የጥበብ - መንገድ ™
Kanalga Telegram’da o‘tish
❝ Art is a step from nature toward the Infinite ~ Kahlil Gibran ™🌸📚 @abawassie ✉️
Ko'proq ko'rsatish5 662
Obunachilar
+724 soatlar
+537 kunlar
+23130 kunlar
Ma'lumot yuklanmoqda...
O'xshash kanallar
Taglar buluti
Ma'lumot yo'q
Muammo bormi? Iltimos, sahifani yangilang yoki bizning qo'llab-quvvatlash boshqaruvchimizga murojaat qiling>.
Kirish va chiqish esdaliklari
---
---
---
---
---
---
Obunachilarni jalb qilish
Avgust '26
Avgust '26
+11
0 kanalda
Iyul '26
+315
1 kanalda
Get PRO
Iyun '26
+321
1 kanalda
Get PRO
May '26
+327
2 kanalda
Get PRO
Aprel '26
+242
1 kanalda
Get PRO
Mart '26
+108
2 kanalda
Get PRO
Fevral '26
+100
1 kanalda
Get PRO
Yanvar '26
+102
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '25
+129
2 kanalda
Get PRO
Noyabr '25
+139
2 kanalda
Get PRO
Oktabr '25
+65
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '25
+40
1 kanalda
Get PRO
Avgust '25
+61
2 kanalda
Get PRO
Iyul '25
+113
6 kanalda
Get PRO
Iyun '25
+194
3 kanalda
Get PRO
May '25
+349
6 kanalda
Get PRO
Aprel '25
+306
3 kanalda
Get PRO
Mart '25
+398
4 kanalda
Get PRO
Fevral '25
+356
2 kanalda
Get PRO
Yanvar '25
+517
2 kanalda
Get PRO
Dekabr '24
+754
2 kanalda
Get PRO
Noyabr '24
+637
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '24
+719
2 kanalda
Get PRO
Sentabr '24
+49
0 kanalda
Get PRO
Avgust '24
+62
0 kanalda
Get PRO
Iyul '24
+40
0 kanalda
Get PRO
Iyun '24
+54
1 kanalda
Get PRO
May '24
+53
2 kanalda
Get PRO
Aprel '24
+75
2 kanalda
Get PRO
Mart '24
+327
3 kanalda
Get PRO
Fevral '24
+118
2 kanalda
Get PRO
Yanvar '24
+108
2 kanalda
Get PRO
Dekabr '23
+70
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '23
+46
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '23
+240
0 kanalda
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 01 Avgust | +11 |
Kanal postlari
ምናልባትም በዚህ ዘመን ካሉ ዉስን ገጣሚዎች መካከል አንዱ መዘክር ግርማ ነዉ ። ምናልባትም በዕዉቀቱ ስዩም ነዉ ሊበልጠዉ የሚችለዉ እናም ምን መሰላችሁ መዘክር ገጣሚ ብቻ እንዳላይደለ ነዉ በዚች መጠነኛ አዲስ የግጥም መድብል መፅሐፍ የተረዳሁት በዉስጡ ፍልስፍናዊ ሙግቶችን ለመመለስ ይሞክራል የእግዜርን መኖር ለነስቴፈን ሆኪንግ ምላሽ ይሰጣል ..... ብቻ ብዙ እናም መጀመሪያ ላይ ያለችዉን ግጥም ልጋብዛችሁ ፦
ለደጃችን አበባ
ለጓሯችን ዝቃቅቤ
ለሳሎናችን ሙዚቃ
ለትዝታችን ደብዳቤ
ለጉያችን መልካም ሽቱ
ለጓዳችን መተቃቀፍ
ለመደርደሪያችን መፅሐፍት
ለጥፋታችን መነቃቀፍ
ለግድግዳችን ሥዕል
ለሥዕላችን ዓይነ ልቦና
በቤታችን ቤት ለ'ንቦሳ
በጽዋችን አንዲት ጠላ ...
እና
አንዲት ወንዝ
በግቢያችን አቋርጣ የምታልፍ
አንዲት ጸሐይ
በነሐሴ ብርድ የምታቅፍ
አንዲት የምናፎጭባት አፋፍ ...
አንድ የምንቀበለዉ ጥሪ
አንድ የምንሸኘዉ ታቦት
ብዙ ስኒ አንድ ረከቦት
አንድ ፍቅር የምንሄደዉ
አንድ አንቺን የምወደዉ ...
