ar
Feedback
ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa

ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa

الذهاب إلى القناة على Telegram

እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa

تُعد قناة ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa (@ibnshifa) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 18 798 مشتركاً، محتلاً المرتبة 4 349 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 1 788 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 18 798 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 113، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 63، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 15.66‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 5.77‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 939 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 083 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 21 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

18 798
المشتركون
+6324 ساعات
+1737 أيام
+11330 أيام
أرشيف المشاركات
ታላቁ የኢስላም ሊቅ ሸይኹ'ል ኢስላም ኢብኑ ተይሚየህ (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:-በባሪያው ልብ ውስጥ ተውሒዱ በጠነከር ልክ እምነቱ፣እርጋታው፣በአላህ ላይ መመካቱና እርግጠኛነቱ ይጠነክራል” [መጅሙዕ አል-ፈታዋ 28/35] " t.me/ibnshifa

‏صورة من حسين عبد الله
‏صورة من حسين عبد الله

🌺ቁርአናዊ ጥያቄ ትክክለኛውን መልስ በመንካት ወደ ሰለፊዮች ቻናል ይቀላቀሉ👌
🌺ቁርአናዊ ጥያቄ ትክክለኛውን መልስ በመንካት ወደ ሰለፊዮች ቻናል ይቀላቀሉ👌

🌺ቁርአናዊ ጥያቄ ትክክለኛውን መልስ በመንካት ወደ ሰለፊዮች ቻናል ይቀላቀሉ👌
🌺ቁርአናዊ ጥያቄ ትክክለኛውን መልስ በመንካት ወደ ሰለፊዮች ቻናል ይቀላቀሉ👌

🕌 የአባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጂድ ልዩ የቻሌንጅና ጨረታ ፕሮግራም 🕌 ​✨ የመስጂዳችንን እዳ በገንዘብ ለማገዝ ታላቅ ሳምንታዊ የሶደቀል ጃሪያ አጋጣሚ! ​🚲 ከ 40,000 እስከ 50,000 ብ
🕌 የአባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጂድ ልዩ የቻሌንጅና ጨረታ ፕሮግራም 🕌 ​✨ የመስጂዳችንን እዳ በገንዘብ ለማገዝ ታላቅ ሳምንታዊ የሶደቀል ጃሪያ አጋጣሚ! ​🚲 ከ 40,000 እስከ 50,000 ብር የሚያወጣ፣ እጅግ ዘመናዊ፣ ደረጃውን የጠበቀና ለጉዞ ፍጹም ምቹ የሆነ ልዩ የብስክሌት ቻሌንጅና በተለያዩ ጨረታወች ላይ ይሳተፉ፣ የአኼራ ቤትዎን ይስሩ! 💎 ​⏰ ፕሮግራሙ ቅዳሜ ምሽት 2፡30 ላይ በቴሌግራም ግሩፓችን በቀጥታ ይተላለፋል! ⚡️ ​👇👇👇 ሊንኩን ተጭነው ይግቡ 👇👇👇 ​🔗 ወደ ላይቭ ፕሮግራሙ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፦ 👉 https://t.me/bilalmesji

የባጢል ባለቤቶች ዝም ካለ ሰው ጋር ፀብ የላቸውም!! "قَالَ ابْنُ طَاهِرٍ : سَمِعْتُ أبا إسماعيل الأنصاري الهروي يَقُولُ: عُرِضْتُ عَلَى السَّيْفِ خَمْسَ مَرَّاتٍ ، لَا يُقَالُ لِي : ارْجِعْ عَنْ مَذْهَبِكَ . لَكِنْ يُقَالُ لِي : اسْكُتْ عَمَّنْ خَالَفَكَ . فَأَقُولُ : لَا أَسْكُتُ ." سير أعلام النبلاء ١٨/٥٠٣ 🔷 አቡ ጧሂር 481 ዓ. ሂ ላይ የሞቱትን በጊዜያቸው ታጋይ የነበሩና ኹራሳን ላይም "ሸይኹ'ል ኢስላም" በሚል ትልቅ መእረግ የሚታወቁትን ታላቁን ሰለፍ አቡ ኢስማዒል አል ሀረዊን (ረሂመሁላህ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ አለ:- “አምስት ጊዜ ለሰይፍ ቀርቤያለሁ (ሊገደሉ)፣ ከያዝከው መንገድ ተመለስ አልባልም ነበር፣ ነገር ግን በሚቃረንህ ላይ ከመናገር ዝም በል ነበር የምባለው፣ እኔም መልሴ ዝም አልልም የሚል ነበር” [ሲየር አዕላም አንኑበላእ ጥራዝ 18/503] #Join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f

