የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
تُعد قناة የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 116 مشتركاً، محتلاً المرتبة 6 291 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 2 401 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 116 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 10 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 473، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 10، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 38.95%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً N/A% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 492 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 0 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 28.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 11 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
14 116
المشتركون
+1024 ساعات
+957 أيام
+47330 أيام
أرشيف المشاركات
"የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫
እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በጋራ ጉባኤ በአንድነት ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚመክሩበት፣ የትውልዱን መጻኢ ጉዞ የሚተልሙበት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለነገው ትውልድ ሊያሻግሩ የሚችሉ ዐውደ ሐሳቦች ለውይይት የሚቀርቡበት ታላቅ በዓል ነው። ይህ በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ተሰጥቶት በየዓመቱ እየተከናወነ የሚገኘው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ዘንድሮ በሀገራዊ ጉዳይ ምክንያት በመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ደረጃ ጠቅላላ ጉባኤውን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማከናወን ባይችልም በሁሉም አህጉረ ስብከት፣ በየወረዳው እና በየአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ዕለቱ በደማቅ ሁኔታ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ይውላል።
ቅዱስ ጳውሎስ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ብቻ አይደለም ያለን ይህንንም የመንፈስ አንድነት እንዴት መጠበቅ እንዳለብን በመንገርም ጭምር ነው እንጂ። ይኸውም በፍጹም የዋሕነት፤ ራሳችሁን ዝቅ አድርጋችሁ፣ እየታገሣችሁ፣ ለወንድሞቻችሁም እሺ እያላችሁ፣ በፍቅር እየተጋችሁና እየተባበራችሁ በማለት ነው። የአንድነታችንንም ዓላማ እንዳንዘነጋ ሲገልጽልን “ለአንዱ ተስፋችሁ እንደመጠራታችሁ” ይለናል። እኛም የ15ኛ ዓመት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ቀንን ስናከብር ከወትሮ በላቀ የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ መትጋት እንዲገባን ይህን የቅዱስ ጳውሎስን ምክር መርሐችን አድርገናል። ከሁል ጊዜው በላይ ዓለምም ሆነ ሀገራችን እየተጓዘችበት ካለው አስፈሪ የጥፋት ጉዞ ትውልዱን መጠበቅ፣ ማዳንና ማሰማራት የሚቻለው የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ ስንተጋ ብቻ ነው።
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትውልዱን በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ለመጠብቅ የመንፈስን አንድነት መርሕ ይዞ የሚጓዝ መዋቅር ነው። ታዲያ ይህንን አንድነታችንን ከውስጥም ከውጭም ፈተናዎች ለመጠበቅ እየታየ ያለውን በጎ ፍሬ ለማስቀጠል ትጋትን ገንዘብ ልናደርግ ይገባናል እንላለን። ምን እንኳን በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘንድሮውን ዓለም አቀፋዊ ጠቅላላ ጉባኤያችንን ማከናወን ባንችልም በያለንበት መዋቅር ዕለቱን ልንዘክረው ይገባናል። በመጨረሻም የዘንድሮውን ዓለም ዓቀፍዊ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የሚከናወንበትን ዕለት በቅርቡ የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ እንላለን።
የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
ግንቦት 22/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
+6
የ2018ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት የ12ኛ ክፍል የናሙና ምዘና ተሰጠ።
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ግንቦት 17 2018ዓ.ም
በመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት እየተተገበረ በሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት ተምረው ለሀገር አቀፍ ለሙከራ የናሙና ምዘና የደረሱ ተማሪዎችን ለ4ኛ ጊዜ አስፈተነ።