ከቡራን ሆይ ይህች ስነ ግጥም እንዳታልፋችሁ! በበኩሌ በከበሬታ ኮፍያዬን አንስቻለሁ ለመዘክር ግርማ!
| 2 | Matn yo'q... | 138 |
| 3 | በመንገዴ - ላይ 📷 📖 | 417 |
| 4 | ሰብለ ወርቅ መጽሐፍ የቆዩ መጸሐፍት መደበር 📚📖
<< የልቦለድ >>
<< የፍልስፍና >>
<< የታሪክ >>
እንዲሁ ም መሠል
<< መጽሐፍ ት >>
እኛ ጋር ያገኛሉ ።
# በተለያዩ ዓለማት በታማኝነት Delivery ካሉበት እናደርሳለን !
☎️ 0946523397 ይደውሉልን ፡፡
ይዘዙን
@Sebleold Books Delivery 📚
@sebleworkbooks 📖 | 493 |
| 5 | እስቲ ዛሬ ደግሞ ለለውጥ ያክል አለቃ ክንፌ የላኩልኝን ግጥም መሳይ ምክር ልጋብዛችሁ!
(ለለጅ ምክር የአባት መታዘቢያ)
ልዠ ሆይ!
ሙቫይልህን አስቀምጥ
ምክሬን አድምጥ !
ጦርነትን የሚጠምቀው
እድሜውን ብትጠይቀው
የማቱሳላ ገራዥ
የአብርሀም ዣንጥላ ያዥ
በጎሽ ያረሰ
አዳምና ሄዋን ገምጠው የተፉትን በለስ አንስቶ የጎረሰ
የሎጥን ሚስት ሀውልት የላሰ
ሆኖ ታገኘዋለህ ፤
ልዠ ሆይ!
ጦርነትን የሚያውጀው
ያረጀው ነው የጃጀው
ግና ጦርሜዳ ላይ የሚዋጋው
ያንተ ብጤ ነው ለጋው፤
ሜሲ አንደመታት ኩዋስ ወደ መቃብር የሚልለጋው፤
ልዠዋ!
በጀግኖች ዘመን እንኩዋ-“ከመሞት መሰነበት” ይባላል
የሰማእት ሀውልት ሆኖ ተመቆም
ህያው ሆኖ መተኛት ይሻላል
ልዠ ሆይ!
በሀያላን እንዳትታፈስ
ሁንባቸው መንፈስ
መንፈስ መሆን ቢሳንህ ; ሁንባቸው የጎመን ፈስ
ቀን እስኪያልፍ ድረስ ወደ ጎረቤት አገር ንፈስ፤
ልዠ ሆይ !
ጦርነት ማለት
አንድ ሀሙስ የቀራቸው ሸባዎች፣
አንድ ሀሙስ ብቻ የኖሩትን አበባዎች
የሚያስቀጥፉበት አዝመራ ነውና
በሰማእትነት ስም
ምትክ አልባ ሕይወትህ ሳይከስም
እሸት አካልህን ሳይለውጡት ወደ ፍግ
ተግተህ አፈግፍግ፤
ልጄ ሆይ!
ለማንም ኩስለመናም
ነፍስ ይማር ለማለት አንኩዋ ጊዜ ለሌለው
የሙቫይልህን ካሜራ አንጂ ጠመንጃህን አትወልውለው፤
አለቃ ክነፌ በተሳትፎዎ ይቀጥሉበት!
©Bewketu Seyum | 762 |
| 6 | ‘‛ ¹ ኑዛዜ …’’
ይህ የአንድ ወጣት ኑዛዜ ነው ፡ ከቤቱ ጣሪያ የሾለኩ ስሜቶች ፣ከምርጌቱ ፈልቀቀው የወጡ አቧራ ያራሳቸው ጭቀቅታም ኤሎሄዎች …ከትራስ መሃል የተሸለቀቁ ዕንባዎች ! ከህይወት ገጼ የተፋቁ የድረሱልኝ ድምፀት እኔ ማለት '' በህይወት ጫጉላ በአንድ ለሊት ለተፈፀመች ሽፍደት የተወለድኩ ከንቱ ፍጥረት … ራሴ ባልፈጠርኩት ዓለም ለሰው ፍቃደ - ስጋ የተሰዋሁ የለሊት በግ !
ቅዥታም ህልም አንግቦ - ከህይወት ጋር እንቆቅልሽ የምጫወት መናኛ ..
