es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 034 suscriptores, ocupando la posición 5 713 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 253 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 034 suscriptores.

Según los últimos datos del 23 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 700, y en las últimas 24 horas de 15, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 41.38%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 14.08% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 6 220 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 116 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 29.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 24 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 034
Suscriptores
+1524 horas
+1657 días
+70030 días
Archivo de publicaciones
የመጋቤ ሐዲስ ኀይለ እግዚእ አሰፋ በ2018 ዓ.ም የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች የአሠልጣኞች ሥልጠና መክፈቻ መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት መልእክት “ዘጸምአ ይምጻእ ኀቤየ ወይስተይ ወዘሂ የአምን
+1
የመጋቤ ሐዲስ ኀይለ እግዚእ አሰፋ በ2018 ዓ.ም የአህጉረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች የአሠልጣኞች ሥልጠና መክፈቻ መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት መልእክት “ዘጸምአ ይምጻእ ኀቤየ ወይስተይ ወዘሂ የአምን ብየ አፍላገ ማየ ሕይወት ይውሕዝ እምከርሡ” “የተጠማ ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፣ በእኔም የሚያምን መጽሐፍ እንደተናገረ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል” (ዮሐ7፡37) ይኸን ቃል የተናገው መድኅነ ዓለም ክርስቶስ ነው፡፡ ቃሉም የተነገራቸው በሥልጠና ላይ ለነበሩ ደቀ መዛሙርት ነው፡፡ ቃሉን ጠጥተው ጽምዐ ነፍሳቸውን እንዲያርቁ፣ ከዓለማዊ ግብር እንዲላቀቁ፣ በሃይማኖትና በምግባር እንዲልቁ ፣ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን አንዲለብሱ፣ ከብሌት እንዲታደሱ፣ በአእምሮ እንዲጎለብሱ ስለጠራቸው “የተጠማ ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ” በማለት የሰውን ልጆች ሁሉ ወደ እርሱ ጠርቷቸዋል፡፡ በመተርጒማን ዘይቤ ደረቅ ሐዲስ በሚል የትንቢት መጽሐፉ የሚታወቀው ነገረ ክርስቶስን በተመለከተ በምልአትና በስፋት የጻፈው ልዑለ ቃል ኢሳይስም “እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ ወደ ውኃ ሂዱ” ሲል ትንቢታዊ ምክሩን ለግሶአል፡፡ ( ትን .ኢሳ 55፡1) .... https://eotc-gssu.org/a/የመጋቤ-ሐዲስ-ኀይለ-እግዚእ-አሰፋ-በ2018-ዓ-ም/

