uz
Feedback
ASTU Network ®️

ASTU Network ®️

Kanalga Telegram’da o‘tish

🛜 ASTU Network ®️ ➲ Join us || @ASTU_Network || || @ASTU_Network_Group || 📚 Library: @ASTU_Network_Library 👁‍🗨 We are here to keep you updated! ➲ Admin 📩 👤 @NS_Nazu Ⓝ Ŋazarene Ŝon [🥷] |➲| @ASTU_Network

Ko'proq ko'rsatish
4 866
Obunachilar
+1124 soatlar
+647 kunlar
+32530 kunlar
Postlar arxiv
#Fun 😸 It's personal, but lemme just share it if it can make u smile even a little... 🤗😅 Tonight, one of our relatives came to our home and asked them if I was at home. They said, "Yes, he is here,"... and called me. I met him on my way out. 🚶🏼‍♂‍➡️ And then he said, "I got some issues on my PC, so your parents once told me you're studying Software Engineering, so I thought you can fix it before I go to a technician and pay some money."😅 AFTER HEARING THIS I EXPLODED BY LAUGHING 🤣🤣 (But it was inside, coz I don't wanna hurt him) 🤣... Bruh my job isn't fixing your computer 😭😂 Then I asked what the problem was. It was just one software stopping working in the middle of something just because it wasn't updated, and it was such an old version that he doesn't even remember when he even installed it, probably 10 years ago as I guessed, a decade 💀. The RAM was 8 and there was no other problem... everything else was cool. I told him to download the latest setup and install it. And then finally he said, "THANKS A LOT! YOU SAVED ME FROM PAYING MONEY!" 🤓 ... he even took my number and said, "I will call you if there is a problem with updating it or another problem."😁 Me again: 😭😂😭 .

#Archive ቀኑ ጥር 9 ፣ 2018 ዓ.ም ነው። በወቅቱ መንግስት የአዲስአበባን መንገዶች በኮሪደር ልማት እያደሰ ስለነበር ቀድሞ ከነበረው ተጨማሪ የሰው ሀይል ተፈልጎ ነበር። በመሆኑም በጥር 8 ፣
#Archive ቀኑ ጥር 9 ፣ 2018 ዓ.ም ነው። በወቅቱ መንግስት የአዲስአበባን መንገዶች በኮሪደር ልማት እያደሰ ስለነበር ቀድሞ ከነበረው ተጨማሪ የሰው ሀይል ተፈልጎ ነበር። በመሆኑም በጥር 8 ፣ 2018 ዓ.ም ማምሻውን የአዲስአበባ መንገዶች ባለስልጣን ለ48 የስራ መደቦች ብቻ ክፍት የስራ ማስታወቂያ ያወጣል። በሚቀጥለው ቀን ከጠዋት ጀምሮ እስከ ረፋድ ድረስ በመስሪያ ቤቱ አከባቢ በሺዎች የሚቆጠሩ ስራ ፍለጋ የወጡ ወጣቶች አከባቢውን አጥለቅልቀው ማርፈዳቸው በሰዓቱ እጅግ አነጋጋሪ ሆኖ ነበር። ይህ ምስል ዝም ብሎ ሰልፍ ወይም አንድ አስገራሚ ትዕይንትን የሚያሳይ ብቻ አልነበረም። ይልቁንም በኢትዮጵያ ወጣቶች ትከሻ ላይ ያለውን የኑሮ ጫና እና የስራ ጥማት በግልጽ የሚናገር ትልቅ አዋጅ እንዲሁም ልብን የሚሰብርና የሀገራችንን ትልቁን ማህበራዊ ህመም ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነበር። ​ጥቂት የማይባሉ ወጣቶች ለዚያች ለአንዲት የስራ እድል ሲሉ ማለዳውን ብርዱን ተቋቁመው በሰልፍ ሲጠብቁ አርፍደዋል። ነገር ግን ለ48 ወንበሮች በሺዎች የሚቆጠሩ መመዝገባቸው፣ በሀገራችን ያለው የስራ አጥነት ችግር ምን ያህል አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደደረሰ ያሳያል። ወጣቱ ዝግጁ ነው፣ ጉልበትና እውቀት አለው፤ የሚጎድለው ግን ያንን አቅሙን የሚጠቀምበት መድረክ ነው። ይህ ትዕይንት ለፖሊሲ አውጭዎች ትልቅ የቤት ስራ የሚሰጥ ነው። ​ስራ አጥነት የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ ክብርና ተስፋ ጉዳይ ነው። እንዲህ ያለውን ሰፊ ክፍተት ለመሙላት መደበኛ ከሆነው አሰራር ወጣ ያለ እና ወጣቱን በተግባር ተጠቃሚ የሚያደርግ መፍትሄ ከመቼውም ጊዜ በላይ ያስፈልጋል። የእነዚህን ወጣቶች አይን ስንመለከት፣ ነገን በተሻለ ተስፋ እንዲጠብቁ የሚያደርግ ተግባራዊ እርምጃ መጠበቃችን ተገቢ ነው። |➲| @ASTU_Network