‘‛ ዕንባ አለኝ ግን አይወርድልኝም ’’
ለመጽናናት በራሴ ሣቅ ደስታን እፈጥርና እስቃለሁ ግን ፈገገታዬ ጠፍቷል ልቤ ም ጭምት ሁኗል ።
“ በራሴ ገደብ የለሽ ፍላጎት ልቤን አሰቃያታለሁ ። ’’
በመውደዴ ንጋት እየጎበዝኩ ‛‛ መልሼ ! ፍቅር ከነፍሴ ጋር ያስተሳረውን ፈትል ልበጥስ አሞቅቃለሁ ።
የቀኑን ደንጋዛ ብርሃን ላለማየት እንዲጨልምልኝ ብዬ መልሼ ጥልማሞት ጨለማ እያልኩ ለሊቱን እፀየፈዋለሁ ።
እርግማን ፀጋን ያበቅል ይመስል ፡፡
በህይወቴ ተስፋ እቆርጣለሁ ፡ መልሼ ራሴ በደረስኩት የቃላት ሙዚቃ እፅናናለሁ ።
የተከለከኩትን ነገር በንጋት ጤዛ ሳይረግፍ
ክዋክብት ሳይከቱ እያሳደድኩ የኔ መሆኑ ሲገባኝ እርም እንደ ተባለ ጠብ አድርጌ ሌላን ተፈላጊ ማሳደድ እጀምራለሁ …
አዋቂና የተማረ ሰው ለመምሰል የቃላት ግሳንግስ እየደረደርኩ ተሰሚነቴን አፋጥልና መልሼ ደግሞ ሲነኩ ሲበድሉኝ የትልቅነት ካባ ብል እንደ በላው ፈትል የበጣጠሳል ..ድንጋይ እንዳረፈበት ገል እንኮታኮታለሁ ።
ልቤ በየመንገዱ እየዛለብኝ ነው ። እግሮቼ ቀርፋፋነት አቸንፏቸዋል ።
ድካም ከተፈታተነኝ ዋለ አደረ ፡ በአልመሽ አልነጋ ም ግብግብ ውስጥ ተወንክዬ መንፈሴ ሲራቆት ስጋዬ ጥልማሞት ሲበላው ልብ ብያለሁ ።
የደስታ ቃርሚያ ፍለጋ በተጫጫሩ ምርጌት ውበት ፍለጋ እሞካሞካለሁ ፡ በል ሲለኝ ከለጋ ህፃናት ፊት ውበት ርህራሄ እማለዳለሁ ፡፡ ቤተ መቅደስ ወርጄ ሰላም እረፍትን አስሳለሁ ከውበት ዛፍ እተገናለሁ ( ቢያፅናናኝ !) ግን አይሆንም ።
.. አይኖቸ የድካም ሞራ ተመርጎባቸው ፡ለዘራ ሰብ ለሰላምታ የዘረጋኋቸው እጆቼ መሰብሰብ ተስኖኝ ፡ ክንዶቼ እንደቅጠል ልመው ፡ እንደ ሀረግ መንምነው እንደ ቅርፊት ሻክረው ይታየኛል ።
በቅጡ ከዚህ ቦታ ያለላልኩት ‛‛ ህማም እህታ ’’ ያቃሰተኛል.. ጨፍጋጋ ለሊሎቶች በመባተት ና በመንቃት እኩሌታ እየተወረገረገች ነፍሴ ትቀበዘበዛለች ።
ያልፈጠርኳቸውን ቁስሎች ልብልባት ሁነውብኝ አቅም ያጠረኛል ፡ ለእንቅልፍ የተጋደምኩባቸውን ለሊቶች ፡ በዛው መቅረትን የተመኘሁባቸውም ነበሩ …
‛‛ ሁሉም ነገር ይደክማል ! ’’
አዎን በበርቱ ይደክማል ..ከዓለም ጋር ተመሳስሎ መኖር ፡ ከራስ ጋር ስሙር ፈጥሮ ..የሃሳብክን ምስቅልቅል ወደ ነገ ምዕራፍ መልክ ማስያዝ ይሄም ብርቱ ፈተና ነው ።
በመንጋቱ ተደስተህ መልሰህ በንጋቱም ብዙም ሳታተርፍበት ጊዜ መጥቶ ይሄዳል ።
ዓለም እንደ አረጄ ፈትል ተበጫጭቃና ሳስታለች
ገላዋ አይደምቅም ፡ ማህፀኗም በጎ ነገር አያፈራም ።
በመንገዴ ያዘኑ የተበደሉ ፍትህ እውነት የተራቡ ግፉዓን ያልፉበታል ። በእነዚህ የተገፉ ህዝቦች መኸል እየኖርኩ ልሰቅ ብል በየትኛው ፈገግታ !?
