልማቱ ለከተማዋ ዘመናዊነትና ውበት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ቢሆንም፤ በሂደቱ ወቅት በቂ ዝግጅት፣ ግልጽነትና ተመጣጣኝ ምትክ አላገኘንም የሚሉ ቅሬታዎች ሲነሱ መቆየታቸው ይታወቃል።
#ዋሱመሐመድ
video 👇Like + Follow👇
https://www.facebook.com/share/18ZGvgBVhp/?mibextid=wwXIfr
====================
ወቅታዊ እና የታመኑ መረጃዎች እንዲደርሱዎ የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 | 3 139 |
| 6 | የእናቱን አስክሬን ቤት አስቀምጦ የእናቱን ቃል ለማክበር የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ከቀብር በፊት እና በኃላ ለፈተና የተቀመጠው ካሊድ
#Ethiopia | ይሕ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ታዳጊ ካሊድ ይባላል ገና የአስራ አራት ዓመት ልጅ ነው።ከሑለት ታናናሽ ወንድሞቹ ጋር በሸገር ከተማ አስተዳደር ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ ከእናቱ ጋር ይኖራል።
ካሊድ ከእናቱ ጋር ሲኖር ወላጅ አባቱ ከእነርሱ ርቆ ሌላ ትዳር መስርቶ ጅጅጋ ከተማ ይኖራል። ካሊድ ሠሞኑን እናቱ ታምወው በነበረበት ወቅት እኔ አንድ ነገር ብሆን ምንም ቢፈጠር አመት የለፋሕበትን ፈተና እንዳታቋርጥ ብለው ቃል ያስገቡታል።
እናትም በነጋታው የስምንተኛ ክፍል ፈተና ሊሲጥ ሠዓታት ሲቀረው ሕይወታቸው ያልፋል።ካሊድ በእናቱ ሞት ከፍተኛ ሐዘን ቢሰማውም ለእናቱ የገባው ቃል አክብሮ የእናቱን አስክሬን እቤት ጥሎ የጥዋት ፈተናውን ተፈተነ።
ካሊድ ከሠዓት እናቱን አልቅሶ ቀብሮ ተመልሶ የከሰዓት ፈተናውን ተፈተነ።የዚሕ የአስራ አራት አመት ታዳጊ የሕይወት ፈተና ብዙዎችን በሐዘን ማስለቀሱን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል።
credit : ዳጉ ጆርናል | 4 271 |
| 7 | ዘመቻው አገረሸ- ቀን ተቆረጠባቸው‼
በደቡብ አፍሪካ የስደተኛ ጠል ቡድኖች ዛቻ በኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቀነ‼
በደቡብ አፍሪካ ጁሃንስበርግና አካባቢው "የውጭ ዜጎች ይውጡልን" ዘመቻ ማገርሸቱን ተከትሎ በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ውጥረት ላይ መሆናቸውን ገለጹ።
አመጸኞቹ እስከ ሰኔ 23 ቀን (June 30) ድረስ አገር ለቀው እንዲወጡ የሰጡት የጊዜ ገደብ እየተቃረበ በመምጣቱና ቡድኖቹ ቤት ለቤት እየዞሩ በማስፈራራታቸው ስጋቱ በርትቷል።
አንዳንድ የአፍሪካ አገራት ዜጎቻቸውን ማስወጣት የጀመሩ ሲሆን፣ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ድርጊቱን ቢያወግዝም ጥቃትና ዝርፊያው አሁንም እየተፈጸመ መሆኑ ተገልጿል።
#ዋሱመሐመድ
video 👇Like + Follow👇
https://www.facebook.com/share/18ZGvgBVhp/?mibextid=wwXIfr
====================
ወቅታዊ እና የታመኑ መረጃዎች እንዲደርሱዎ የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 | 4 307 |
| 8 | የቴዲ አፍሮ የቀድሞው ማናጀር አቶ አዲስ ገሰሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
የጃኖ ባንድ መስራች የነበሩት እና የሙዚቀኛ ገሰሰ ዘለቀ ወንድም የሆኑት ታዋቂው የሙዚቃ ፕሮዲዮሰርና ማኔጀር አቶ አዲስ ገሰሰ በአሜሪካን ሀገር ህይወታቸው ማለፉን የቅርብ ወዳጆቻቸው አስታወቁ።
አቶ አዲስ ዓለም አቀፍ ዝና ያተረፉትን የቦብ ማርሊ ልጆችንእና በርከት ያሉ ታዋቂ ሙዚቀኞችን የማማከርና የማስተዳደር ስራ የሰሩ ጉምቱ የሙዚቃ አስተዳደር ባለሞያ ነበሩ።
አቶ አዲስ የቴዲ አፍሮ ማኔጀር በመሆንም ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል።
በትላንትናው እለት አመሻሹ ላይ በኒው ጀርሲ ግዛት ህይወታቸው ያለፈው አቶ አዲስ ገሰሰ፤ የሞታቸው ምክንያት ለጊዜው ያልታወቀ ሲሆን አስከሬናቸውን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ እንደታሰበ ተነግሯል።
@Addis_News
@Addis_News | 3 927 |
| 9 | የሚሸጥ የቲክቶክ አካውንት ያላችሁ አናግሩን!