photo content

Telegram wallet በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያን ብር ከP2P ግብይት ላይ አስወጥቶታል። ብዙዎቹ ስለክሪፕቶና Trading እንዲያውቁ ትልቅ አስተዋፆ የነበረው Telegram wallet ከዚህ በኋላ
Telegram wallet በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያን ብር ከP2P ግብይት ላይ አስወጥቶታል። ብዙዎቹ ስለክሪፕቶና Trading እንዲያውቁ ትልቅ አስተዋፆ የነበረው Telegram wallet ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ asset ከማስቀመጫነት የዘለለ ጥቅም አይኖረውም። የቴሌግራም premium ለማድረግም በጣም ከባድ ይሆናል። መቼ እንደሚመለስ የታወቀ ነገር የለም። በዚህ አጋጣሚ የተለያዩ የcrypto ኮይኖችን እንገዛለንና እንሸጣለን የሚሉ አጭበርባሪዎች ስለሚበዙ ጥንቃቄ አድርጉ። Online ላይ ማንንም አትመኑ። |➲| @ASTU_Network

It's June 2nd, 2026 🙂 .

This Saturday morning, June 6, there will be a program on our campus. Representatives from INSA will come to see our club. If you have any questions and are able to attend, this program is open to all of you. Don't miss it! It will be especially easy for those who are local. Anyone who has the chance to come is invited ..................... @ECIC_ASTU .....................

Are you happy and relaxed at home? 🤔 As you expected it to be? 😕 .
Are you happy and relaxed at home? 🤔 As you expected it to be? 😕 .

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው! 🗳️🇪🇹🙂 |➲| @ASTU_Network
+1
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው! 🗳️🇪🇹🙂 |➲| @ASTU_Network

መንገድ ላይ የቀሩት ተማሪዎች‼️ ከግንቦት 21/2018 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል ባለው የጸጥታ ችግር ምክኒያት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መንገድ ላይ እንዳሉ መንገዱ ተዘግቶባቸው ለተለያዩ ችግሮች ተጋል
መንገድ ላይ የቀሩት ተማሪዎች‼️ ከግንቦት 21/2018 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል ባለው የጸጥታ ችግር ምክኒያት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መንገድ ላይ እንዳሉ መንገዱ ተዘግቶባቸው ለተለያዩ ችግሮች ተጋልጠዋል። መንገድ ተዘግቶባቸው ከቤተሰቦቻቸው ሳይደርሱ ከቀሩት ውስጥ 234  የወልደያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከወልደያ ተነስተው  ጋይንት፣ደበረታቦር፣ወረታ ፣ባህርዳር፣ጎንደርና በዙሪያ ወደ ሚገኙ ቦታዎች እየተጓዙ ያሉ ተማሪዎች ሰሜን ወሎ ዞን ፍላቂት ገረገራ ከተማ፡ሲደርሱ መንገድ ተዘግቶባቸው በከተማው ለመቆየት ተገደዋል። የከተማ አስተዳደሩ  ከንቲባ አቶ አንደበት ተስፋየ የአካባቢውን ህብረተሰብ፣ ወጣት፣የመናሃሪያ አስተባባሪዎችን፣በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን፣ሹፌሮችን፣እድሮችንና ነጋዴዎችን በማስተባበር ምግብና መጠጥ  አዘጋጅቶ ተማሪዎችን እየተንከባከቡ ይገኛል። # በከተማው የሚገኙ አልጋ ቤቶች ለተማሪዎች በነጻ  አልጋቸውን ሰጥተዋል። # የአካባቢው ወጣቶች ለመጠጥና ንጽህና መጠበቂያ ውሃ ለተማሪዎች እያቀረቡ ይገኛል። # ወጣቶችና የአካባቢው ማህበረሰብ እንጀራ እያዋጣና ወጥ እየሰራ ተማሪዎችን እየመገበ ይገኛል። # የሃይማኖት አባቶች ደግሞ በቦታው ተገኝተው ጾለትና ቡራኬ እየሰጧቸው ይገኛል። # ዛሬ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የሰኔ ጾም የሚገባበት በመሆኑ ትናንት የጾም መያዥያ ለክርስቲያን ተማሪዎች ፍየል ታርዶላቸዋል። # ለሙስሊም ተማሪዎችም ለብቻቸው ፍየል ታርዶላቸዋል። ተማሪዎቹ ከቤተሰብ ቢርቁም በፍላቂት ገረገራ ከተማ አስተዳደር ማህበረሰብ ግን የጎደለባቸው ነገር የለም ሲሉ የፍላቂት ገረራ ከተማ ነዋሪዎች ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል። ለዚህ በጎ ተግባር ለፍላቂት ገረራ ከተማ አስተዳደርና ነዋሪዎች ምስጋና ለማቅረብ እንወዳለን። (አዩዘሀበሻ) ===================== 💎⬇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇 https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው! 🗳️🇪🇹🙂 |➲| @ASTU_Network