የባጢል ባለቤቶች ዝም ካለ ሰው ጋር ፀብ የላቸውም!! "قَالَ ابْنُ طَاهِرٍ : سَمِعْتُ أبا إسماعيل الأنصاري الهروي يَقُولُ: عُرِضْتُ عَلَى السَّيْفِ خَمْسَ مَرَّاتٍ ، لَا يُقَالُ لِي : ارْجِعْ عَنْ مَذْهَبِكَ . لَكِنْ يُقَالُ لِي : اسْكُتْ عَمَّنْ خَالَفَكَ . فَأَقُولُ : لَا أَسْكُتُ ." سير أعلام النبلاء ١٨/٥٠٣ 🔷 አቡ ጧሂር 481 ዓ. ሂ ላይ የሞቱትን በጊዜያቸው ታጋይ የነበሩና ኹራሳን ላይም "ሸይኹ'ል ኢስላም" በሚል ትልቅ መእረግ የሚታወቁትን ታላቁን ሰለፍ አቡ ኢስማዒል አል ሀረዊን (ረሂመሁላህ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ አለ:- “አምስት ጊዜ ለሰይፍ ቀርቤያለሁ (ሊገደሉ)፣ ከያዝከው መንገድ ተመለስ አልባልም ነበር፣ ነገር ግን በሚቃረንህ ላይ ከመናገር ዝም በል ነበር የምባለው፣ እኔም መልሴ ዝም አልልም የሚል ነበር” [ሲየር አዕላም አንኑበላእ ጥራዝ 18/503] #Join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f

Repost from N/a
🛑السلام عليكم ورحمة الله وبركاته 🏢በደሎቻ ከተማ ታላቅ የሙሐደራ ድግስ ➥እነሆ የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 13 / 2018 አመተ ልደት ከጧቱ 2:30 ጀምሮ እስከ ዐስር ሰላት ድረስ ለ
🛑السلام عليكم ورحمة الله وبركاته 🏢በደሎቻ ከተማ ታላቅ የሙሐደራ ድግስ ➥እነሆ የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 13 / 2018 አመተ ልደት ከጧቱ 2:30 ጀምሮ እስከ ዐስር ሰላት ድረስ ለየት ያለ የሙሐደራ ዝግጅት ተዘጋጅቷል ። ➨ የከተማው እነ የአካባቢዋ የሱና ቤተሰቦች ሁላችሁም ተጋብዛችኋል። ➽ሁላችሁም ከጓደኞቻችሁ ፣ከቤተሰቦቻችሁ እነ ከጎረቤቶቻችሁ ጋር በመሆን በመሳተፍ ሱናን ለመረዳት እነ ለማሰራጨት የበኩላችንን አስተዋጽኦ እናበርክት !!! 💺የእለቱ ተጋባዥ እንግዶቻችን ❶ ኡስታዝ ዒዙዲን ከሁልበራግ 🗞ርዕስ (حول المنهاج) ስለ ሚንሓጅ ❷ኡስታዝ አቡ ኑህ ከወራቤ 🗞ርዕስ كيف ننصر  السنة (ሱናን እንዴት እንርዳ) ➌ ዘይኑደን ዳርፈታ 🗞ርዕሰ ስለ ቢድዐህ ➍አቡ ቂርጣስ ሰበሁዲን 🗞ርዕሰ ስለ ተቅዋ ❺ ኡስታዝ ተውፊቅ 🗞ርዕሰ ስለ ተውሂድ ➥ሌሎችም ኡስታዞችና ወንድሞች ይኖራሉ ። 🌍አድራሻ ደሎቻ ከተማ አስተዳደር 02 ቀበሌ ኢማሙ አሽሻፍዒይ መድረሳ ➥የቴሌግራም ጉሩፖች https://t.me/+-z3frS3hvUg5ZTJk https://t.me/mesjedibnuteymeya https://t.me/+-z3frS3hvUg5ZTJk