ለዚህ የናሙና ምዘና የደረሱ በአዲስ አበባና በሸገር ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ አጥቢያዎች ሲሆኑ ምዘናውንም ግንቦት 16 ቀን ወስደዋል። በመቀጠልም በወርሐ ሰኔ መጨረሻ የማጠቃለያ ምዘና እንደሚወስዱ ይጠበቃል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
ለሁሉም የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር:- የሰንበት ትምህርት ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ ሰነድ በዚህ ሊንክ በተያያዘው ሰነድ መሠረት ተልኳል። https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-የሥራ-አመራር-ምርጫ-ማስ/
በውጭ ዓለም ለሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅርና ተባባሪ አካላት የእንግሊዘኛ ትርጉም ተሳትፎ ጥሪ። በየሀገረ ስብከቱ ያሉ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት ለተጀመተው የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት የእንግሊዘኛ ትርጉም ፕሮጀክት ሥራ ግብዓትና ተሳታፊዎችን ለመላክ በሚከተለው ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ።
https://eotc-gssu.org/a/የእንግሊዝኛ-ትርጉም-ሥራ-የተሳትፎ-ጥሪ/
+2
ሥርዓተ ትምህርቱን ለሚያስተገብሩ የአብነት መምህራንና ደቀመዛሙርት ሥልጠና ተሰጠ።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የካቲት 24/2018 ዓ.ም
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው የአሰላ ማኅደረ ስብሐት በዓታ ለማርያምና ቅዱስ ፋኑኤል ወቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ገዳም ለሚገኙ የአብነት መምህራንና ደቀ መዛሙርት ከየካቲት 21-22/2018 ዓ.ም ለኹለት ተከታታይ ቀናት ከመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በተላኩ ልዑካን በመ/ሃ ቀሲስ ይታገሡ ደሴና በመ/ር ሚኪያስ ግዛቸው የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ ልሳነ ግዝ የማስተማር ዘዴ፣ ትምህርተ ሃይማኖትና ብቁ መምህራን እንዴት ማፍራት ይቻላል በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ሥልጠናው ተሰጥቶዋል።
በሥልጠናው የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ክፍል ሓላፊ መ/ምሕረት ወልደ ሰንበት"፣ ክቡር የገዳሙ አስተዳዳሪና የሥልጠናው አዘጋጅ መልአከ ስብሐት ገረመው ሸዋዬ ተገኝተው ሥልጠናውን በማነቃቃት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል። ከሥልጠናው በኋላም የአብነት መምህራኑ በሥርዓተ ትምህርቱ የተካተተውን ልሳነ ግእዝና ትርጓሜ መጻሕፍት ለሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እንደሚያስተምሩ ይጠበቃል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
የመተከል ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጋር በመተባበር በቀን 14/06/2018 ዓ.ም. ለአድባራት አለቆች ለመምህራን እና ለሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ሐላፊዎች ስልጠና ሰጠ።
በእለቱ ከየወረዳ ቤተ ክህነቱ የሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ሐላፊ ከ39 አቢያተ ክርስቲያናት የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ እና መምህራን በተገኙበት ስለ ኢ/ኦ/ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ሁኔታ ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አደረጃጀት እና አወቃቀር እንድሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህት ምንነት እና ትግበራ ዙሪያ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 11:00 ድረስ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተላከው መምህር ያሬድ ዮናስ አማካኝነት ሥልጠናው ከተሰጠ በኋላ በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይትምተደርጓል።
በዕለቱ የመተከል ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መ/ም/ኅሩይ ብሩ እና የሰንበት ክፍል ሐላፊ ቀሲስ ንብረት እጅጉ የውይይት መርሐ ግብር ያደረጉ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይ ጥያቄ እና መልስ ከተደረገበት በኋላ ለሥልጠና መርሐ ግብሩ መሳካት አስተዋፅዖአቸው ለላቀ አካላት እና ለሥልጠናው ተሳታፊዎች የእውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
በመጨረሻም ሠልጣኞች ወደ አጥቢያቸው እንደተመለሱ ሰንበት ትምህርት ቤትን በማጠናከር ሥርዓተ ትምህርቱን እንዲያስቀጥሉ በወረዳ ደረጃ የሰንበት ትምህርት ቤትን በማቋቋም ደረጃ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ አፅዕኖት በመስጠት አባታዊ መመሪያ ሰጥተው የዕለቱ መርሐ ግብር በጸሎት ተጠናቋል።
መረጃው የመተከል ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
#አስተርዕዮ_ማርያም
"ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።" ራዕ 12፡1
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት በዓል (አስተርዕዮ ማርያም) በሰላም አደረሳችሁ!
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