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው! 🗳️🇪🇹🙂 .

ኢትዮጵያ ትመርጣለች! 🗳 ኢትዮጵያ ልትመርጥ ተዘጋጅታለች! 🇪🇹🙂 |➲| @ASTU_Network

#ምርጫ2018 #ማሳሰቢያ! እንደሚታወቀው ነገ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም በሀገራችን ኢትዮጵያ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ይካሄዳል። በመሆኑም ለመምረጥ የተመዘገባችሁ ተማሪዎች ምርጫው ክፍት በሚሆንበት ሰዓት በምትመርጡበት የምርጫ ጣቢያ በመገኘት የምርጫው ተሳታፊ በመሆን ሀገራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ይሁን። #ማስጠንቀቂያ! ሀገራችን እንደምታውቁት ሰላም የላትም። እዚህም እዚያም የሚሰማው ነገር ለመስማት የሚከብድ እና የሚዘገንን ከሆነ ሰነባብቷል። በመሆኑም በየአካባቢው የጸጥታ ስጋት ሊኖር ስለሚችል ተማሪዎች በተቻላችሁ መጠን እራሳችሁን እንድትጠብቁ እንላለን። ስጋቱን ለመቀነስ እና ደህንነትን ለመጠበቅ ፣ ከተፈቀደው ስዓት ውጪ ባለመንቀሳቀስ እንዲሁም ቢቻል የነገን እና ከዚያ በኋላ ያለውን ቀን ከቤት ባለመውጣት ብታሳልፉ ይመረጣል። Nobody cares! Take care of your own self! መልካም ምሽት! |➲| @ASTU_Network

" አንዱ ተማሪ ድንገተኛ ክፍል ላይ እንደደረሰ ህይወቱ አልፏል። ሁለቱ ደግሞ ኦፕራሲዮን ክፍል ከገቡ በኋላ ነው ህይወታቸው ያለፈው " - የጤና ባለሞያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በጎንደር ዩኒቨርስቲ ጤና ሳ
+1
" አንዱ ተማሪ ድንገተኛ ክፍል ላይ እንደደረሰ ህይወቱ አልፏል። ሁለቱ ደግሞ ኦፕራሲዮን ክፍል ከገቡ በኋላ ነው ህይወታቸው ያለፈው " - የጤና ባለሞያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በጎንደር ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ተማሪዎች ተሰብስበው የአርሰናል እና ፒኤስጂ የቻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ እያዩ በነበረበት ወቅት በተከሰተው ፍንዳታ የተጎዱ ተማሪዎች ለህክምና ወደ ዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል መምጣታቸውንና የሞቱ ተማሪዎች እንዳሉ አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ የጤና ባለሞያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል። በዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል እንደሚሰሩ የገለጹልን እኚሁ የጤና ባለሞያ ፍዳታው የተከሰተው ትናንት ምሽት 2 ሰዓት ተኩል ገደማ መሆኑን ገልጸውልናል። " ማን እንደጣለው አይታወቅም ቦምብ ፈንድቶ ነው በርከት ያሉ ተማሪዎች ተጎድተው የመጡት። የሞቱ አሉ መባሉም እውነት ነው " ሲሉ ተናግረዋል። " አንዱ ተማሪ ድንገተኛ ክፍል ላይ እንደደረሰ ህይወቱ አልፏል። ሁለቱ ደግሞ ኦፕራሲዮን ክፍል ከገቡ በኋላ ነው የሞቱት። ሦስት ተማሪዎች ናቸው የሞቱት " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። የተጎዱ ተማሪዎች ስንት ናቸው ? ያልናቸው ባለሙያው " የተጎዱት በርከት ያሉ ተማሪዎች ናቸው። ቁጥሩን በትክክል አላውቀውም ግን በርከት ያሉ ተጎጂ ተማሪዎች ናቸው የመጡት " ብለዋል። ተማሪዎች የተግጂዎችን ቁጥር 20 አድርሰውታል፤ በርከት ያሉ ሲባል 20 ይሆናሉ ? ስንላቸው፣ " ይሆናሉ አዎ። እንደዛ ይሆናሉ " ሲሉ መልሰዋል። ፍንዳታው የቦምብ መሆኑን እንዴት እንደታወቀ ሲገልጹ ፥ " ቦምብ መሆኑን ያወቅነው ከጉዳቱ አንፃር ፍንጥርጣሪዎቹ ቁስል ላይ ስለተገኙ ነው " ብለዋል። የተግዱት የዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል ውስጥ ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