እኛ የሰው ልጆች
‛‛ በተስፋ ማጣት ና ተስፋ በማድረግ ወሰኖች ተሰፍተን እንቃትታለን ’’
ለመሆኑ ለመኖር ያለምናቸው ውጥንጥኖች እርባናቸው ምንድነው ?
እኛን እንደምስጥ እየቦረቡሩ እነረሱ መውዛት መጠርቃት አይደለምን !?
‛‛ ምናለ ! ምቾት ን አንድ ቀን ተኝቸው
ዘላለም ባንቀላፋሁ …!’’
© የአባ ልጅ ! | 893 |
| 7 | Matn yo'q... | 744 |
| 8 | ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፣ ሌሊቶቼ የዶስቶየቭስኪ ሆነዋል። እንቅልፍ እምቢ ሲለኝ "Notes from Underground"ን አነባለሁ፤ እናም ይህ መጽሐፍ መነበብ ያለበት ልክ በእነዚህ ሰዓታት ነው ብዬ ማመን ጀምሬያለሁ። አንዳንድ መጽሐፍት የረፋድ ጠዋቶች ናቸው። አንዳንዶች ደግሞ የከሰዓት በኋላ። ሌሎች ደግሞ የእኩለ ሌሊት።
ከዶስቶየቭስኪ ጋር ከተዋወቃችሁ በኋላ፣ በብቸኝነታችሁ ውስጥ ዳግም ብቸኛ መሆን አትችሉም። የጊዜን ገደብ ተሻግሮ፣ በዝምታ አጠገባችሁ የሚቀመጥ አንድ ሩሲያዊ ሽማግሌ አለ። ከሀሳባችሁ አያቋርጣችሁም፤ እንደውም ይገፋፋቹሃል።
አእምሮዬ ውስጥ ያለው ድምጽ የኔ ይሁን የ'Underground man' የምረሳበት ጊዜ አለ። ሁለታችንም ቀላል መልሶችን አናምንም። ሁለታችንም ንቃተ-ህሊናን ከምርቃት ይልቅ ሸክም ሆኖ አግኝተነዋል። የሰው ነፍስ በምክንያታዊነት እና በእድገት ሃልዮቶች ውስጥ ተዋቅሮ ለመቀመጥ እጅግ በጣም የሚቃረኑ ባህሪያት እንዳሉት ሁለታችንም እናስባለን።
ሆኖም የምንለያይበት አንድ ቦታ አለ። ዶስቶየቭስኪ የገደሉ ጫፍ ላይ እግዚአብሔርን እስኪያገኘው ድረስ በጥልቁ ገደል ውስጥ ተጉዟል። እኔ ደግሞ ያንኑ ጨለማ አቋርጬ ስሄድ ያገኘሁት የጠለቀ ዝምታን ብቻ ነው። አንድ ዓይነት ደረጃ ወደ ታች እንወርዳለን፣ ግን ታች ስንደርስ እርሱ ይንበረከካል፣ እኔ ግን ጉዞዬን እቀጥላለሁ።
ምናልባት ደጋግሜ ወደ'ሱ የምመለሰው ለዚህ ይሆናል፤ እምነቶቼን ስለሚያረጋግጥልኝ ሳይሆን፣ አስተሳሰቤን ሳያንኳስስ ስለሚፈትናቸው። ስቃይን ሳያሽሞነሙን የስቃይን ክብር የሚረዳ ሰው ነው። የሰውን ልጅ ወደ ማሽንነት ሳያወርድ ከንቱነቱን ማየት ይችላል። እያንዳንዱን ተቃርኖ ያጋልጥና ከተቃርኖዎቹ ጋር ብቻዬን ይተወኛል።
መጽሐፍቶቹ ከልቦለድ ይልቅ ለመቀላቀል ዘግይቼ እንደተወለድኩባቸው ውይይቶች የሚሰሙኝ ለዚህ ይመስለኛል።
አንዳንዴ እያንዳንዱ ትውልድ የራሱ የሆነ 'Underground Man' ይኖረው ይሆን ብዬ አስባለሁ። ሰውየውን ራሱን ማለቴ ሳይሆን፣ ከመጠን ያለፈ ንቃተ-ህሊና የራሱ እስር ቤት መሆን እንደሚችል የሚረዳ ሰው። በእርግጠኝነት ላይ የሚስቅ፣ ተስፋን የሚጠራጠር እና ማወቅ ብዙውን ጊዜ ስቃይን ከማከም ይልቅ ይበልጥ እንደሚያጠልቀው የሚረዳ ሰው።