ለሀራም ፍቅር ጊዜ "መርሃባ" ብላ ትቀበላለች ለሀላል ፍቅር ጊዜ "አላማ አለኝ" እያለች ትሸሻለች ከዛን …………

የዓሹራ ቀን አጿጿም እና በዕለቱ የሚከሰቱ ቢድዓዎች ————— እንደሚታወቀው የዓሹራ ቀን ፆም ማለትም ሙሀረም 10ኛውን ቀን መፆም ከታላላቅ ሶናዎች ነው። ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል:- (أَفْضَلُ الصِّيَامِ بَعْدَ رَمَضَانَ شَهْرُ اللَّهِ الْمُحَرَّمُ) رواه مسلم “ከረመዷን በኋላ በላጩ ፆም የሙሀረም ወር ፆም ነው።” [ሙስሊም 1163 ዘግበውታል።] ይህ ፆም የረመዷን ወር ከመደንገጉ በፊት ግዴታ ነበርም ተብሏል። የሚፆምበትን ምክንያት:- በመሰረቱ እንደ ሙስሊም ማንኛውም በቁርኣን እና በሶሂህ ሀዲስ የመጣን መልካም ስራ፣ ትእዛዝም ይሁን ክልከላ ምክንያቱን አወቅነውም አላወቅነውም መተግበርና መቀበል ግዴታችን ነው። በግልፅ ማስረጃ የመጣ ነገር እስከሆነ ድረስ መተግበር ነው። የዓሹራ ፆም ምክንያት አለው። በሚከተለው ሀዲስም ተብራርቷል:- عن ابن عباس ((قَدِمَ النَّبِيُّ -صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ- المَدِينَةَ فَرَأَى الْيَهُودَ تَصُومُ يَوْمَ عَاشُورَاءَ فَقَالَ مَا هَذَا؟ قَالُوا: هَذَا يَوْمٌ صَالِحٌ، هَذَا يَوْمٌ نَجَّى اللَّهُ بَنِي إِسْرَائِيلَ مِنْ عَدُوِّهِمْ فَصَامَهُ مُوسَى، قَالَ فَأَنَا أَحَقُّ بِمُوسَى مِنْكُمْ فَصَامَهُ وَأَمَرَ بِصِيَامِهِ)).  في صحيح البخاري ከኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ:- “ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ወደ መዲና በገቡ ጊዜ አይሁዶች የዓሹራን ቀን (ሙሀረም 10ኛውን ቀን) ሲፆሙ አዩዋቸው፣ ነቢዩም ለአይሁዶች ይህ ምትፆሙት ምንድነው? አሉዋቸው፣ ይህ ምርጥ ቀን ነው፣ ይህ ቀን አላህ በኒ ኢስራኢሎችን ከጠላታቸው የገላገለበት ቀን ነው፣ ሙሳ ፆሞታል። አሉ፣ ነቢዩም እኔ ለሙሳ ከናንተ የበለጠ የቀረብኩኝ ነኝ ብለው ፆሙት፣ እንዲፆምም አዘዙ።” [ቡኻሪ ዘግበውታል።] አጿጿሙን በተመለከተ:- ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል:- ( لَئِنْ بَقِيتُ إِلَى قَابِلٍ لَأَصُومَنَّ التَّاسِعَ ) ، أخرجه مسلم “ወደፊት ከቆየሁ ዘጠነኛውንም (ቀን) እፆማለሁ።” [ሙስሊም ዘግበውታል።] በዚህ መሰረት ዘጠነኛውንና አስረኛውን ቀን እንፆማለን ማለት ነው። ይህም ከምንም አይነት ጭቅጭቅ ነፃ የሆነው አጿጿም ነው። 10ኛው እና 11ኛው??? ዘጠነኛው ቀን ያመለጠው 10ኛውን እና 11ኛውን መፆሙን በተመለከተ ግን የተወሰኑ ጭቅጭቆች አሉበት። እንደ ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁላህ) ያሉ ሊቃውንቶች 10 እና 11 መፆም ይቻላል ሲሉ የሚከተለውን ሀዲስ ማስረጃ ያደርጋሉ:- (صُومُوا يَوْمَ عَاشُورَاءَ ، وَخَالِفُوا فِيهِ الْيَهُودَ ، صُومُوا قَبْلَهُ يَوْمًا أَوْ بَعْدَهُ يَوْمًا). رواه أحمد في مسنده “የዓሹራን ቀን ፁሙ፣ አይሁዶችን በመቃራንም ከፊቱ ወይም ከኋላው አንድ ቀን ፁሙ።” ኢማሙ አሕመድ በሙስነዳቸው የዘገቡት ሲሆን አልባኒን ጨምሮ ሌሎችም በርካታ ዓሊሞች ዷዒፍ ነው ብለውታል። የዚህን ሀዲስ ዷዒፍነት ያመኑ ዑለማዎች ሆነው ዘጠነኛው ቀን ያመለጠው ሰው 11ኛውን ለመፆሙ ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) "በሚቀጥለው ካደረሰኝ 9ኛውን እፆማለሁ።” ማለታቸው፣ ምክንያቱ ለ11ኛው ቀንም ይሆናል። ይላሉ፣ 9ኛውን ቀን እፆም ነበር ያሉበት ምክንያቱ አይሁዶችን ለመቃረን ነውና። 