" በፍንዳታው የተማሪዎች ህይወት አልፏል ፤ ጉዳትም ደርሷል " - የጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ⚫️ " መጀመሪያ ላይ የሆነ የሮኬት አይነት ድምጽ ተሰማን፣ ከዛ ስንነሳ እንደመብረቅ ድፍን ነው ያደረ
+1
" በፍንዳታው የተማሪዎች ህይወት አልፏል ፤ ጉዳትም ደርሷል " - የጎንደር ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ⚫️ " መጀመሪያ ላይ የሆነ የሮኬት አይነት ድምጽ ተሰማን፣ ከዛ ስንነሳ እንደመብረቅ ድፍን ነው ያደረገን ! " በጎንደር ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት የአርሴናል እና ፒኤስጂ የቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ በሚተላለፍበት ወቅት በተከሰተ "ፍንዳታ" የተማሪዎች ህይወት ማለፉና ጉዳት መድረሱን የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ተማሪዎቹ ፍንዳታው "ቦንብ" ነው ሲሉ የገለጹ ሲሆን "ዲ.ኤስ ቲቪ ውስጥ ጭንቅንቅ ብሎ ስለነበር ከቦንቡ በተጨማሪ ተረጋግጦ የተጎዳም አለ ትክክለኛው ጉዳት ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ አልቻልንም" ብለዋል። አደጋው ስለተከሰተበት ሰዓትም ሲያስረዱ ፥ "የአርሰናል ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ሊያልቅ ጥቂት ደቂቃ ሲቀረው ነው ፍንዳታውን የሰማነው" ሲሉ ለቲክቫህ ተናግረዋል። አንድ ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ የጤና ሳይንስ ተማሪ ፤ " አሁን ላይ በካምፓሱ ፖሊሶች ገብተው የፍንዳታውን መንስኤ እያጣሩ ነው " ያለ ሲሆን " አሁን ካምፓሱ ሰላም ነው፣ ግን ከዚህ በፊት ከነበረው ሁኔታ የተወሰነ ነገር ተቀይሯል። ጠዋት ላይ የሞቱ ልጆችን አስክሬን ወደቤተሰቦቻቸው ሸኝተናል። አሁን የተወሰነ የሀዘን ድባብ አለ። ግን ተረጋግቷል " ብሏል። " በትክክል የሟቾች ቁጥር ባይታወቅም በእርግጠኝነት ሁለት ተማሪዎች ሞተዋል።  ጠዋት የአስክሬን ሽኝት አድርገናል። አሁንም ቢሆን ሌላ የሞተ ተማሪ ይኖራል። ማታ ጉዳት ከደረሰባቸው ውስጥ በርካቶች በአንቡላንስ ወደ ጤና ተቋማት ተወስደዋል። ፍንዳታው ያስከተለው ጉዳት ከባድ ነው " ሲል አክሏል። አብዛኞቹ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በካምፓሱ ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑንም ጠቁሟል። በሰዓቱ ጨዋታውን ከፊት ወንበር ላይ ሁኜ እያየሁ ነበር ያለን አንድ ተማሪ ደግሞ " የመጀመሪያው የጨዋታ ስዓት አልቆ ለእረፍት ልንወጣ ስንል ነው ፍንዳታው የተከሰተው " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል። " በጣም ትልቅ አዳራሽ ነው ኳስ የምናይበት፣ ግን በጣም ሰው ሞልቶት ተጨናንቋል፣ መግቢያ መውጫ የለውም። እያየን የነበረው በፕሮጀክተር እና በቴሌቪዥን ነበር " ሲል ገልጿል። " መጀመሪያ ላይ የሆነ የሮኬት አይነት ድምጽ ተሰማን፣ ከዛ ስንነሳ እንደመብረቅ ድፍን ነው ያደረገን። ከፊታችን ብረት ስለነበር በድንጋይ መተውት ነው ብለን ነበር ያሰብነው። ግን ጭሱ በጣም አፈነን፣ በጣም ብዙ ተማሪ ነበርን እየተረጋገጥን በድንጋጤ ወጣን " ሲል አስረድቷል። " ውጪ ከወጣን በኋላ ብዙ ተማሪ መመታቱን አየን፣ እኔም መጀመሪያ ደህና ነበርኩ፣ ከወጣሁ በኋላ ሳይ እግሬን ተመትቻለሁ። ምን እንደፈነዳ እንኳ አላውቅም። እኔ ያየሁት የሞቱ ሁለት ናቸው። ሌላ አላየሁም። ግን ለሞት የሚያሰጋቸው አሉ " ሲል አክሏል። " ሁለቱንም እግሬን ነው የተመታሁት፣ እስካሁን እግሬ ላይ የገባው የፍንዳታው ፍንጥርጣሪ አልወጣልኝም። ግንባሬንም ተመትቻለሁ"  ሲል በስዓቱ የተፈጠረውን ገልጿል። የትላንት ምሽቱን ፍንዳታ ለዩንቭርስቲው ቅርበት ያላቸው የከተማው ነዋሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያረጋገጡ ሲሆን ተማሪዎች መጎዳታቸውንና ህይወታቸው ያለፉ "ተማሪዎች" መኖራቸውንም ገልጸዋል። የሞቱት ተማሪዎች ቁጥር 3 እንደሆነ፤ 3 ሌሎች ተማሪዎች ከባድ አደጋ እንደደረሰባቸውና ከ30 ያላነሱት ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን እኚሁ ቅርበት ያላቸው ሰው አረጋግጠዋል። ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ሌላኛው የጎንደር ነዋሪም " በዩኒቨርሲቲ የምትማር አንድ ልጅ አለች ብዙ ተማሪ መጎዳቱን ገልጻልኛለች እኛም መረጃውን ሰምተናል። ምን ያህል ተማሪዎች እንደተጎዱ እና ስለፍንዳታው አይነት ግን አላውቅም " ሲሉ ገልጸዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን በተመለከተ የተማሪዎች ህብረት አመራሮችን አነጋግሯል ፤ የቦምብ ፍዳታ መከሰቱንና የተማሪ ህይወት ማለፉን አረጋግጠዋል። " ፍንዳታው በቦምብ ነው የተከሰተው፤ ተማሪዎች የዲኤስቲቪ ኳስ ጨዋታ እየተከታተሉ ባሉበት ሰዓት ነው የተከሰተው " ሲሉ ነው የገለጹት። የተጎዱ ተማሪዎችን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸው አመራሮቹ " የተጎዱ ተማሪዎች የህክምና ክትትል እያደረጉ ነው ያሉት፤ በርካታ ተማሪዎች ነበሩ የተጎዱት ግን የተወሰኑ ተማሪዎች ናቸው። ውስጡ ያሉ ተማሪዎች ሙሉ አልተጎዱም " ሲሉ አክለዋል። ህይወታቸው ያለፉ ተማሪዎች ስለመኖራቸው ጥያቄ ያቀረብንላቸው የተማሪዎች ኅብረት አባላት " ሁለት ተማሪዎች ለህክምና ከገቡ በኋላ ህይወታቸው አልፏል። ሆስፒታል ከገቡ በኋላ ነው ህይወታቸው ያለፈው " ብለዋል። የተማሪዎቹ አስክሬንም ለቤተሰቦቻቸው መላኩን አክለው ገልጸውልናል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን ከዩኒቨርስቲው አመራሮች ተጨማሪ ቃል ለመቀበል ያደረገው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