ምናልባት እንቅልፍ ያጡ ሰዎች ሁሉ ውሎ አድሮ ዶስቶየቭስኪን ያገኙት ይሆናል። ያኔ የሌሊቱ ባዶነት ትንሽ ይቀንሳል።
ከአንድ ክፍለ ዘመን በፊት የሞተ አንድ ሩሲያዊ ሽማግሌ፣ አሁንም እንቅልፍ አልባ ሌሊቶቼን ይጎበኛል። ውይይታችን ቀጥሏል።
— ዮንታን አቢስ | 873 |
| 9 | Matn yo'q... | 712 |
| 10 | በ20ኛዉ ክፍለ ዘመን ከነበሩ ፋና ወጊ ሙህራን መካከል ነጋድራስ ገብረህይወት ባይከዳኝ ይገኝበታል ይህ ወጣት ሙህር ሁለት መፅሐፍቶችን ከትቧል የመጀመሪያ መፅሐፉ " አጤ ምኒልክ እና ኢትዮጵያ " የምትል ታሪክን እና በዘመኑ የነበሩ ህዝቦች ካሉበት ድንቁርና እንዲነቁ መልዕክት የሚያስተላልፍ ይዘት ያለዉ ሁለተኛዉ መፅሐፍ ደግሞ " መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር " የሚል ፖለቲካና ኢኮኖሚን የሚዳስስ ደንቅ መፅሐፍ ነዉ ። አጤ ምኒልክ እና ኢትዮጵያ የሚለዉ መፅሐፉን ስመለከት ስለ ሀገሩ ያለዉ ቁጭት መብሰልሰል ወደ ኋላ መቅርት ምን ያዕክል ያሳስበዉና ያበሳጨዉ እንደነበር እንደዚህ በማለት ይገልፃል ፦
" የኛ የኢትዮጵያዊያን ያለፈዉ ታሪክ እጅግ ያሳዝናል ። ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት ጀምሮ እስካሁን ድረስ ፍፁም የሆነ ሰላም አግኝተን ናዉቅም ....." ( በዚህ ሀሳብ ዉስጥ የዉጭ ጠላትንም የሀገር ዉስጥ አለመስማትንም እያነሳ ይብሰለሰላል ) " ካለመስማማታችን የተነሳ ግን ሌሎች ህዝቦች በአዕምሮና በጥበብ እየበረቱ ሲሄዱ እኛ ወደ ኋላ ቀረን ። እንደ አረመኔዎች እስኪቆጥሩን ድረስ ። የዱሮዉም ያሁኑም ኑሯችን እጅግ ያሳዝናል ። በመላዉ ዓለም ላይ ሰላም ሲሰፍን አዕምሮም ስትበራ እኛ በጨለማ እንኖራለን ። እርስ በርሳችንም መጠራጠር አልተዉንም ።" ይሄን ሀሳብ በጥልቀት ተመልከቱት እስካሁንም ድረስ በዚህ መንገድ መኖራችን እና አለመለወጣችን ያሳፍራል ። ለማንኛዉም መፅሐፉን አግኝታችሁ ብታነቡት ብዙ ነገር አንደሚጨምርላችሁ ጥርጥር የለኝም ። | 1 059 |
| 11 | ወጣቶች ነበርን
በእውቀቱ ስዩም
ጊዜ ሲራመድ ኮቴው ድምጥ አልባ
ከየት ተነስቶ ወደ የት ገባ
ከየት ተነስቶ ወዴት ደረሰ
ጠጉር መንጥሮ፣ ፊት እያረሰ፤
ወጣቶች ነበርን
ቅጽር የሰራን ፤ አምባ የሰበርን
ኮካ ኮላውን ባሲድ በርዘን
ብንጎነጨው፤ የማይመርዘን፤
በራዱን ያጋልን፣ ሙት ልብ ያስነሳን
ግራዋ በልተን ፤ ሎሚ ያገሳን፤
ተስፋችን ብዙ፤ እድሚያችን ለጋ
ስንሰማራ፣ ትርጉም ፍለጋ
ገላችን አይፈዝ፣ ጭቃ ቢለሰን
የማናስቀይም፤ ቡትቶ ለብሰን
ገጻችን ብሩህ፤ ልባችን ሽፍታ
ስንመነጠቅ፤ ወደ ከፍታ
የስኬት ገነት፣ ደጃፏን ከፍታ
ምትቀበለን ፣ እየመሰለን
ከቁመታችን፤ በላይ የዘለልን፤
ወጣቶች ነበርን
ዛሬ እንደዋዛ