👇
@reporter_ethiopianbot | 3 131 |
| 10 | ህውሃት በራያ አላማጣ ‼
የህወሃት ታጣቂዎች ወደ ወሎ አቅጣጫ በእግር እንዲንቀሳቀሱ መታዘዛቸው ተገለጠ‼
የህወሃት ታጣቂዎች በአላማጣ በኩል ወደ ወሎ መስመር በእግር ጉዞ እንዲያደርጉ ትዕዛዝ መተላለፉ ተሰማ። ስለሁኔታው የደረሱኝ መረጃዎች :-
📌 ታጣቂዎቹ ጉዟቸውን ያደረጉት ወደ ወልቃይት መስመር ሳይሆን ወደ ወሎ አካባቢ ሲሆን፣ ይህም ግጭቱን በወሎ መስመር ላይ ለማተኮር የተደረገ እቅድ እንደሆነ ተጠቁሟል።
📌 በተሽከርካሪ መጓዝ የሚያስከትለውን ከፍተኛ አደጋ ለመቀነስና ለጥንቃቄ ሲባል ታጣቂዎቹ በእግር እንዲንቀሳቀሱ ተደርጓል።
📌 በተለይ «አርሚ 15» የተባለው የጦር ክፍል በእግር ጉዞውን እንዲያከናውንና በመቀጠልም ወደ ኤርትራ አቅጣጫ እንዲያቀና መመሪያ እንደተሰጠው ተገልጿል።
📌አሜሪካ ዛሬ በሰሜን ኢትዮጵያ እንዲሁም በመላው ቀጠና ያለውን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ጥለዋል ባሏቸው የህወሓት አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ገደብ መጣሏ ይታወሳል።
#ዋሱመሐመድ
video 👇Like + Follow👇
https://www.facebook.com/share/18ZGvgBVhp/?mibextid=wwXIfr
====================
ወቅታዊ እና የታመኑ መረጃዎች እንዲደርሱዎ የቴሌግራም ቻናሉን join በማድረግ በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 | 3 444 |
| 11 | ጦርነቱን ኢራን አሸንፋለች-ዊኪፔዲያ‼️
ታዋቂው ድረገፅ Wikipedia የኢራን እና የአሜሪካ ጦርነት በኢራን አሸናፊነት መጠናቀቁን በድረገፁ ላይ በይፋ አስቀምጧል። | 3 195 |
| 12 | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰርን በተመለከተ ይህን ብሏል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ያላስተሳሰሩ ደንበኞች የባንክ አገልግሎት ማግኘት አይችሉም። በመሆኑም ባንካችን ያዘጋጀውን የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) በመጠቀም ወይም ወደሚቀርባችሁ የባንካችን ቅርንጫፍ በመሄድ ሂሳባችሁን እንድታስተሳስሩ እንገልፃለን ብሏል።
@seledadotio
@seledadotio | 3 340 |
| 13 | 1447ኛው የዒድ አልአድሃ በዓል ረቡዕ ይውላል።
ዛሬ በሳዑዲ አረቢያ ጨረቃ በመታየቷ የዙል-ሂጃ ወር መግባቱ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (የዓረፋ) በዓል ዕሮብ ረቡዕ ግንቦት 19 ተከብሮ ይውላል።
#Haramain
@tikvahethiopia | 3 693 |
| 14 | የዒድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል የሚውልበትን ቀን ለመወሰን የዙል ሂጃህ ወር ጨረቃ ዛሬ ማታ ትጠበቃለች!
የታላቁን የዒድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል የሚውልበትን ትክክለኛ ቀን ለመወሰን፣ የዙል ሂጃህን ወር መግቢያ ጨረቃ ዛሬ ማታ ይከታተላሉ።
እንደ ዘገባዎች መግለጫ፡
* የጨረቃዋ መታየት ዛሬ ማታ ከተረጋገጠ፣ ታላቁ የዒድ በዓል ረቡዕ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም (May 27, 2026) ይጀምራል።
* ጨረቃዋ ዛሬ ማታ ካልታየች ደግሞ፣ በዓሉ ሐሙስ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም (May 28, 2026) ላይ የሚውል ይሆናል።
በዓሉ የሚውልበት ቀን በይፋ እስኪታወቅ ድረስ፣ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዙል ሂጃህ ወር እና ለታላቁ የዒድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ይህ በዓል የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የደግነት በዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን።
ዒድ ሙባረክ!