9ኛውን እና 10ኛውን ቀን ብቻ መፆም ነው፣ 9ኛው ካመለጠ ደግሞ 10ኛውን ብቻ መፆም ነው እንጂ 11ኛው የለም የሚሉት ደግሞ፣ "9ኛውን ቀን እፆም ነበር" ያሉበት ምክንያት አይሁዶችን ለመቃረን ቢሆንም  11ኛውን ለመፆም ማስረጃ አይሆንም ብለዋል። 1ኛ, ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በወቅቱ 10ኛውን ፆመው ነው ያቆሙት እንጂ 11ኛውን አልፆሙም። 2ኛ, በሚቀጥለው ካደረሰኝ 9ኛውን ወይም 11ኛውን እፆማለሁ ሳይሆን ያሉት 9ኛውን ብቻ ነው ከ10ኛው ጨምረው እንደሚፆሙት የተናገሩት። በነዚህ ምክንያቶች አንድ ሰው 9ኛው ካመለጠው 10ኛውን ብቻ ነው የሚፆመው ይላሉ። እንደ ማስረጃው አመዛኝነት ግን ከጭቅጭቁ ለመውጣትም በተቻለ መጠን 9ኛው እንዳያመልጥ ጥረት አድርጎ 9 እና 10 መፆም፣ 9ኛው ካመለጠ ግን ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ንም 9ኛው አምልጧቸው 10ኛውን ብቻ ስለ ፆሙ 10ኛውን ብቻ መፆም ነው። ወላሁ አዕለም!! የዓሹራ ቀን ቢድዓዎች። ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁላህ) እንዲህ ብለዋል:- “መኳኳልን እና መጋጌጥን፣ በቀኑ ለየት ያለ ሶላትን መስገድም ሆነ ሌሎች ለየት ያሉ ተግባሮችን በላጭነት አስመልክተው የመጡ ሀዲሶች በጠቅላላ ዷዒፍ ናቸው። የዚያን ቀን ከመፆም ውጭ ሌሎችን ነገሮች የሚጠቁም አንድም ትክክለኛ ከነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የተረጋገጠ ሀዲስ የለም። "የዓሹራ ቀን ባለው አቅም ሰፋ አድርጎ ያመቻቸ ሰው፣ የሌሎችንም አመታት አላህ ሰፋ ያድርግለት።” የሚለው ሀዲስ ኢማሙ አሕመድ ሶሂህ አይደለም ብለውታል። የዚያን ቀን እለቱን አስመልክቶ መኳኳል፣ መቀባባት፣ ሽቶ መጠቀም፣ ውሸታሞች ያስቀመጡትና ሌላውም ተቀብሏቸው ከሀዘን ወደ ደስታ የሽግግር ቀን ብለው መጋጌጫ አድርገው የያዙት ነው። ይህን ያደረጉት ሙብተዲዕና ከአህሉ ሱንና ያፈነገጡ ጭፍሮች ናቸው። አህሉ ሱንናዎች ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ያዘዙበትን የሚፈፅሙና ሸይጧን ያዘዘበትን ቢድዐ የሚጠነቀቁ (የሚርቁ) ናቸው።” [አልመናር አልሙነይፍ ፊ ሶሂሂ ወዷዒፍ 89] የሳዑዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴም "ይህን ቀን በመጋጌጥም ሆነ በምግብ ለየት ማድረግ አይፈቀድም። እንዲሁም ሺዓዎች እንደሚያደርጉትም የሀዘን ቀን አድርጎ ራስን በስለት መሰል ነገር መጉዳት አይፈቀድም። በዚያን ቀንም ሆነ በሌሎች ቀኖች ፋጢማን መለመን አይፈቀድም፣ በተውበት እንጂ አላህ ከማይምረው ከትልቁ ሺርክም ነው። ” ብሏል። [ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ ቁ. 22177] ሸይኽ ረቢዕ ቢን ሃዲ ዑመይር አልመድኸሊ (ሀፊዘሁላህ) በዚያ ቀን ለዕለቱ ብሎ ለየት ያለ ምግብ አዘጋጅቶ መብላት ይፈቀዳል ወይ? ተብለው ተጠይቀው፣ ሲመልሱ:- "በዓሹራ ለየት ያለ ነገር መዘጋጀት አለበት፣ ወደ አላህ ያቃርባል የሚል እምነት ኖሯቸው ከሆነ የሰሩት ይህ ቢድዓ ነው። ባረከላሁ ፊኩም።” ብለዋል። በሀገራችን በዚህ ቀን የተለያዩ ቢድዐዎች በተለይ ሱፊዮች ዘንድ ይፈፀማልና በዚህ ቀን ከፆም ውጪ ምንም አይነት ለየት ያለ ተግባር እንደሌለ አውቀን ከተለያዩ ቢድዐዎች ተጠንቅቀን ልናስጠነቅቅ ይገባል!!። ✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa) የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f