ዘንድሮን ምሰን፤ ታች አምናን ቀበርን፤ | 853 |
| 12 | ወጣቶች ነበርን
በእውቀቱ ስዩም
ጊዜ ሲራመድ ኮቴው ድምጥ አልባ
ከየት ተነስቶ ወደ የት ገባ
ከየት ተነስቶ ወዴት ደረሰ
ጠጉር መንጥሮ፣ ፊት እያረሰ፤
ወጣቶች ነበርን
ቅጽር የሰራን ፤ አምባ የሰበርን
ኮካ ኮላውን ባሲድ በርዘን
ብንጎነጨው፤ የማይመርዘን፤
በራዱን ያጋልን፣ ሙት ልብ ያስነሳን
ግራዋ በልተን ፤ ሎሚ ያገሳን፤
ተስፋችን ብዙ፤ እድሚያችን ለጋ
ስንሰማራ፣ ትርጉም ፍለጋ
ገላችን አይፈዝ፣ ጭቃ ቢለሰን
የማናስቀይም፤ ቡትቶ ለብሰን
ገጻችን ብሩህ፤ ልባችን ሽፍታ
ስንመነጠቅ፤ ወደ ከፍታ
የስኬት ገነት፣ ደጃፏን ከፍታ
ምትቀበለን ፣ እየመሰለን
ከቁመታችን፤ በላይ የዘለልን፤
ወጣቶች ነበርን
ዛሬ እንደዋዛ
ዘንድሮን ምሰን፤ ታች አምናን ቀበርን፤ | 1 |
| 13 | ጦቢያ:- በሕይወትዎ ውስጥ የሚናፍቁትና የሚጠሉት ነገር ምንድነው? የሚያስቀናዎትስ ነገር አለ?
ሎሬት ፀጋዬ፦ ጥበብ ይናፍቀኛል። ተቻችሎ መኖር የሚያውቅ ሕዝብ ያስቀናኛል፡፡ ድንቁርና ያስፈራኛል፡፡ ጦርነት ደሞ ያስጠላኛል፡፡ አባቴ ከማይጨው ሳይመለሱ ገና በአራስነቴ ያባቴን ቤት የጣልያን ባንዳዎች ስላቃጠሉትና እናቴ ወይዘሮ ፈለቀች ዳኜና ታላቅ እህቴ ወይዘሮ አስካለ ገብረመድሀን ብቻቸውን በአገልግል አዝለውኝ ስለተሰደዱ ይመስለኛል እሳት፣ ጦርነትና ስደት የሚያስጠላኝ። (ፈገግታ)
© ጦቢያ መጽሔት 🌸📚 | 1 565 |
| 14 | በያላችሁበት ሠላም ብያለሁ ክቡራን ከተወሰነ መጠፋፋት በኋላ ዛሬ በ ቶማስ ፔን ( Thomas Paine ) ህይወት እና The age of Reason ) መፅሐፍ ትንሽ ነገር ለማለት ተገኝቻለሁ ።
ታሪክ ዉስጥ ዓለምን የለወጡ ሰዎች ሁልጊዜ ጦር የመዘዙ ( የያዙ ) ጀግኖች ብቻ አልነበሩም ። አንዳንዶች በብዕራቸው ከጦረኞች በላይ በቃላቶቻቸዉ ብዙዎችን ማርከዋል ። ከነዚህም መካከል በጣም ታዋቂዉ በ18ኛዉ ክፍለ ዘመን ተፅዕኖ ፈጣሪዉ ቶማስ ፔን ነዉ ። ቶማስ ፔን መንግስታትን በሰይፍ አልተዋጋም ነገር ግን በቃላቶቹ ሚሊዮኖችን እንዲያስቡ አድርጓል ።
ቶማስ ፒን በ1737 በእንግሊዝ ተወለደ በህይወቱ ዉስጥም የተለየ ክብር ወይም ሀብት አልነበረዉም ። በወጣትነቱ የተለያዩ ስራዎችን ሰርቷል ። ቶማስ ፔን በዘመኑ ከነበሩ ሰዎች መካከል ለየት የሚያደርገዉ ብዙ ሰዎች እዉነት ነዉ ብለዉ በቀላሉ የሚቀበሉትን እርሱ ግን ለምን ? ብሎ ይጠይቅ ነበር ።
በ1774 ወደ አሜሪካ ተሰደደ በዚያን ጊዜ አሜሪካ ከእንግሊዝ ነፃ ለመዉጣት እየታገለች ነበር ። ቶማስ ፔን በ1776 በፃፈዉ common sense የተባለዉ በቅርፅ ትንሽ በይዘት ግን ብዙ ሀሳቦችን የተሸከመ መፅሐፍ በአሜሪካ ታሪክ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጠረ ። የነፃነት ሀሳብን በቀላል እና በሚያሳምን ቋንቋ ለህዝብ አቀረበ ብዙዎችም ይህ መፅሐፍ የአሜሪካን አብዮት እንዳፋጠነ ይቆጥሩታል ።