Kul 'am wa antum bi-khair! | 3 530 |
| 15 | ዛሬ የእናቶች ቀን እየተከበረ ይገኛል
ለሁሉም እናቶች እንኳን ለእናቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ። ፈጣሪ ለእናቶቻችን ረጅም እድሜ ከ ጤና ጋር ይስጠልን።🙏
🙏ክብር ለነዛ የሰው ፊት እየገረፋቸው በመከራ መሀል ሰው ላደረጉን እናቶች🥰
እስቲ ለእናቶቻችን ❤️
SHARE | @ETHIO_ARSENAL | 5 051 |
| 16 | ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ሊመጡ ነው
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑ ተዘግቧል
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ናይሮቢ የሚካሄደውን "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ ካጠናቀቁ በኋላ፣ በመጪው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለአጭር የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ታውቋል።
ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት በጥንቃቄ የተመረጡ የፈረንሳይ ግዙፍ ኩባንያዎች መሪዎችን በማስከተል ሲሆን፣ ጉብኝቱም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው ይላል የካፒታል ዘገባ።
በፕሬዝዳንቱ የታጀበው ልዑክ እንደ ካርፉር ያሉ ታዋቂ የችርቻሮ ንግድ ተቋማትን እና ሜሪዲያም የተሰኘውን የኢንቨስትመንት ድርጅት አመራሮችን ያካተተ ሲሆን፣ በተለይም ካርፉር ከኢትዮጵያው ሚድሮክ ጋር በፈጠረው የፍራንቻይዝ ስምምነት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ማቀዱ የጉብኝቱ አንዱ ዋነኛ ትኩረት መሆኑ ተጠቁሟል። | 4 871 |
| 17 | በአዲስአበባ የሚገኘዉ የፋኖ ክንፍ ቅሬታ አነሳ
ለተሃድሶ እየተሰጠ ያለው ስልጠና አጥጋቢ አይደለም ሲል “በአማራ ክልል ትጥቅ ትግል” ላይ የነበረው እና አሁን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር እየተወያየ ያለው ‛የፋኖ ክንፍ’ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በበኩሉ በጫካ ካሉ ከታጣቂዎች ጋር እያካሄደ ያለውን ግንኙነትን በተመለከተ አንዳንድ ጉዳዮች በግልጽ አይነገሩም ብሏል።
‛የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት’ ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ሀላፊ እያሱ አባተ እንደገለጹት “ለተሃድሶ በትንሹ ዘጠና ቀናት መስጠት ነበረበት” ያሉ ሲሆን አሁን ላይ ግን እየተሰጠ ያለው ለሰባት ቀናት ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
Via Ankuar Merja | 3 606 |
| 18 | በፌደራል ፖሊስ እና በባለሀብቷ በረከት ወርቁ መካከል ያለው ውጥረት አይሏል!
ባለሀብት በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ) በወንጀል መፈለጓን ተከትሎ ከባድ ውንጀላዎችን የሰነዘረችበት ምላሽ ሰጥታለች።
ባለሀብቷ ከእርሻ ስራዋ ወጥታ ወደ ወርቅ ማዕድን ዘርፍ መግባቷን እንደምትቆጭ ገልጻ፣ ስምንት ሚሊዮን ብር ሀገር አሳጣሽ መባሏን በማጣጣል "እናንተ ራሳችሁ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወስዳችሁብኛል" ስትል ስማቸውን ያልጠቀሰቻቸውን አካላት ወንጅላለች።
በተጨማሪም የተፈቀደላትን ነዳጅ እንዳልወሰደችና ሌሎች አካላት ሸጠው እንደበሉት በመጥቀስ፣ ድርጊቱ እሷን ከመንገድ ለማስወገድ የተጠነሰሰ ሴራ እንደሆነ ገልጻለች።
ባለሀብቷ አብሮት ስሙ የተጠቀሰው አቡሽ አየለ 28 የሚደርሱ የወርቅ ማውጫዎች ያሉትና ለብሔራዊ ባንክ በኩንታል ወርቅ የሚያስገባ መሆኑን በመጥቀስ፣ በወርቅና ነዳጅ ዘርፍ ያሉ ጥቂት ቡድኖች ሌሎች ተወዳዳሪዎች እንዲወገዱ እያደረጉ ነው ስትል ተናግራለች።
"መጨረሻውን አብረን እናያለን" በሚል መልእክት ምላሽዋን የደመደመችው በረከት ወርቁ፣ ከዚህ ድርጊት ጀርባ ያሉ ግለሰቦች እጃቸውን እንዲሰበስቡ አሳስባለች።
በአሁኑ ወቅት ጉዳዩ በፖሊስ የክትትል ሂደት እና በባለሀብቷ የመከላከል ምላሽ መካከል ሆኖ ከፍተኛ ህዝባዊ ትኩረትን ስቧል።#ጉርሻ | 2 906 |
| 19 | ወ/ሮ በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ)ን ጨምሮ 4 ሰዎችን በወንጀል እንደሚፈልጋቸው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።
ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል እንደሚፈልጋቸው ነው ያስታወቀው።
ግለሰቦቹ፥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል ተብለው ክስ ከተመሰረተባቸው 13 ግለሰቦች መካከል ናቸው።
ቴሌግራም ቻናላችንን JOIN በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በትኩሱ ይከታተሉ 👇
■➥ http://T.ME/REPORTERETH
■➥ http://T.ME/REPORTERETH | 3 620 |
| 20 | በዛሬው ዕለት በአለማችን የአህዮች ቀን እየተከበረ ይገኛል !
ለአህያ ጓደያቹ ላኩለት 😁 | 3 409 |
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