photo content

የእለተ ጁምዓ ሱንናዎችና ስርኣቶች ————— ① መታጠብና መቀባባት ከሰልማነል ፋሪሲይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል አለ:- “አንድ ሰው በእለተ ጁምዓ ታጥቦ፣ ከመፀዳዳትም የቻለውንም ተፀዳድቶ፣ ከሚቀባባ ነገርም ተቀባብቶ፣ ቤቱ ውስጥ ከሚገኝ ሽቶ ተቀብቶ፣ ከዚያም ከቤቱ ወጥቶ በሁለት ሰዎች መካከል ካልለያየ፣ ከዚያም የተፃፈለትን ከሰገደ፣ ከዚያም ኢማሙ በተናገረ ጊዜ ዝም ካለ፣ በዚያች ጁምዓ እና በቀጣዩዋ ጁምዓ መካከል ያለውን ወንጀል ይቅር ይባላል።” [ቡኻሪ 883 ላይ ዘግበውታል] ② ከሌላ ጊዜ የተሻለ ቆንጆ የሆነውን ልብስ መልበስ ከሙሀመድ ኢብን የህያ ኢብን ሂባን (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “አንዳችሁ ለእለተ ጁምዓ ከሌላ ጊዜ የተሻሉ ሁለት ልብሶችን ብይዝ የተሻለ ነው” [አቡዳውድ 1078 ላይ የተዘገበ ሲሆን አልባኒ ሶሂህ ብለውታል] ③ በጊዜ ወደ መስጂድ መግባት ከአቢሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “በእለተ ጁምዓ ለጀናባ የሚታጠብ አይነትን ትጥበት የታጠበ፣ ከዚያም (ወደ መስጂድ) የተጓዘ ሰው ልክ ግመል ለሶደቃ እንዳቀረበ ነው፣ በሁለተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ልክ ለሶደቃ ከብት (ላም) እንዳቀረበ ነው፣ በሶስተኛው ጊዜ የተጓዘ ሰው ልክ ቀንዳማ የሆነ ሙክት እንዳቀረበ ነው፣ በአራተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ለሶደቃ ዶሮ እንዳቀረበ ነው፣ በአምስተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ለሶደቃ እንቁላል እንዳቀረበ ነው፣ ኢማሙ  ሚንበር ላይ ከወጣ መላኢካዎች ኹጥባውን ለማዳመጥ ይሳተፋሉ።” [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል] ④ መስጂድ ከገቡ በኋላ በሁለት ሰዎች መካከል አለመለያየት (በሁለት ሰዎች ትከሻ ላይ አለመረማመድ) ጃቢር ኢብን ዐብደላህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ:- የአላህ መልእክተኛ ﷺ እየኾጠቡ እያለ አንድ ሰው ገባ፣ ሰዎች ላይ እየተረማመደ ነበርና የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ አሉት:- “ቁጭ በል! በእርግጥም አስቸግረሃል አርፍደሃልም።” [ኢብን ማጀህ 923 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ብለውታል] ⑤ ሱረቱል ከህፍን መቅራት (ማንበብ) ከአቢ ሰዒድ አል-ኹድሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “በእለተ ጁምዓ ሱረቱል ከህፍን ያነበበ ሰው በእርሱና በበይተል ዐቲቅ መካከል ብርሃን ይበራለታል።” [አልባኒ በሶሂሁል ጃሚዕ 6471 ላይ ሶሂህ ነው ብለውታል።] ⑥ ዱዓ ማብዛትና በእለተ ጁምዓ ዱዓ ተቀባይ የሚሆንባትን ሰኣት መጠባበቅ ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየላሁ ዐንሁ)  የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል አለ:- “የጁምዓ ቀን አስራ ሁለት ሰኣት ነው፣ ከእርሷ ውስጥ አንዲት ሰኣት አለች ሙስሊም የሆነ ባሪያ በዚያች ሰኣት አላህን ከጠየቀ አላህ የጠየቀውን ይሰጠዋል፣ (ያቺን ሰኣት) በመጨረሻ ሰኣት ከአስር በኋላ አካባቢ ፈልጓት።” [ሶሂሁል ጃሚዕ 8190 ላይ አልባኒ ሶሂህ ነው ብለውታል።] ከአነስ ኢብን ማሊክ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “የዱዓ ተቀባይነት የሚከጀልባትን ሰኣት ከአስር በኋላ ፀሀይ ወደ መግቢያዋ እስከምትቃረብ ድረስ ባለው ጊዜ ፈልጓት።” [ትርሚዚይ 1237 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ብለውታል።] ⑦ በነቢዩ ﷺ ላይ ሶለዋት ማብዛት ከሶፍዋን ኢብን ሱለይም (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “የጁምዓ ቀን እና የጁምዓ ሌሊት ከሆነ (ከገባ) በኔ ላይ ሶለዋት አብዙ።” [በሶሂሁል ጃሚዕ 776 ላይ አልባኒ ሶሂህ ብለውታል።] ማሳሰቢያ:- ይህ ተግባር የሚመለከተው ወንዶችን ነው። በተለይ ሽቶ ተቀብቶ መውጣት ለሴት ልጅ ሙሉ በሙሉ ሀራም ነው። ሴቶች ምንም አይነት ጌጣጌጥ ያለውን እና ወንዶችን ሊፈትን የሚችል ልብስም ሆነ ሽታ ያለው ቅባትና ሽቶ ሳይጠቀሙ ሙሉ በሙሉ የሴቶችን ሸሪዓዊ ስርኣት ያሟላ አለባበስ ለብሰው በአደብ ወደ መስጂድ መሄዱ አይከለከሉም። ✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa) የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f