ፔን አሜሪካን ለቆ ወደ ፈረንሳይ ሲጓዝ በዛን ወቅት ፈረንሳይ የሞት ቅጣትና ኃይለኛ ደም መፋሰስ ነበር ። ቶማስ ፔንም ለነፃነትና ለሰብዓዊ መብት ተከራከረ ። የፈረንሳይ አብዮት ወደ እልቂትና ደም መፋሰስ ሲለወጥ ዝም አላለም የሞት ቅጣቱን በግልፅ ተቃወመ ለጣላቶችም ፍትህ እንዲሰጥ ጠየቀ በዚህ ተቃዉሞ ምክንያት ወደ እስር ቤት ተወረወረ ።
ይህ የእስር ቤት ቦታ ግን ታሪክን የሚቀይር መፅሐፍ የተወለደበት ቦታ ሆነ ይህ መፅሐፍም the age of reason ይሰኛል ።
ብዙ ሰዎች ቶማስ ፔንን እንደ ኤቲስት ይመለከቱታል ነገር ግን ይህ ትክክል አይመስለኝም ( በእኔ አመለካከት እና ሀሳቦቹ ወደ ዴይዝም የሚያደላ ነዉ እናም እርሱ ዴይስት ይመስለኛል ) ቶማስ ፔን አምላክ አለ ብሎ ያምን ነበር ። ነገር ግን የሰዎች ሃይማኖት አምላክን በትክክል አያቀርብም በማለት ይቃወም ነበር ። እርሱ በአምላክ ማመኑን የሚያሳዉቅበት ሁነኛ ንግግሩ እንዲህ ይላል " I believe in one God,and no mor, " ይህ ንግግሩ አንድ ጠቃሚ ነገር ያሳየናል ። ቶማስ ፔን የሚቃወመዉ የአምላክን መኖር አይደለም ሰዎች ስለ አምላክ የፈጠሯቸዉን ተቋማት እና የማይጠየቁ ስልጣኖችን ነዉ ።
ቶማስ ፔን ለምክንያት ከፍተኛ ቦታ ይሰጣል በእርሱ ዕይታ እዉነተኛ ሃይማኖት ጥያቄዎች አያስፈሩትም ምክንያቱም እዉነተኛ ከሆነ በጥያቄ ሊወድቅ አይችልም ይላል ። ወደ the age of reason የሚወስደን ትልቁ ጥያቄም ይህ ነዉ ፦" ሰዉ አምላክን ማመን ይችላል ነገር ግን የተደራጀ ሃይማኖትን መቀበል ያስፈልገዋልን " ? ሲል ይጠይቃል ። ይህንንም ጥያቄ በራሱ ለመመለስ ፔን የፃፈዉ the age of reason በዘመኑ አወዛጋቢ መፅሐፍ ሆነ ። አንዳንዶቹ የነፃ አስተሳሰብ ጀግና ብለዉ አሞካሹት ሌሎች ደግሞ ከሃይማኖት የወጣ መናፍቅ ሰዉ ብለዉ አወገዙት ። ነገር ግን ይህ መፅሐፍ ሶስት መቶ አመታት ለመድፈን ምንም ያህል በማይቀረዉ መልኩ እስካሁንም በመነበብ ላይ ይገኛል ምክንያቱም መፅሐፉ የሚያቀርበዉ ጥያቄ የ18ኛዉ ክፍለ ዘመን ብቻ አይደለም በ20ኛዉም ሆነ የ21ኛዉ ክፍለ ዘመን ጥያቄ ስለሆነ ነዉ ።
በቀጣይ The age of reason የሚለዉን የመፅሐፉን ዋና ዋና መከራከሪያ ሀሳቦቹን ይዤላችሁ የምቀርብ ይሆናል ። | 767 |
| 15 | Matn yo'q... | 663 |
| 16 | ሕይወትን በሆነ መንገድ ኖሬያታለሁ፥ እናም በሌላ ወይም ከዚህ ተቃራኒ በሆነ አኗኗር ልኖራት ይቻለኝ ነበር፡ ብዙ ነገር ሰርቻለሁ ሌሎች ብዙ ነገሮች ደግሞ አልሰራሁም ፡፡ይህንን ሠርቻለሁ .....ያኛውን ግ ን አልሰራሁም እና ምን ይጠበስ ..?
