የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 356 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 146 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 357 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 356 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 507، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 14، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 25.68%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 13.08% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 3 681 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 875 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 28.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 24 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 356
المشتركون
+1424 ساعات
+1027 أيام
+50730 أيام
أرشيف المشاركات
+6
በ2016 ዓ.ም የወልቂጤ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተስፋ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሕፃናትን ጨምሮ ከ1-12ኛ ክፍል በተዘረጋው ሥርዓተ ት/ት መሠረት ሲያስተምር ቆይቶ የዓመቱን ማጠቃለያ መርሐ ግብር ሐምሌ 14 2016 ዓ.ም ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንዲሁም የተማሪ ወላጆች በተገኙበት ተከናውኗል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ በሰንበት ት/ቤቱ ከየክፍሉ እና ከአጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
መረጃውን ከተስፋ ሕይወት ሚድያ አግኝተነዋል።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok+6
ብፁዕ አብነ አብርሃም በኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ላይ በመገኘት አባታዊ መምሪያና ቡራኬ አስተላለፉ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 12/11/2016 ዓ.ም
ብፁዕ አብነ አብርሃም በኹለተኛው የአኅጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ላይ በመገኘት አባታዊ መምሪያና ቡራኬ አስተላለፉ። በመልዕክታቸውም <<የሥራ ጊዜ ዛሬ ነው፤ ነፍሳትን የማዳን ሥራ ዛሬ ነው።>> በሚል መነሻ << እስካሁን የመጣንበትን የቃል ትምህርት ይዘን አሁን ደሞ ዘመኑን የሚዋጅ ዘመናዊ የትምህርት መስጫ መንገድ ያስፈልጋል። በተለይ ሕፃናት ልዩ አቀራረብ ይፈልጋሉ በሚመጥናቸው መንገድ ማቅረብ ደግሞ የኛ ድርሻ ነው ለዚህም እናንተ አደራ አለባቹ>> በማለት አባታዊ መልዕክታቸውን ከተለያየ አኅጉረ ስብከት ለመጡ የሰንበት ት/ቤት መምህራን አስተላልፈዋል።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥር በሚገኙ አጥቢያዎች የ፬ [4] ኛ , የ፮ [6] ኛ እና የ፲ [10] ኛ ክፍል ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም የማጠቃለያ ምዘና ሐምሌ 21/2016 ዓ.ም ይሰጣል !!!
#የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
+4
ኹለተኛ ዙር የአኀጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ተጀመረ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) 08/11/2016 ዓ.ም
ኹለተኛ ዙር የአኀጉረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ከ16 ሀገረ ስብከት ለመጡ ከ 200 በላይ ሠልጣኞች መሠጠት ተጀመረ።
ጉባኤው ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ የበላይ ሊቀ ጳጳስ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ሐላፊ ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም ሰብሳቢ በተገኙበት ተጀምሯል።
ብፁዕነታቸው ሥልጠናው እርስ በእርስ የምትተዋወቁበት ልምድ የምትለዋወጡበትና የምትተጋገዙበት ብሎም ለቤተ ክርስቲያን መልካም ፍሬን የምታፈሩበት ይሁን በማለት አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዎል።
ሥልጠናው ለተከታታይ 20 ቀናት በመደበኛ መርሐ ግብር በቀንና በማታ በክህሎት ፤ በእውቀት ፣ በዶግማና አስተዳደር ዘርፍ የሚሰጥ ይሆናል።
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
Repost from የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
#ከሐምሌ_22_እስከ_ሐምሌ_28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም አወጀ።
በሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ በጾም በጸሎት በመወሰን ፣ ምሕላ ይታወጃል። ምሕላ የሚታወጀው ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ሁሉን ማድረግ ወደሚችለው እግዚአብሔር ምልጃን ለማቅረብ ነው።
"ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል " ያለው ቋሚ ሲኖዶስ " በእውነት የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ እግዚአብሔር ፦
✤ መተላለፋችንን ይቅር እንዲለን፣
✤ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣
✤ ለቤተ ክርስቲያናችን ፍቅር አንድነት፣
✤ ለሕዝባችን ደኅንነት እንዲሰጥልን ከአንድነት ገዳማት ኅብረት በቀረበው ጥያቄ መነሻነት ምሕላ ማወጅ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል" ብሏል።
በዚህም በመላ የሀገራችን ክፍልና ሌሎች አህጉራተ ዓለም የሚገኙ መነኰሳትና መነኰሳይያት ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ ለሰባት ተከታታይ ቀናት በቅድስት ቤተ ክርስቲያኗ ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ትውፊት መሠረት የገዳማት ኅብረቱን ጥሪ ተቀብለው የምሕላ ጸሎት እንዲያደርሱ ጥሪ አቅርቧል።
በጤና ችግር ምክንያት ካልሆነ በስተቀርም እስከ ዕርበተ ፀሐይ በመጾም ሱባኤ እንዲይዙ ፣ ቋሚ ሲኖዶስ ከአደራ ጋር አሳስቧል።
ከዚህ በተጨማሪ ሁሉም የቤተክርስቲያን አገልጋዮች እና ምእመናን ሀገራዊ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ፍቅር አንድነትን ለማስፈን ጾምና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የሚያደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርገውት መደበኛው ሥራቸውን በያሉበት ቦታ እየሰሩ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆነው በጾም በጸሎት እንድተጉ ጥሪ ተላልፏል።
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