🇸🇦ሰለፊዮች ሆይ የምርጥ የሰለፊይ መሻይኮች ኡስታዞች እንዲሁም ወንድሞች ቻናል እያለላቹ በየሙብተዲእ ቻናል ምን ትሰራላቹህ? አሁን ጉዳዬ ላሳጥርላቹህ እና ከታች ጆይን የምትለዋን ምልክት ስትፈልጉ
🇸🇦ሰለፊዮች ሆይ የምርጥ የሰለፊይ መሻይኮች ኡስታዞች እንዲሁም ወንድሞች ቻናል እያለላቹ በየሙብተዲእ ቻናል ምን ትሰራላቹህ? አሁን ጉዳዬ ላሳጥርላቹህ እና ከታች ጆይን የምትለዋን ምልክት ስትፈልጉ በአውራ ጣታቹ ስትፈልጉ በቀለበት ጣታቹ ብቻ በፈለጋቹት ጣታቹ ጆይን(JOIN) የምትለዋን ምልክት በመንካት ወደ ኢትዮጵያ የሰለፊዮች ቻናል ተቀላቀሉ🇸🇦

ከ"ሰሂህ አል-ቡኻሪ" ማብራሪያና ትንታኔ የተወሰዱ መሰረታዊ፣አንገብጋቢ አንዲሁም ወቅታዊ ወሳኝ ምክሮች፦   ዑመር ቢን ዐብዱል-ዐዚዝ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ ❝እውነትን ከዝንባሌህ (ከስሜትህ) ጋር ስለገጠመ ብቻ የሚከተል፣እንዲሁ ከስሜትህ ጋር ሲቃረን (ሲጣረስ) ደግሞ የሚቃወም ሰው አትሁን...አንተ በዚህ ሁኔታህ እውነትን በመከተልህ ምንዳ አታገኝም...❞   ኢብኑ ተይሚያም (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና) ይህንኑ በሁለት ቦታዎች ላይ ጠቅሶታል፤ምክንያቱም ያ ሰው የፈለገው እውነትን መከተል ሳይሆን የራሱን ፍላጎት (ስሜት/ዝንባሌ) መከተል ነበር፣ ለአላህ ብሎም አልነበረም።   በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች (Platforms) ላይ የምታሰራጨውን (ነሽር የምታደርገውን) ነገር አላህ ይጠይቅሃል—ይህንን ያሰራጨኸው ለራስህ ዝንባሌ ነው?!ወይስ ለነፍሲያ በቀል ነው?! ወይስ ለአላህ ብለህ ነው?! እያንዳንዱ ሰው ራሱን ሊመረምር (ለጠይቅ/ከራሱ ጋር መሀሰባ ሊያደርግ  ይገባል።   አንድ ሰው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች (Platforms) ላይ ምክር አዘል ፅሁፎችን (አዲዮችን) ካሰራጨ... እገሌ እኔን ፈልጎበት ነው ወይም እገሌ እኔን ነው የፈለገው" አትበል!፤ አዎን አንተን ነው የፈለገበት አንተ ሙስሊም አይደለህም እንዴ?!...ስለዚህ፣ ነገርየው  እውነት ከሆነ—የተባለው ነገር አንተን ሚመለከትህ ከሆነ አላህን በመፍራት ወደ እሱ ተመለስ። ነገርየው አንተን የማይመለከትህ ከሆነ ደግሞ አላህን አመስግን!፤ ምክንያቱም ዲን ማለት መመካከር ነውና።    የቀደሙት ሰለፎች (ሶሃቦች፣ ታቢዒዮች...) ይህን— "እገሌ እኔን ነው የፈለገው" የሚለውን ፍልስፍና በፍጹም አያውቁትም ነበር። እነርሱ እውነትን ከታላላቆችም፣ከታናናሾችም ይቀበላሉ!፤ በቁርኣን ውስጥ ስለ ሙሽሪኮች፣ ስለ ከሃዲዎች እና ስለ ኃጢአተኞች የተጠቀሱትን ታሪኮች እንኳ ይህ እኛን ነው የሚመለከተው አላሉም፤አላህ ቁርኣንን እንድናስተነትን እንዲሁ እነሱ በወደቁበት እንዳንወድቅ አዞናል   ከቀደምት ሰለፎች መካከል አንዱም እንኳ አንድን ቁርኣን ወይም ሐዲስ ሲሰማ —ይህ እኔን ነው የሚመለከተው!  ብሎ የተነሳ አናገኝም።   በእኛ እና በሰለፎች መካከል ትልቅ ልዩነት አለ!፤ ሰለፎች ወደ ራሳቸው ይመለሱ ነበር (ራሳቸውን ይወቅሱና ይገስጹ ነበር)።  እኛ ግን በተቃራኒው ይህንን በሽታ በሌሎች ላይ እንወረውራለን። ስለዚህ ከዚህ መጥፎ በሽታ ራቁ!