photo content

#ምርጫ2018 ምን ያህል የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በመራጭነት ተመዘገቡ ? በዩኒቨርስቲዎች በተከናወነ የመራጮች ምዝገባ 20,122 ተማሪዎች የመራጭነት ምዝገባ ማከናወናቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦር
+1
#ምርጫ2018 ምን ያህል የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በመራጭነት ተመዘገቡ ? በዩኒቨርስቲዎች በተከናወነ የመራጮች ምዝገባ 20,122 ተማሪዎች የመራጭነት ምዝገባ ማከናወናቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ለሰጠው መግለጫ አስታውቋል። ለመራጭነት የተመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ማነሱን ተመልክቶ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለምን ? ሲል ለቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ ጥያቄ አቅርቧል። ሰብሳቢዋ ቁጥሩ አነስተኛ መሆኑን ገልጸው ሆኖም በአከባቢያቸው ባለ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ በርካታ ተማሪዎች በአከባቢያቸው ባለ የምርጫ ጣቢያ በመመዝገባቸው ቁጥሩ መቀነሱን በምክንያትነት ጠቅሰዋል። ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የለማው የመመዝገቢያ ፕላትፎርም ዘግይቶ ወደ ተግባር መግባቱን የገለጹት ሰብሳቢዋ ጉዳዩ ምርመራ የሚጠይቅ ቢሆንም በአጭሩ ግን በመደበኛ መኖሪያ ቦታቸው በመደበኛው የምዝገባ ሁኔታ የተመዘገቡ ብዙ አሉ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም @tikvahethiopia

#ስፖርት : በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂ አርሴናልን በፍጹም መለያ ምት በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት መሆን ቻለ። ፒኤስጂ አርሰናልን በመለያ ምት 4 ለ 3 ማሸነፍ ችሏል። ሁለቱ ክለቦች
+1
#ስፖርት : በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂ አርሴናልን በፍጹም መለያ ምት በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት መሆን ቻለ። ፒኤስጂ አርሰናልን በመለያ ምት 4 ለ 3 ማሸነፍ ችሏል። ሁለቱ ክለቦች መደበኛውን የጨዋታ ክፍለጊዜ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀው ተጨማሪ ደቂቃ ቢሰጣቸውም ሊሸናነፉ አልቻሉም። ይህን ተከትሎ ወደ መለያ ምት አምርተው ፒኤስጂ ማሸነፍ ችሏል። ፒኤስጂ ለተከታታይ አመት ነው ዋንጫውን ማንሳት የቻለው። ቲክቫህ ስፖርት / @tikvahethsport ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

🚀 Tech With Hos Joke aside — This channel is about building skills that actually open doors in tech. 👉 What you’ll find her
🚀 Tech With Hos Joke aside — This channel is about building skills that actually open doors in tech. 👉 What you’ll find here: ➲ Core 💻 Computer Science & programming fundamentals. ➲ Competitive programming insights (ICPC 🧠 mindset) ➲ Real-world 🌐 software development tools, workflows, and projects ➲ Practical data analysis 📊 concepts ➲ Lessons inspired by ICPC finalists and top 🏆 competitive programmers ➲ Career guidance from seniors working in big tech ➲ Essential tech news 📰 and trends for serious students For students who think long-term, build leverage early, and aim high.
Maintained by -👨‍💻 Mr. Hosam Adem 🔰Software Engineering student at ASTU, 🔰Competitive Programmer & A2SVian 📥 Contact hos - Telegram
Join Channel |➲| Tech with hos #techwithhos #technews #hos

#Update #CBE ውድ ደንበኛችን: * የተሻሻለውን የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ሲያዘምኑ 'Passphrase' ጠይቆዎት ከነበረ ወይም ማንኛውንም አይነት ድጋፍ ካስፈለገዎት ወደ አቅራቢያዎ በሚገኝ
#Update #CBE ውድ ደንበኛችን: * የተሻሻለውን የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ሲያዘምኑ 'Passphrase'  ጠይቆዎት ከነበረ ወይም ማንኛውንም አይነት ድጋፍ ካስፈለገዎት ወደ አቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ በመሄድ አገልግሎቱን እንደገና በቀላሉ አስጀምረው መጠቀም የሚችሉ መሆኑን እያሳወቅን፤ መተግበሪያውን እስኪያስተካከሉ ድረስ አገልግሎቱን በ USSD *889# በኩል እንዲጠቀሙ በአክብሮት እንገልፃለን። በዚህ አጋጣሚ ከሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ጋር በተያያዘ በስልክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም አይነት የአሰራር ሂደት የሌለ መሆኑን በመረዳት እራስዎን ከአጭበርባሪዎች ይጠብቁ። ለማንኛውም አይነት መረጃ 951 በነፃ ይደውሉ! * የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!! ©️ CBE |➲| @ASTU_Network