Albert Camus
The stranger 🖤
@sebleold ✉️ | 1 105 |
| 17 | በእውቀቱ ስዩም
የታሪክ እውቀቱ ያስደንቀኛል። ሰፊ እና ዝርዝር የታሪክ እውቀት አለው። የነገስታት ታሪክ፣ የቤተክህነት ታሪክ፣ የጦርነት ታሪክ ወዘተ ወዘተ
ታሪክ በመሰረቱ አሰልቺ ነው። በዚህን ግዜ እንዲህ ሆነ እንዲህ ተከሰተ ወዘተ ወዘተ ይህንን እውቀቱን ሳይቸክ በለዛ አስውቦ በ ጥበብ ይተርካል ያነበበውን ታሪክ እንደወረደ ሳይሆን አመንዥኮ ከራሱ ጋር አዋህዶ የራሱን ቀለም ጨምሮ እንካችሁ ይላል። ደግሞም ታሪክ አውቃለሁ ብሎ አይዘላብድም የታሪክ እውቀቱን በትክክለኛ አውድ ነው የሚጠቀመው። ለሁሉም አውድ የሚሆን የታሪክ እውቀት ከየት አመጣ?! ምን ያህል ቢያነብ ነው?! 'ገርሞኝም አያባራ' አለ ጋሽ ስብሐት።
በግሌ ለግጥም እምብዛም ነኝ። መንፈሴ ብዙም ለግጥም አይደነግጥም የበእውቄን ግጥም ግን እያሳደድኩ አነባለሁ ቃላቶቹ ፍጹም ሆነው ሲሰካኩለት ሚሊየን ግዜ ተመልክቼ ተደንቄያለሁ። በሚያነሳው ሃሳብ እና ቁምነገር፣ በተመረጡ ቃላቶቹ፤ ስሜትን ቆንጥጦ በመያዙ ዘወትር እንደተደመምኩ ነው።
ሌላው የበውቄ ታላቅ ችሎታ ቧልቱ ነው። በዚህ እንደ ማርክ ትዌይን ካሉ ታላላቅ ቧልተኞች ጋር ይመደባል ቧልት የነጠረ የጥበብ ዘዬ ነው ቧልት አለቅጥ የተነፋ ፊኛን የሚያስተነፍስ የተወጠረ ስሜትን የሚያረግብ ረቂቅ መሳሪያ ነው። በእውቄ በቧልቱ ትልልቅ ጉዳዮችን በምጸት ይተቻል። ከማንኛውም አናዳጅ ሁኔታ ውስጥ ፈገግታ ይፈጥራል፤ ሳቅ ያመርታል።
ሁሉም ዘመን የራሱ ደራሲዎች፣ ገጣሚዎች፣ ፈላስፋዎች፣ ጸሀፊ ተውኔቶች አሉት። በእናንተ ዘመን ማነበር ተብዬ ብጠየቅ ሳላመነታ፦በእውቀቱ ስዩም እላለሁ።
©Tewodros Shewangizaw Zergaw | 1 408 |
| 18 | ተይው እንተወው
ተይው እንተወው፣...
የዘመን ቃፊሩን ማለፍ አልቻልንና
ይህ ዓለም ጥበቱ፣ አልመጠነንና፤
ተይው እንተወው፣...
ውጥኑ ግብ ይሁን
ጅማሬው ፍፃሜ፣
ቅፅበቷ ሙሉ ዕድሜሽ
ወቅቷ ዘላለሜ።
[ ደበበ ሰይፉ ] | 2 308 |
| 19 | https://t.me/ShegerFMRadio102_1/25861 | 1 264 |
| 20 | Matn yo'q... | 348 |