፤ ከሚቀርቡላችሁ ጠቃሚ ምክሮች ተጠቀሙ፣ ነገር ግን ማንኛውንም ነገር ከመቀበላችሁ በፊት ራሳችሁን መርምሩ፣ተጠያቂ አድርጉ፣ እና ከእንደዚህ አይነት ስሜቶች (ዝንባሌዎች) እራሳችሁን አርቁ። አላህን ዓፊያን እንማፀነዋለን። https://t.me/HussinAssilty/3361"ሰሂህ አል-ቡኻሪ" ማብራሪያና ትንታኔ የተወሰዱ መሰረታዊ፣አንገብጋቢ አንዲሁም ወቅታዊ ወሳኝ ምክሮች፦   ዑመር ቢን ዐብዱል-ዐዚዝ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ ❝እውነትን ከዝንባሌህ (ከስሜትህ) ጋር ስለገጠመ ብቻ የሚከተል፣እንዲሁ ከስሜትህ ጋር ሲቃረን (ሲጣረስ) ደግሞ የሚቃወም ሰው አትሁን...አንተ በዚህ ሁኔታህ እውነትን በመከተልህ ምንዳ አታገኝም...❞   ኢብኑ ተይሚያም (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና) ይህንኑ በሁለት ቦታዎች ላይ ጠቅሶታል፤ምክንያቱም ያ ሰው የፈለገው እውነትን መከተል ሳይሆን የራሱን ፍላጎት (ስሜት/ዝንባሌ) መከተል ነበር፣ ለአላህ ብሎም አልነበረም።   በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች (Platforms) ላይ የምታሰራጨውን (ነሽር የምታደርገውን) ነገር አላህ ይጠይቅሃል—ይህንን ያሰራጨኸው ለራስህ ዝንባሌ ነው?!ወይስ ለነፍሲያ በቀል ነው?! ወይስ ለአላህ ብለህ ነው?! እያንዳንዱ ሰው ራሱን ሊመረምር (ለጠይቅ/ከራሱ ጋር መሀሰባ ሊያደርግ  ይገባል።   አንድ ሰው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች (Platforms) ላይ ምክር አዘል ፅሁፎችን (አዲዮችን) ካሰራጨ... እገሌ እኔን ፈልጎበት ነው ወይም እገሌ እኔን ነው የፈለገው" አትበል!፤ አዎን አንተን ነው የፈለገበት አንተ ሙስሊም አይደለህም እንዴ?!...ስለዚህ፣ ነገርየው  እውነት ከሆነ—የተባለው ነገር አንተን ሚመለከትህ ከሆነ አላህን በመፍራት ወደ እሱ ተመለስ። ነገርየው አንተን የማይመለከትህ ከሆነ ደግሞ አላህን አመስግን!፤ ምክንያቱም ዲን ማለት መመካከር ነውና።    የቀደሙት ሰለፎች (ሶሃቦች፣ ታቢዒዮች...) ይህን— "እገሌ እኔን ነው የፈለገው" የሚለውን ፍልስፍና በፍጹም አያውቁትም ነበር። እነርሱ እውነትን ከታላላቆችም፣ከታናናሾችም ይቀበላሉ!፤ በቁርኣን ውስጥ ስለ ሙሽሪኮች፣ ስለ ከሃዲዎች እና ስለ ኃጢአተኞች የተጠቀሱትን ታሪኮች እንኳ ይህ እኛን ነው የሚመለከተው አላሉም፤አላህ ቁርኣንን እንድናስተነትን እንዲሁ እነሱ በወደቁበት እንዳንወድቅ አዞናል   ከቀደምት ሰለፎች መካከል አንዱም እንኳ አንድን ቁርኣን ወይም ሐዲስ ሲሰማ —ይህ እኔን ነው የሚመለከተው!  ብሎ የተነሳ አናገኝም።   በእኛ እና በሰለፎች መካከል ትልቅ ልዩነት አለ!፤ ሰለፎች ወደ ራሳቸው ይመለሱ ነበር (ራሳቸውን ይወቅሱና ይገስጹ ነበር)።  እኛ ግን በተቃራኒው ይህንን በሽታ በሌሎች ላይ እንወረውራለን። ስለዚህ ከዚህ መጥፎ በሽታ ራቁ!፤ ከሚቀርቡላችሁ ጠቃሚ ምክሮች ተጠቀሙ፣ ነገር ግን ማንኛውንም ነገር ከመቀበላችሁ በፊት ራሳችሁን መርምሩ፣ተጠያቂ አድርጉ፣ እና ከእንደዚህ አይነት ስሜቶች (ዝንባሌዎች) እራሳችሁን አርቁ። አላህን ዓፊያን እንማፀነዋለን። https://t.me/HussinAssilty/3361