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት የውስጥ ዝርዝ
+7
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት የውስጥ ዝርዝር ማስፈጸሚያ ሰነድ በ2016 ዓ.ም በተዘጋጀው እና በ2018 ዓ.ም የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ ሰነድ መሠረት ሁሉም ሀገረ ስብከቶች ወደ ተግባራዊ ሥራ በመግባት ላይ መሆናቸው ይታወቃል። በመዋቅራዊ አሠራሩም በተገለጸው መሠረት አጥቢያ ሰንበት ት/ቤት፣ ክፍለ ከተማ፣ መንበረ ጵጵስና እና መንበረ ፓትርያርክ ደረጃ በደረጃ ወጥ በሆነ አሠራርና ጊዜ እንዲፈጸም ትግበራ ላይ ይገኛል። በዚህም መሠረት የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማከናወናቸውን ተከትሎ በአዲሱ አደረጃጀት የተመረጡ ከ2300በ ላይ የሰንበት ት/ቤት ሥራ  አመራሮች  እና የአፈጻጸም ቁጥጥር እና ክትትል ጉባኤ አባላትን  ሐምሌ 11 ፣12 እና 25 /2018 ዓ.ም በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቅቆ  ሥልጠናው ዛሬ ሐምሌ 11/12/18/25 /2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:30 አስከ 11:30  በአስራ ኹለት የስልጠና ጣቢያዎች መስጠት ጀምሯል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት 4ኛው የአህጉረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ በዛሬው ዕለት ተጀመረ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም በዛሬው የመክፈቻ መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ አገልግሎት መምርያ ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ ፣ ሊቀ ጉባኤ መሐሪ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ምክትል ሐላፊ ፣ ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥራ አመራር አባላት እና የመምሪያው ልዩ ልዩ ሠራተኞች በተገኙበት በጸሎተ ወንጌል ተጀምሯል። ብፁዕ አቡነ ማርቆስ በመዝሙር 125(126):5 ላይ "በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ያጭዳሉ።" የሚለውን የዳዊት መዝሙር መነሻ አድርገው ገበሬ በልቅሶ በመከራ በክረምት ዘርን እንደሚዘራ በገበሬ አምሳል መምህራንም ዘር የተባለ ቅዱስ ወንጌልን በልቅሶ በመከራ ለማስተማር  መዘጋጀት ይገባችዋል በማለት ለሰልጣኝ መምህራኑ አባታዊ ቡራኬና መልእክት አስተላልፈዋል። "የተጠማ ቢኖር ወደኔ ይምጣና ይጠጣ በእኔ የሚያምን ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚል የሕይወት ውኃ ምንጭ ከሆዱ ይፈልቃል።" ዮሐ 7:38 በሚል ቃል መነሻ አድርገው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በመቀጠልም በዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው አጠቃላይ የሥልጠናውን ይዘትና አካሄድ ላይ ገለጻ አድርገዋል። ሥልጠናው በ3 መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን እነርሱም መሠረተ እምነት ዶግማ እና የሥርዓተ አምልኮ ጉዳዮች ፣ ሥርዓተ ትምህርትን የሚመለከቱ ሥልጠናዎች እንዲሁም ተግባራዊ ሥራና የሕይወት ክህሎት ናቸው። በሥልጠናውም ላይ ከ37 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ ከ315 በላይ ሠልጣኞች ይሳተፋሉ። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

እንኳን ደስ አላችሁ!!! በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አድነት ከዚህ በፊት ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በአማርኛ እንዲሁም ከ
እንኳን ደስ አላችሁ!!! በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አድነት ከዚህ በፊት ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በአማርኛ እንዲሁም ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል በኦሮምኛ የመማርያ መጻሕፍትን በማዘጋጀት የግዥ ጥቅል (Package) ተዘጋጅቶላችሁ እየወሰዳችሁ እንደሆነ ይታወቃል። አሁን ደግሞ የቅድመ ሕጻናት ሀ እና ለ 2 ጥራዝ መጻሕፍት እና ከ8ኛ እስከ 10ኛ ክፍል 3 ጥራዝ መጻሕፍት ህትመት መድረሱን እያበሰርን ከ2019 ዓ.ም የትምህርት ዓመት አስቀድሞ መጻሕፍቱን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ገዝታችሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

#ታላቅ_የምሥራች የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 2ኛ ዙር የበይነመረብ (ኦንላይን) የነገረ መለኮት ትምህርት ምዝገባ እያካሄደ ይገኛል። እርስዎም የዚህ መልካም እድል ተጠቃሚ ይሆኑ ዘ
#ታላቅ_የምሥራች የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ 2ኛ ዙር የበይነመረብ (ኦንላይን) የነገረ መለኮት ትምህርት ምዝገባ እያካሄደ ይገኛል። እርስዎም የዚህ መልካም እድል ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ እየጋበዝንዎት መላው ኦርቶዶክሰዊ ተሳታፊ እንዲሆን ይህን መልእክት በማጋራት ክርስቲያናዊ  ኃላፊነትዎን እንዲወጡ በማለት ከታች የምዝገባ ማመልከቻ ቅጽ እና የኦንላይን ትምህርት ማስተባበሪያው የቴሌግራም ገጽ ማስፈንጠሪያ (#Link) አስቀምጠንልዎታል:: የምዝገባ የማመልከቻውን ቅጽ ለመሙላት 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://forms.gle/bHGroCYF5a3MDxV19 ለተጨማሪ መረጃ እና ማስታወቂያዎችን ለመከታተል የቴሌ ግራም ገጹን ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/Sewasiwe_Birhan_Kidus_Pawlos
ይህ መልእክት ለኦርቶዶክሳውያን ሁሉ እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግ ክርስቲያናዊ ኃላፊነትዎን ይወጡ።

በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነተ  በሀገረ ስብከቱ ሥር ለሚገኙ  በአዲሱ ሥርዓተ  ትምህርት መሠረት የ4ተኛ እና የ8ተኛ ክፍል  የሚኒስትሪ ፈተና ተሰጠ።   የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ምዘናው በጭሮ  በአራቱ አድባራት  ተማሪዎች  የፈተናውን አሰጣጥ ሊቀ ኅሩያን ቆሞስ አባ ፍቅረ ዮሐንስ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ   ከማደራጃው ኃላፊ  መጋቤ ሥርዓት ዘነበ ብርሐኑ  እንዲሁም የአንድነቱ ተቀዳሚ ሰብሳቢ  መ/ር መኮንን አብዩ  ሌሎቹችም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አማራር በመገኘት  የሀገረ ስብከቱ ስራ  አስኪያጅ ቡራኬና ጸሎት ሰጥተው  ፈተናውን አስጀምረዋል።  ፈተናውም በሀገረ ስብከቱ አዳራሽ   እንዲሁም  በአቡነ ጎርጎሪዎስ ትምህርት ቤት ተሰጥቷል። በተጨማሪም በወረዳ  ላሉት የሰንበት ትምህርት  ቤት ተፈተኞች   1. በጡሎ  ዶባ ወረዳ  በሂርና  ሁለቱ አድባራት ና በዶባ  ቅ/ሚካኤል  ቤተክርስቲያን 2.በቦኬ ኦዳ ቡልቱም ወረዳ  በበዴሳ  ሁለቱ አድባራት ና በመካኒሳ ቅ/ገብርኤል  ቤተክርስቲያን  3. በዳሮ ለቡ ወረዳ  መቻራ መድኃኔዓለም    ቤተክርስቲያን 4. በሀብሮ ወረዳ   ገለምሶ ሁለቱ አድባራት እና  በልበሊቲ ቅ/ጊዮርጊስ   ቤተክርስቲያን   5. በገመቺስ ወረዳ  በቁኒ ሁለቱም አድባራት ፈተናው መስጠት ተችሏል።  ይህ የስርዓተ ትምህርት የምዘና ስራ አምና በአንድ ወረዳ ብቻ ተሰጥቶ ቢሆንም  ዘንድሮ በ5 ወረዳ እና  ከ16 ለሚበልጡ ሰንበት ትምህርት ቤቶች  ፈተናው ተዘጋጅቶ መበተን ተችሏል። በርዕሰ ከተማው ለሚገኙ ተፈታኞችም የሀገረ ስብከቱ    ሊቀ ጳጳስ  አቡነ እንጦንስ  በፈተናው ማብቂያ ላይ በመገኘት ልጆቻቸውን ሲያበረቱ ምክር ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬን በመስጠ በጸሎት ማጠቃለያ ማድረግ ተችሏል። የሰንበት ትምህርት ቤቱ ማደራጃ እና የሰንበት ትምህርት  ቤቶች አንድነት በሚቀጥለው የትምህርት  ዘመን  በ9 ወረዳዎች  ተዳራሽ ለማድረግ ስራዎችን ከወዲሁ እየሰራ ይገኛል። የረዳን እግዚአብሔር  ይመስገን። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት የ2018 ዓ.ም ሀገረ ስብከት አቀፍ የ4ኛ ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል የሞዴል ፈተናዎች ሰጠ፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ስር የሚገኙ ሰንበት
+3
በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት የ2018 ዓ.ም ሀገረ ስብከት አቀፍ የ4ኛ ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል የሞዴል ፈተናዎች ሰጠ፡፡   በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ስር የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የ2018 ዓ.ም ሀገረ ስብከት አቀፍ  የሞዴል ተሰጠ። በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ 6 ወረዳ ቤተ ክህነት  መንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ አዳማ ፣ቢሾፍቱና አካባቢው፤ ሉሜ ፣አዳሚ ቱሉ፤ዱግዳ ፣እና በቦሰት ወርዳ ቤተ ክህነት በስሮቻቸው ባሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን ሲከታተሉ ለቆዩት 3000 ተማሪዎች የ2018 ዓ.ም ሞዴል  ፈተና በቀን 07/09/2018 ዓ.ም  ተሰጥቷል፡፡  የሞዴል ፈተናው  ስድስት የትምህርት አይነቶችን   ለየብቻቸው ተዘጋጅቶ  ተሰጥቷል። የተሰጠው ፈተና  መሠረተ ሃይማኖት፤ ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባር ፤ልሳነ ግዕዝ ፤የቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት፤ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እና ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ለእያንዳንዱ ትምህርቶችን 50 ጥያቄዎችን ያከተተ ሲሆን  በሀገረ ስብከቱ አንድነት የሚዘጋጀው የ4ተኛ 8ተኛ እና 10ኛ ክፍል ሀገረ ስብከት አእቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና በወጣይ ወር  በሁሉም ወረዳዎች ባሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ይሰጣል። መረጃው የምሥራቅ ሸዋ ሀገረስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

"የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በጋራ ጉባኤ በአንድነት ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚመክሩበት፣ የትውልዱን መጻኢ ጉዞ የሚተልሙበት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለነገው ትውልድ ሊያሻግሩ የሚችሉ ዐውደ ሐሳቦች ለውይይት የሚቀርቡበት ታላቅ በዓል ነው። ይህ በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ተሰጥቶት በየዓመቱ እየተከናወነ የሚገኘው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ዘንድሮ በሀገራዊ ጉዳይ ምክንያት በመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ደረጃ ጠቅላላ ጉባኤውን በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማከናወን ባይችልም በሁሉም አህጉረ ስብከት፣ በየወረዳው እና በየአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ዕለቱ በደማቅ ሁኔታ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ይውላል። ቅዱስ ጳውሎስ "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ብቻ አይደለም ያለን ይህንንም የመንፈስ አንድነት እንዴት መጠበቅ እንዳለብን በመንገርም ጭምር ነው እንጂ። ይኸውም በፍጹም የዋሕነት፤ ራሳችሁን ዝቅ አድርጋችሁ፣ እየታገሣችሁ፣ ለወንድሞቻችሁም እሺ እያላችሁ፣ በፍቅር እየተጋችሁና እየተባበራችሁ በማለት ነው። የአንድነታችንንም ዓላማ እንዳንዘነጋ ሲገልጽልን “ለአንዱ ተስፋችሁ እንደመጠራታችሁ” ይለናል። እኛም የ15ኛ ዓመት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ቀንን ስናከብር ከወትሮ በላቀ የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ መትጋት እንዲገባን ይህን የቅዱስ ጳውሎስን ምክር መርሐችን አድርገናል። ከሁል ጊዜው በላይ ዓለምም ሆነ ሀገራችን እየተጓዘችበት ካለው አስፈሪ የጥፋት ጉዞ ትውልዱን መጠበቅ፣ ማዳንና ማሰማራት የሚቻለው የመንፈስ አንድነታችንን ለመጠበቅ ስንተጋ ብቻ ነው። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ትውልዱን በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ለመጠብቅ የመንፈስን አንድነት መርሕ ይዞ የሚጓዝ መዋቅር ነው። ታዲያ ይህንን አንድነታችንን ከውስጥም ከውጭም ፈተናዎች ለመጠበቅ እየታየ ያለውን በጎ ፍሬ ለማስቀጠል ትጋትን ገንዘብ ልናደርግ ይገባናል እንላለን። ምን እንኳን በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘንድሮውን ዓለም አቀፋዊ ጠቅላላ ጉባኤያችንን ማከናወን ባንችልም በያለንበት መዋቅር ዕለቱን ልንዘክረው ይገባናል። በመጨረሻም የዘንድሮውን ዓለም ዓቀፍዊ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የሚከናወንበትን ዕለት በቅርቡ የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን እንኳን ለዓመታዊው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ እንላለን።   የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ግንቦት 22/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን መሪ ቃል:- "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህ
በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን መሪ ቃል:- "የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ" ኤፌ ፬;፫ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የ2018ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት የ12ኛ ክፍል የናሙና ምዘና ተሰጠ። የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ግንቦት 17 2018ዓ.ም በመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህር
+6
የ2018ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት የ12ኛ ክፍል የናሙና ምዘና ተሰጠ። የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ግንቦት 17 2018ዓ.ም በመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት እየተተገበረ በሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት ተምረው ለሀገር አቀፍ ለሙከራ የናሙና ምዘና የደረሱ ተማሪዎችን ለ4ኛ ጊዜ አስፈተነ። ለዚህ የናሙና ምዘና የደረሱ በአዲስ አበባና በሸገር ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ አጥቢያዎች ሲሆኑ ምዘናውንም ግንቦት 16 ቀን ወስደዋል። በመቀጠልም በወርሐ ሰኔ መጨረሻ የማጠቃለያ ምዘና እንደሚወስዱ ይጠበቃል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)

ለሁሉም የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር:- የሰንበት ትምህርት ቤቶች  የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ ሰነድ በዚህ ሊንክ በተያያዘው ሰነድ መሠረት ተልኳል። https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-የሥራ-አመራር-ምርጫ-ማስ/ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ለሁሉም የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር:- የሰንበት ትምህርት ቤቶች  የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ ሰነድ በዚህ ሊንክ በተያያዘው ሰነድ መሠረት ተልኳል። https://eotc-gssu.org/a/የሰንበት-ት-ቤቶች-የሥራ-አመራር-ምርጫ-ማስ/

ስቅለት! እንኳን አደረሳችሁ! “ሕመማችንንም ተሸክሞአል” ኢሳ 53፡4 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube
ስቅለት! እንኳን አደረሳችሁ! “ሕመማችንንም ተሸክሞአል” ኢሳ 53፡4 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በውጭ ዓለም ለሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅርና ተባባሪ አካላት የእንግሊዘኛ ትርጉም ተሳትፎ ጥሪ። በየሀገረ ስብከቱ ያሉ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት ለተጀመተው የሰንበት
በውጭ ዓለም ለሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅርና ተባባሪ አካላት የእንግሊዘኛ ትርጉም ተሳትፎ ጥሪ። በየሀገረ ስብከቱ ያሉ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት ለተጀመተው የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት የእንግሊዘኛ ትርጉም ፕሮጀክት ሥራ ግብዓትና ተሳታፊዎችን ለመላክ በሚከተለው ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ። https://eotc-gssu.org/a/የእንግሊዝኛ-ትርጉም-ሥራ-የተሳትፎ-ጥሪ/

ሥርዓተ ትምህርቱን ለሚያስተገብሩ የአብነት መምህራንና ደቀመዛሙርት ሥልጠና ተሰጠ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የካቲት 24/2018 ዓ.ም በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው የአሰላ ማኅደረ ስ
+2
ሥርዓተ ትምህርቱን ለሚያስተገብሩ የአብነት መምህራንና ደቀመዛሙርት ሥልጠና ተሰጠ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የካቲት 24/2018 ዓ.ም በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው የአሰላ ማኅደረ ስብሐት በዓታ ለማርያምና ቅዱስ ፋኑኤል ወቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ገዳም ለሚገኙ የአብነት መምህራንና ደቀ መዛሙርት ከየካቲት 21-22/2018 ዓ.ም ለኹለት ተከታታይ ቀናት ከመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በተላኩ ልዑካን በመ/ሃ ቀሲስ ይታገሡ ደሴና በመ/ር ሚኪያስ ግዛቸው የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ ልሳነ ግዝ የማስተማር ዘዴ፣ ትምህርተ ሃይማኖትና ብቁ መምህራን እንዴት ማፍራት ይቻላል በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ሥልጠናው ተሰጥቶዋል። በሥልጠናው የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች ክፍል ሓላፊ መ/ምሕረት ወልደ ሰንበት"፣ ክቡር የገዳሙ አስተዳዳሪና የሥልጠናው አዘጋጅ መልአከ ስብሐት ገረመው ሸዋዬ ተገኝተው ሥልጠናውን በማነቃቃት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል። ከሥልጠናው በኋላም የአብነት መምህራኑ በሥርዓተ ትምህርቱ የተካተተውን ልሳነ ግእዝና ትርጓሜ መጻሕፍት ለሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እንደሚያስተምሩ ይጠበቃል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

አድዋ "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን።" መዝ 43፡5 እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
አድዋ "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን።" መዝ 43፡5 እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website