من شرح صحيح البخاري. قال عمر بن عبد العزيز :" لا تكن ممن يتبع الحق إذا وافق هواه ويخالفه إذا خالف هواه فإذا أنت لا تثاب على ما اتبعته من الحق وتعاقب على ما خالفته" قال ابن تيمية وهو كما قال رضي الله عنه لأنه في الموضعيين إنما قصد اتباع هواه لم يعمل لله. _الفوائد التي تنشرها سيسألك الله عنها هل نشرتها انتصارا لهواك وانتقاما لنفسك كل واحد يجب أن يراجع نفسه . لا تقل فلان يقصدني أو يريدني نعم يقصدك ألست مسلما ؟ أنت مخاطب بالكتاب والسنة فإذا كان فيك تتوب إلى الله وإذا لم يكن فيك تحمد الله لأن الدين النصيحة.السلف لا يعرفون هذه الفلسفة يقصدني لا يقصدني لأنهم يقبلون الحق من الصغير والكبير فكتاب الله فيه أخبار المشركين والكفار والعصاة وأمرنا الله بتدبر كتابه حتى لا نقع فيما وقعوا فيه. -لم نجد أحدا من السلف إذا سمع آية أو حديثا أو أثرا قال يقصدني ويعنيني !!! نعم يقصدك ألست ضعيفا تتعرض لاتباع هواك . -من الفوارق بيننا وبين السلف السلف يرجعون إلى أنفسهم يعاتبونها ويذمونها ويحتقرونها أما نحن فنرمي على غيرنا . تجنبوا هذه الأمراض واستفيدوا من الفوائد قبل أي أحد ففتشوا أنفسكم وحاسبوها وازجروها . نسأل الله العافية

🇸🇦ሰለፊዮች ሆይ የምርጥ የሰለፊይ መሻይኮች ኡስታዞች እንዲሁም ወንድሞች ቻናል እያለላቹ በየሙብተዲእ ቻናል ምን ትሰራላቹህ? አሁን ጉዳዬ ላሳጥርላቹህ እና ከታች ጆይን የምትለዋን ምልክት ስትፈልጉ
🇸🇦ሰለፊዮች ሆይ የምርጥ የሰለፊይ መሻይኮች ኡስታዞች እንዲሁም ወንድሞች ቻናል እያለላቹ በየሙብተዲእ ቻናል ምን ትሰራላቹህ? አሁን ጉዳዬ ላሳጥርላቹህ እና ከታች ጆይን የምትለዋን ምልክት ስትፈልጉ በአውራ ጣታቹ ስትፈልጉ በቀለበት ጣታቹ ብቻ በፈለጋቹት ጣታቹ ጆይን(JOIN) የምትለዋን ምልክት በመንካት ወደ ኢትዮጵያ የሰለፊዮች ቻናል ተቀላቀሉ🇸🇦

ፀጥ ካልክ ሁሉ ወዳጅህ ነው ከተናገርክ ግን ከመጠላትም አልፈህ ለእስርም ለግድያም ተጋለጣለህ! ተውሒድንና ሱናን የያዘ የሰለፎቹን መንገድ በአግባቡ የተረዳ ሰው ግን ዝም አይልም ማነህ አንተ! ከየት ወደየት? ፅና እንጂ ምን ያልፈሰፍስሃል? እያለ ይናገራል ይገስፃል? ተመልከት👇👇 جاء في ترجمة إسماعيل الهروي أنه قال: "عرضت على السيف خمس مرات، لا يُقال لي: ارجع عن مذهبك، لكن اسكت عمّن خالفك، فأقول: لا أسكت" [سير أعلام النبلاء ٥٠٩/١٨].

🔷 ምስጋና በመዋደዳችሁ ፣ በመተዛዘናችሁ ፣ በርህራሄያችሁ የምንቀናባችሁ ባህር ዳር የምትገኙ  የአህለሱና ተርጓሚዎች አሏህ ጀዛችሁን ይክፈላችሁ።  በሁሉም ቦታ የሚገኙ ሰለፍዮች ምን ነው በእነርሱ (አካሄድ) በተከተሉ!! ኢስላምና ሙስሊሞችን በእናንተ ይጥቀም! አሏህን  በመታዘዝ ላይ እድሜያችሁን  ያርዝመው! ሰለፍይ ተርጓሚዎችንም እንዲሁ! አምሳያችሁን ያብዛው! እስከሞት ድረስ በተውሂድ በሱና ያጽናችሁ!! በዶክተር ሸይኽ ሁሰይን ብን ሙሐመድ اللهم آمين https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة