es
Feedback
የጥበብ - መንገድ ™

የጥበብ - መንገድ ™

Ir al canal en Telegram

❝ Art is a step from nature toward the Infinite ~ Kahlil Gibran ™🌸📚 @abawassie ✉️

Mostrar más
5 506
Suscriptores
+824 horas
+447 días
+23830 días

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '26
+127
en 0 canales
junio '26
+321
en 1 canales
Get PRO
mayo '26
+327
en 2 canales
Get PRO
abril '26
+242
en 1 canales
Get PRO
marzo '26
+108
en 2 canales
Get PRO
febrero '26
+100
en 1 canales
Get PRO
enero '26
+102
en 0 canales
Get PRO
diciembre '25
+129
en 2 canales
Get PRO
noviembre '25
+139
en 2 canales
Get PRO
octubre '25
+65
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+40
en 1 canales
Get PRO
agosto '25
+61
en 2 canales
Get PRO
julio '25
+113
en 6 canales
Get PRO
junio '25
+194
en 3 canales
Get PRO
mayo '25
+349
en 6 canales
Get PRO
abril '25
+306
en 3 canales
Get PRO
marzo '25
+398
en 4 canales
Get PRO
febrero '25
+356
en 2 canales
Get PRO
enero '25
+517
en 2 canales
Get PRO
diciembre '24
+754
en 2 canales
Get PRO
noviembre '24
+637
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+719
en 2 canales
Get PRO
septiembre '24
+49
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+62
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+40
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+54
en 1 canales
Get PRO
mayo '24
+53
en 2 canales
Get PRO
abril '24
+75
en 2 canales
Get PRO
marzo '24
+327
en 3 canales
Get PRO
febrero '24
+118
en 2 canales
Get PRO
enero '24
+108
en 2 canales
Get PRO
diciembre '23
+70
en 0 canales
Get PRO
noviembre '23
+46
en 0 canales
Get PRO
octubre '23
+240
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
12 julio+9
11 julio+8
10 julio+13
09 julio+12
08 julio+7
07 julio+10
06 julio+8
05 julio+12
04 julio+15
03 julio+13
02 julio+8
01 julio+12
Publicaciones del Canal
አሁን ደሞ ሮናልዶ አርጀንቲናዊው ቢሆን እያሉ መከራከር ጀምረዋል 😭 the same logic ልጅ እያለን ክንፍ ቢኖረኝ እየበረርኩ አሜሪካ እሄድ ነበር እንደምንለው !
አሁን ደሞ ሮናልዶ አርጀንቲናዊው ቢሆን እያሉ መከራከር ጀምረዋል 😭 the same logic ልጅ እያለን ክንፍ ቢኖረኝ እየበረርኩ አሜሪካ እሄድ ነበር እንደምንለው !

2
ቤት አልከራይም አውቃለሁ ጉዳቴን ይዣት እዞራለሁ ሱቄን በደረቴ 🖤 ንጉሴ አስማማው 🎶
ቤት አልከራይም አውቃለሁ ጉዳቴን ይዣት እዞራለሁ ሱቄን በደረቴ 🖤 ንጉሴ አስማማው 🎶
270
3
Will you renounce Satan? ቮልቴር በ18ኛው ክፍለ ዘመን የነበረ ታዋቂ የፈረንሳይ አሳቢ ነው። ስለ መጽሐፍ ቅዱስ እና ስለ ሃይማኖት የነበረው አመለካከት እጅግ ጠንካራ ትችቶችን የያዘ ነበር። ቮልቴር በዋነኝነት Organized Religion እና የሃይማኖት አክራሪነትን ተችቷል። ቮልቴር መጽሐፍ ቅዱስንም በከፍተኛ ሁኔታ ተችቷል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ የታሪክ እና የሳይንስ መረጃዎች ተቃራኒዎች ናቸው ብሎ ያምን ነበር። "መጽሐፍ ቅዱስ ሞኞች የጻፉት ስነ-ምግባር የጎደላቸው ሰዎች የሚያስተምሩት እና የዋህ ሕጻናት እንዲያስታውሱት የሚደረግ ነገር ነው" በማለት በግልጽ ተችቷል:: ክርስቲያናዊ እምነትን "አስቂኝ እና አደገኛ የጭፍን እምነት" (Infamous superstition) በማለትም ይጠራው ነበር። ቮልቴር ከመሞቱ በፊት የቤተ ክርስቲያን ሰዎች ከእርሱ ጋር ለመገናኘት እና ክርስትናን እንዲቀበል ለማድረግ ብዙ ጥረት አድርገው ነበር። እናም አንድ ቀን አንድ ካህን ቮልቴር በሞት አልጋ ላይ እያለ "ሰይጣንን ትክደዋለህ?" Will you renounce Satan? ብለው ጠየቁት ቮልቴርም “ አሁን በዚህ ጊዜ አዳዲስ ጠላቶችን ማፍራት አልፈልግም” This is no time to be making new enemies በማለት በካህኑ ጥያቄ ተበሳጭቶ "በሰላም ልሙት!" Let me die in peace! ብሎ እንደነበር ይገለጻል። አብዛኞቹ የታሪክ ተመራማሪዎች ይህ አባባል “አሁን በዚህ ጊዜ አዳዲስ ጠላቶችን ማፍራት አልፈልግም” This is no time to be making new enemies ቮልቴር በትክክል የተናገረው ሳይሆን በኋላ በተረት እና ቀልድ መልክ የተፈጠረ (apocryphal) እንደሆነ ይስማማሉ። ይህ አባባል በወቅቱ ለነበሩ ሌሎች ታዋቂ ሰዎችም ሲሰጥ የነበረ እና ከጊዜ በኋላ ከቮልቴር ስም ጋር የተያያዘ ነው የሚሉ አሉ። እንደ አለቃ ገብርሃና /ነወር ለልብሴ/ ©Yonas Zewde
403
4
"ከዚህ በኋላ ክርስቶስን በገንዘብ የሸጠው ሰው ላይ አልፈርድም።በደካሞችና በሰካራሞች ልብ ውስጥ ምን እንዳለ የሚያውቀው ፈጣሪ ነው።" ከአንድ ሰዓት በኋላ ወደ ሆቴሉ ስመለስ ጨቅላ ህጻን ያቀፈች ወጣ
"ከዚህ በኋላ ክርስቶስን በገንዘብ የሸጠው ሰው ላይ አልፈርድም።በደካሞችና በሰካራሞች ልብ ውስጥ ምን እንዳለ የሚያውቀው ፈጣሪ ነው።" ከአንድ ሰዓት በኋላ ወደ ሆቴሉ ስመለስ ጨቅላ ህጻን ያቀፈች ወጣት አየሁ። ሕፃኑ ስድስት ሳምንት ቢሆነው ነው። በዚያ ቅፅፈት ነበር ህፃኑ ለመጀመርያ ጊዜ ፈገግ ሲል እናቱ ያየችው። እናትየዋ በጥልቅ ስሜት ደጋግማ ስታማትብ አየኋትና ጠየቅኋት። "ፈጣሪ ከሰማይ ሆኖ ከልቡ የሚፀልይን አንድ ሃጢያተኛ የሚሰማውን ደስታ የሚያክል ሌላ ደስታ ቢኖር የህፃን ልጇን ፈገግታ ለመጀመርያ ጊዜ የምታይ እናት ልብ ውስጥ ያለ ደስታ ነው"አለቺኝ። የወጣቷ ሴት ንግግር ጥልቅ ነበር። በውስጥ መላውን የክርስትና አስተምህሮ ብቻ ሳይሆን በፈጣሪ እና በሰው ልጅ መካከል ያለውን የአባትና ልጅ የፍቅር ትስስር የሚገልፅ ነበር። በንግግሯ የክርስቶስን መሠረታዊ ሃሳብ መግለጿ ልቤን ነካው። ሊዮቭ ኒኮላዮቪች ሚሽኪን(ልዑሉ) ©Fydor ዶስቶቭስኪ 🖤📚 @sebleworkbooks
481
5
ንቃት [ ፍራንዝ ካፍካ ፣ ትርገጓሚት፦ ሙሉ ወርቁ  ] ፈረሴን ከጋጣው እንዲያመጣልኝ አዘዝኩ።አሽከሩ አልረዳኝም፣ እኔ ራሴ ወደ ጋጣው ገባሁና ፣ ኮርቻውን ጭኜ ተፈናጠጥኩ። በርቀት ጥሩምባ ሲነፋ እሰማለሁ፣ ምን ማለት እንደሆነ ጠየኩት። ምንም አያውቅምና ፣ ምንም አልመለሰም። በሩ ላይ አስቁሞ "ጌታዬ ወደ የት ነው የምትጋልበው?" ሲል ጠየቀኝ "አላውቅም ከዚህ መራቅ ብቻ ፣ ያለማቋረጥ ከዚህ መራቅ፣ ግቤ ላይ መድረስ የምችለው በዚህ መንገድ ብቻ ነው።" አልኩ። "ግብህን ታውቀዋለህ ማለት ነው?" ጠየቀ። "አዎ" መለስኩ፣ "ተናገርኩ እኮ ከዚህ መራቅ፣ እሱ ነው ግቤ።" "ምንም ስንቅ አልያዝክም።" "ምንም አልፈልግም፤ ጉዞው ከመርዘሙ የተነሳ በመንገድ ላይ ምንም ካላገኘሁ ለመራብ እገደዳለሁ፤ ምንም ስንቅ ሊያድነኝ አይችልም፤ ደስ የሚለው ነገር ምን እንደሚገጥመኝ ባይታወቅም፣ በእርግጥ ታላቅ ጉዞ ነው።" መድረስ የሚባል ነገር የለም!
520
6
ሲራክ እስክንድርን፡ ትኩር ብሎ ሲመለከተው ከቆየ በኋላ «ለመሆኑ ስለምንድነው የምትፅፈው?» ብሎ ጠየቀው ፡፡ «ምን ማለትህ ነው?» «ድርሰት እወዳለሁ» ጥሩ ግን ድርሰት፡ ፍቅር ብቻውን በቂ አይደለም
ሲራክ እስክንድርን፡ ትኩር ብሎ ሲመለከተው ከቆየ በኋላ «ለመሆኑ ስለምንድነው የምትፅፈው?» ብሎ ጠየቀው ፡፡ «ምን ማለትህ ነው?» «ድርሰት እወዳለሁ» ጥሩ ግን ድርሰት፡ ፍቅር ብቻውን በቂ አይደለም፡፡ «ድርሰት ተልዕኮም አላት ፡፡» «ያንተ ድርሰት ተልዕኮ ምንድነው?» «በድርሰትህ ምን ለመግለፅ ነው የምትፈልገው ?» «ሀቅ ፡ውበት ፡በድርሰት ሌላ ምን የሚገለፅ ነገር አለ?» «የማን ሀቅ፡ የማን ውበት?» .... ( በዓሉ ግርማ ፡ ደራሲው)
825
7
ያ ማ ል ዳ ል 🖤
ያ ማ ል ዳ ል 🖤
917
8
"መማር፣መማር፣መማር አሁንም መማር" © ሌኒን !
"መማር፣መማር፣መማር አሁንም መማር"         © ሌኒን !
994
9
* ‹‹በገብርዬ የታማኝነት ስሜት በሕልም እንኳን መሸፈት ራሱ እንደ ክህደት የሚቆጠር ነበር፡፡ ይህንን ክህደት አንደ ደህና ነገር ለሰው ማውራት ደግሞ ከትዝብት ያለፈ ዓመፅ መስሎ ተሰማው፡፡ ሰው በሚ
* ‹‹በገብርዬ የታማኝነት ስሜት በሕልም እንኳን መሸፈት ራሱ እንደ ክህደት የሚቆጠር ነበር፡፡ ይህንን ክህደት አንደ ደህና ነገር ለሰው ማውራት ደግሞ ከትዝብት ያለፈ ዓመፅ መስሎ ተሰማው፡፡ ሰው በሚጠላው ላይ ይሸፍታል፡፡ "የተበደለ ሰውም ቢያምፅ አይፈረድበትም፡፡" በሚወዱትና በሚታመኑት ላይ እንዴት ሲደረግ ይታሰባል? ገብርዬ ተራቅቆ ባይፈላሰፍም ማንም ሰው አንድ ጠቅላላ ሥርዓት መከተል እንደሚገባ ይሰማዋል፡፡ በጦር ሜዳ ደረቱን አስጥቶ ልቡን ሰጥቶ የሚዋጋውን ያህል አገር በመበጥበጥ፤ መንደር ለማመስ ለመዝረፍ ወይም ለመፈራትና ለመታወቅ የሚደረግ ሽፍትነትን በጣም ይጠላል፤ ይጠየፋል፤ ቴዎድሮስን ያመነበት ዋናው ምክንያትም ይኸው ነበር፡፡›› የታንጉት - ምስጢር ❤️ © ከብርሃኑ ዘርይሁን
988
10
የሆነው ሁሉ ሁኖ መጨረሻ ላይ ሕሊና አዕምሮን ፈልጋ ስትሔድ በሩን ዘግተው ሊያስቆሟት የሚሞክሩት እኒያው ደባል ሱሶቹ ነበሩ። የዚያኔ ግን ድክመቷን ብቻ ሳይሆን ድክመቶቹንም ጠንቅቃ ስለተረዳች ማናቸውም ሊያስቆሟት አልቻሉም። የወይን አበባዬ 📯 የወይን 🎶 © Mickel Azmeraw
1 300
11
የወንዶች ጉዳይን ከሳቅ በዘለለ መረዳት የሚፈልግ አንድም ጤነኛ ሰው ያለ አይመስለኝም። እኔ ግን ጤና ስለሚጎለኝ የወደድኩትን ነገር እስክጠላው ድረስ መጎርጎሬን አላቆምም። የመጀመሪያው ጥያቄዬ "ደራሲው የዋና ገፀባሕሪዎቹን ስም አዕምሮ እና ሕሊና ያለው ባጋጣሚ ነው?" የሚለው ነበር። በርግጥ ይሕ ጥያቄ ብቻውን ወደ ሌላ አለም ይወስደኛል ብዬ አላሰብኩትም። ምክኒያቱም ሌሎች ደራሲዎች እንዲህ አይነት ነገር የሚያደርጉት ከላይ ሲታይ ደስ ስላላቸው ብቻ ነው የሚሆነው። አድማሱ ግን የደበቀውን ታሪክ እንድናገኝበት ያስቀመጠልን ካርታ ነበር። ፊትለፊታችን ሁኖ የተሰወረው ስቶሪ ባጭሩ ይሕ ነው። አዕምሮ ውስጣዊ ሰላም ለማግኘት ሲል ሕሊናውን እየዋሻት ነው። እንዲዋሻት የሚተባበሩት ደግሞ ስድስት ደባል ሱሶች አሉበት😃 ላይሆን ይችላል...ይሕ ቲዎሪ ብቻ ነው። እስከሚያስኬደን ድረስ እንሒድበት🙂 ወዳጆቹ...እስከጥግ የሚገዙለት አንድ ነገር አላቸው። አንደኛው ያገኘውን የሚያገበሰብስ ሆዳም ነው። አንደኛው አላፊ አግዳሚውን የሚያስረግዝ ዘማዊ ነው። አንደኛው ሰርግ ቤት ሳይቀር ከመለኮስ የማይመለስ አጫሽ ነው። አንደኛው ከሰከንድ በፊት ያገኛትን ሴት ቂጧን ካልጨበጥኩ የሚል ሴሰኛ ነው። አንደኛው እቁብ ሲወጣለት ልብስ ልግዛ ሶፋ ልቀይር ሳይሆን "ዛሬ ይጠጣል!" የሚል ጠጃም ነው። አንዳቸውም በሰውነታቸው ላይ ሀይል የላቸውም። ህይወታቸው በሱሳቸው ዙሪያ ነው የሚያጠነጥነው። ሱሰኛ ብቻ ሳይሆን ሱስ ራሱ ናቸው። ግን አትጠሏቸውም። በጣም ነው የሚያዝናኑት። ሲጫወቱ ለምናያቸው ለኛ "ጓደኞቼ በሆኑ!" የሚያስብሉ ናቸው። ያው ሱስ ሱስን ይወዳልና አንድ ላይ ሰብሰብ ብለው የመሰረቱት ማሕበርም አላቸው። የዚህ ማሕበር አስተባባሪ እና ዋና ፀሀፊ ቀጮ ነች። ቀጮ እንደሌሎቹ ሱስን አትወክልም። "ታዲያ ሱስ ካልሆነች ሱሶችን የምትሰበስባቸው እሷ ማነች?" ልትሉ ትችላላችሁ። ቀጮ ማለት ሴት ሁና ሳለ ራሷን እንደ ሴት የማታይ ሰው ነች። "ሴቶች" እየተባለ ሲወራ እንኳን እኔን ይመለከተኛል ብላ አትሰማም። ለዛም ነው ወንዶች ሴቶች ላይ ለሚፈፅሙት ተንኮል ተባባሪ ሁና የምትገኘው። ያ ማለት ግን ሴቶችን ትንቃለች ማለት አይደለም። የምትንቀው ራሷን ነው። አዕምሮን ስትመርቅ እንኳን "ቀጠን ያለችዋን፤ እንደ እንዝርት ተሽከርካሪዋን፤ እንደ ዳር ተወርዋሪዋን ያጋጥምህ!" ነው የምትለው። የሷ ምርጥ ሴት...እሷን የማትመስል ነች። ስለዚህ የነዚህ ሱሶች ሰብሳቢ የወረደ በራስ መተማመን ያላት እና ከተቃራኒ ወገን ተሰልፋ የምትዋጋ ፍጡር መሆኗ ስሜት ይሰጣል። ሱሶችን የሚጠራቸው ይሔ አይነቱ ራስ ጠልነት ነው'ና! (ቀጮ Insecurity ነች እያልኩ ነው ምዕመናን😭) አዕምሮም ወደነሱ የተሳበው በዚችው ጎኑ ነው። ማሕበራቸውን እንዲቀላቀል ያላደርጉት ጥረት አልነበረም። አንዱም አልሰራም። የሚወዳት ፍቅረኛው ከውጭ ለመጣ ሰው ጥላው መሔዷም ለሽንፈት አላበቃውም። ከዛ በፊትም ብዙ ሴት ጋ ተለያይቷል። ብርቁ አይደለም ፍቅሩን ማጣት። ለሽንፈት ያጋለጠው ከመሔዷ በፊት የጣለችበት ንግግር ነው። "አንተን ብዬ መቼም ከምመኛት አሜሪካ መቅረት አልችልም!!!" 😃 ይሕ ንግግር ጥላቻም የለውም። ርሕራሔም የለውም። ምርር ያለ እውነት ብቻ ነው። ይሔንን እውነት ለመዋጥ አዕምሮን Pride ያንቀዋል። ያጥወለውለዋል። ስራ ትቶ መኝታ ላይ ይውላል። የዚያኔ ማሕበርተኞቹ ደም እንዳሸተተ ሻርክ ተቀላቀለንና ከሀዘንህ እናድንህ እያሉ ይዞሩታል። የደረሰበትን ሽንፈት እምደሚያስረሱት ደጋግመው ቃል ይገቡለታል። መፍትሔው ያለው በነሱ እጅ እንደሆነ ጨቅጭቀው ያሳምኑታል ልክ ሁነውም ይገኛሉ። በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወደቀበት ተነስቶ መሳቅ መጫወት ይጀምራል። ሕሊናውን ከመዋሸት ቢሆንም ደስታው የተገኘው ከነበረበት መጥፎ ስሜት አንፃር ይሔ አስር እጥፍ የሚሻል መንገድ ይሆንለታል። "አሁንማ እንከባከብሀለን ቅድም እኮ ቅጥል ነው ስታደርገን የነበረው!" እያሉ የበለጠ ሰምጦ እንዲገባ ያበረታቱታል። ውሸቱ እንዲሰራ መንገዱን ያሳልጡለታል። ፅዋ ያነሱለታል። እጃቸውን ጭነው ይመርቁታል። ሁሉም ነገር አልጋ ባልጋ ይሆናል። ችግሩ ይሔንን ስሜት ለማስቀጠል ሁሌም ጧት ተነስቶ አንድ አዲስ ውሸት መዋሸት አለበት። ዛሬ አለቃውን አታልሎ ከስራ የቀረ እንደሆነ ነገ ደግሞ የእህቱን ሽቶ ሰርቆ ቤቱን መበጥበጥ ይኖርበታል። ደባል ሱሶቹ ለሚሰጡት ደስታ በምላሹ ከሱ የሚጠይቁት ሕሊናን እንዲተኛት፤ በውሸት አለም ውስጥ እንዲያባክናት...ባጭሩ Corrupt እንዲያደርጋት ነው። እንደመጀመሪያዎቹ ጊዜያትም ቶሎ ቶሎ አይስቁለትም። በሆነ ባልሆነው ነው የሚነጫነጩበት። "ታዲያ አዕምሮ ይሔ ሁሉ ውሸት ውስጥ ሲዋኝ ሕሊና እንዴት መጠርጠር ይሳናታል?" የሚለው ሁለተኛው ጥያቄዬ ነበር። እንግዲህ አዕምሮ የምናዬው የምንዳስሰው የማሰቢያ ማሽን ነው። ይሕን ማሽን የሚጠልፉትም የምናያቸው የምንዳስሳቸው አደንዛዥ ዕፆች ናቸው። ሕሊና ግን የማናያት፤ 'ማንዳስሳት...አዕምሯችንን እየወቀሰች በትክክለኛው መንገድ እንዲሔድ የምታስገድደው ስውር አለቃችን ነች። ህሊናን ሱስ አያሸንፋትም። እሷን ሚጠልፋት እንደሷ ለማዬት ለመዳሰስ የሚከብደው ዲያቢሎስ አልያም እርኩስ መንፈስ ነው። ሸዊት የምትጫወታት ገፀባህርይ (ማርታ) የምትወክለው ይቺን ከሕሊናችን ጆሮ ላይ የማትጠፋውን አንሾካሿኪ ድምፅ ነው🙂 ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ለአዕምሮ ውሸቶች የምትማልለው እሷ ነች እንጂ ሕሊና አልነበረችም። በፍቅሩ ተይዛለች። "ሶፋ ብናስቀይረው፤ ወርቅ ብናስገዛው" እያለቻት ነው ጆሮዋ ላይ ቁማ። ሐሳቧን ውድቅ እንዳታደርግባት ደግሞ ለቤተሰባችን ስንል ነው እያለች ታግባባታለች። ቤት የጋበዘችው ቀን ሶፋቸው መበላሸቱን ነግራ ልታስገዛው ስትሞክር አዕምሮ "እሰራዋለሁ!" ብሎ መዶሻ ነገር ፍለጋ ይገባል። ማርቲ አመዷ ቡን ብሎ "ምንም ነገር የለንም...ጎረቤትም የላቸውም!" ስትለው ሕሊና ተነስታ ከጠረንጴዛው ስር የተቀመጠውን ዘነዘና ትሰጠዋለች። የአዕምሮ እውነተኛ ማንነነቶች ፈንቅለውት በሚወጡበት ቅፅበቶች ሁሉ ሕሊናን ይማርካታል። በተቃራኒው ማርታን ያቅለሸልሻታል። ሁለቱ ያለ ሶስተኛ ወገን ብቻቸውን ሲገናኙ የሆነ ደስ የሚል ነገር አላቸው። አንዳቸው ላንዳቸው ነው የተፈጠሩት ያስብላሉ። መዋደዳቸውም ያስቀናል። ነገር ግን መሰረቱ ወሸት ላይ ነው'ና ሒሳቡ ሳይወራረድ ግኑኝነቱ ሊፀና አይችልም። አዕምሮ መቼም መቼም መቼም ቢሆን ከገባበት ክብ መውጣት አይችልም። ከገባበት ክብ ልታወጣው የምትችለው ሕሊናው ብቻ ነች። እሷ ደግሞ እሱን ማውጣት እንድትችል በቅድሚያ ጆሮዋ ላይ ያለችውን መንፈስ ጠንቅቃ መረዳት ይኖርባታል። መረዳት ብቻ ሳይሆን ንቃ መተው መቻልም አለባት። ያን ማድረግ እንድትችል መንፈሳዊ እገዛ ትፈልጋለች። ለዛ ነው የቤተክርስቲያኑ ትዕይንት ትክክለኛ ቦታ ላይ ገብቷል የምለው። አዕምሮ እንደልማዱ "ጌታዬ ውሸቴን የማስቀጥልበት ገንዘብ ስጠኝ!" አይነት ፀሎት ይፀልያል። እሷ ግን እውነቱን መኖር እንዲጀምሩ ነው የምትማፀነው። ጌታም የሕሊናን ልመና ሰምቶ የጠዬቀችውን ብርታት ይሰጣታል። ማርታ ያስጀመረቻትን ድራማ ትታ ሀቁን በማፍረጥረጥ አዕምሮን ከገባበት ስካር ታባንነዋለች። ነፍሱ ስትያዝ ይናዘዛል። መክፈል ያለበትን የንስሀ ዋጋ ይከፍላል። እውነቱን ማውራት ሲጀምር እሷም እንዳዲስ እየወደደችው ትመጣለች።
1 274
12
Sin texto...
897
13
[ተራ-ውበት] 'mobile mode ብታደርገው አይሻልም?... ከተቀመጠበት ወንበር ወደ ግራው ዞር ሲል ከቃላት ጉልበት በጥቂት የምትልቅ ውብ ልጅ አጠገቡ ተቀምጣለች : እንደ ማዘን ወይም እንደመሳሳት እያለች ''mobile mode ብታደርገው አይሻልም?... አይንህን ያምሃል' ደግሞም መለስ ብላ : 'ግን ምን አገባሽ' የሚል ጥያቄ ወደ አዕምሮዋ መጥቶ ፊቷ ድቅን ሲል 'ግን ይቅርታ' ብላ መልሱን መጠባበቅ ጀመረች። ልጁም ሲያነበው የነበረውን የሸሊን 'the necessity of atheism' መፅሐፍ አጥፍቶ : ቬነስና አርጤምስ እንዳያጠፏት : ሌሎች አማልዕክቶች ደብቀው ወደ ሙታን አለም የላኳት ወደ ምትመስለው እንስት እየተመለከተ... 'አመሠግናለሁ ግን መነፀሩን ያደረኩት ለዚህ ነው' ሲል መለሰላት። ድጋሜ ወደ አነዋወሩ ተመልሶ : ከአንድ ቀን በፊት ሳፖልስኪ ሲያወራው ስለነበረው ነገር ያወጣና ያወርድ ጀመረ - the stigma of atheism ይላል በልቡ : ተመልሶ ባርት ኢየሱስን የሞራል አባት ስላደረገበት አዲስ መፅሐፍ 'Love thy stranger' እያውጠነጠነ : ወደ ሲ.ኤስ ሊዊዝ ይመለሳል : እውነት ኢየሱስ የሞራል መምህር ብቻ ነው ማመን ይቻላል? የእግዚአብሔር ልጅ ካልሆነ ቀውስ ብንለው አይቀልም? እንደ ጀፈርሰን ቀደን መስፋት ይሻላል : እንደ ሸሊ ጥሩ መምህር ነው ማለት ያዋጣል? አሁንም ስለሚያነው የሸሊ 'the necessity of atheism' ማሰብ ይጀምራል : ሸሊ በዚህ መፅሐፉ ብቻ ከኦክስፎርድ ትምህርት ቤት ተባሯል : ወደ አዕምሮው 'the stigma of atheism' የመጣል። ደግሞ ስለሸሊ ውበትና ግጥም : ስለድፍረቱ : በ29 አመት ከ8 ወር ስለመሞቱ : ደግሞ ለራሱ በእኩል እድሜ እንሞታለን ይለዋል : ደግሞ ወደ ሚስቱ ሜሪ ሸሊ ፍራንክስታይን መፅሐፍ አዕምሮው ይሄዳል : እውነት መልከ ጥፉነት እና ክፋት ይገናኛሉ? ለራሱ እውነት ሜሪ የላቫታርን physiognomy ተቀብላ ይሆን? ያን አካል ማን አውሬ አደረገው? ፋንክስታይንን? ማህበረሰብ? ግን ግን ታዲያ ለውበት ያለን ምልከታ ከማህበረሰቡ ብቻ ነው እንዳንል : እነዛ 'ልትበላኝ ነው' ያሉት ህፃናትስ? physiognomy እውነት ሲሆንስ? ደግሞ ሌላ ወደ ዶክተር ትራቪስ ጥናት : ኢየሱስ የተነሳው መንፈስ ሁኖ ቢሆንስ? እነ አግናሽየስ ተሳስተው ቢሆንስ? መንፈስ አካል አለው? ኦሪገን ከፓጋኖች ጋር በዚህ ጉዳይ እንዴት ተስማማ...? በዚህ መሃል ወደ ልጅት መመልከት ጀመረ : ተያዩ 'አይንህን ግን እንዳያምህ' 'እኔን እንዴት እንደሚያደርገኝ አስታውሸ ነው...' ኦ ምን አይነት መፅሐፍ ነው የምታነቢው 'Dark romantic' ስም ጠቅሳ 'አንብበኋዋል?' 'አይ ለጊዜው እንደሱ አይነት ነገሮች ላይ ጥሩ አይደለሁም' 'እሺ ምንድነው የምታነበው?' '**,,* እና ሃይማኖት' ሃይማኖት ላይ አይኗ በራ 'በጣም religious ነህ?' የሆነ ፍንደቃ አለ ከድምጿ። 'No, I'm an atheist' 'እ?' አላመነችም : ድንጋጤ ፊቷ ላይ በትልቁ ተፅፏል : ደገመላት : ለትንሽ ጊዜ ፀጥታ ነገሰ። ትንሽ ወሬ ጀመሩ 'ስለዚህ አንተን መፍራት አለብኝ : ማንንም አትፈራማ? እንዴት ሰው በፈጣሪ አይምንም? ማስረጃ ራሱ'ኮ አያስፈልግም ...' መልስ መስጠት ጀመረ : እያወራ ከአስር በላይ ስምና መፅሐፍ ይጠቅሳል : በመሃል 'ግን ለምን?' ራሱን ጠየቀ 'ለምንድነው የምቀባጥረው?' መልስ የለም : ዝም አለ : ልጅት ማውራት ጀመረች '****' ለራሱ ከዚህ በፊት የነገረውን ነገር ደገመለት 'እውቀት የሌለው ውበት ምንም ሳይሆን ተራ ውበት ብቻ ነው!' Join 👇 https://t.me/Jonahism
1 174
14
[ተክለሃይማኖታዊ] የኢትዮጵያ ማህበረሰባዊ ውቅር በዕውቀቱ በቋንጆ ቃል እንደነገረን ተክለሃይማኖታዊ ነው : በሌላ አነጋገር እግር አልባ ባለክንፍ : ሰማይ ሰማይ ሲያንጋጥጥ የምድሩን ያጣ : ምድርን የካደ ምድርም የካደችው ማህበረሰቦች እንደ ሰፈራችን ተክልዬ እግር አልባ ባክንፍ ናቸው : በርግጥ አሁን ክንፋችንም ተቆርጦ ከሁሉም ያጣ ማህበረሰብ ሁነናል። በዕወቀቱ ሕሩይ ወልደስላሴ 'የልጅ ምክር ለአባት መታሰቢያ' የሚለውን ስራቸውን ዋቢ በማድረግ የማህበረሰባችንን የልቦና ውቅር ያሳየናል : ሕሩይ ይህን ነበር ያለው... 'ልጄ ሆይ አሳብህ ሁሉ ከሞት በኋላ ወዲያኛው ዓለም ስለሚሆነው ስለነፍስህ ነገር ይሁን እንጅ በዚህ ዓለም በስጋህ ስለሚሆነው ነገር እጅግ አትጨነቅ' ይህ የምናኔ ጥሪ የአገሪቱን ነፍስያ የሰሩ ሰዎች አስኳል ነው። ሕሩይ ቀጥረውም '...ልጄ ሆይ ወደፊት እንደዚህ ያለ መከራ ያገኘኛል ብለህ አትጨነቅ ፤ ነገር ግን የሚሆነው በእግዚአብሔር ፈቃድ ነውና ያለ እርሱ ፈቃድ የሚሆነው አያገኝህም። የውስጥህን የሚያውቅ እግዚአብሔር ካልፈረደብህ ንብረትህ እየሰፋ ጠላትህ እየጠፋ ይሄዳል እንጅ ምንም ክፉ ነገር አይመጣብህምና አትጨነቅ። በእግዚአብሔር ፈቃድ የሚመጣውን መከራ በጉልበቴ ፣ ወይም በእውቀቴ አስቀረዋለሁ ብሎ መጣጣር በመከራ ላይ መከራ ለመጨመር ነው እንጅ ሌላ ትርፍ አይገኝበትም።' አባቶቻችን በርግጥ በዕውቀቱ 'አባቶቻችን በክንፍ ከወፎች ጋር እንጅ በምድር ከሰዎች ጋር ስላልኖሩ የምድሩን ጠባይ አያውቁትም' ሲል ሃቅን ተናግሯል። በእውቀቱ በዛ ፁፉ ላይ የጠቀሰው ባለቅኔ በእውነትም ሳይገልፀን አይቀርም እንዲህ ሲል... ለገቢረ ፤ ጸሎት አዝለፈ ብሂሉ አውርድ ዘተሰቅለ ክንፈ ዘአኀዞ ሰኮና ገደፈ [ጸሎትን ያዘወተረ (አብዝቶ የተማለለ) የተሰቀለ ክንፍ አወርዳለሁ ብሎ የያዘውን ተረከዝ ጣለ] በርግጥ አወርዳለሁ ብሎ አለ እንጅ እንዳወረደ ስላልነገረን ባለቅኔው በሚገባ ገልፆናል። ይሄን ያልኩት ተክለሃይማኖት በፖለቲካ የነበራቸውን ተሳትፎ እና ብልጣብልጥነት ወደጎን አድርጌ ማህበረሰባችን 'በፅድቃቸው' እሳቤ ስለተዋቀረ ነው። Join 👇 https://t.me/Jonahism
931
15
Sin texto...
813
16
የትምህርት ቤት ምገባ (School feeding program) እንደ ሀገር ትኩረቶቻችን ምን ላይ የተኮረ ነው? ብባል በድፍረት መናገር የምችለው ነገር ቢኖር ለችግር ምላሽ በመስጠት ላይ እላለሁ። ብዙ ጊዜ ችግር ሳይከሰት (prevention) ከመከላከል ይልቅ ችግሩ ከተከሰተ በኋላ (response) መፍትሄ መስጠት ይቀለናል። ለምሳሌ አንድ የመብራት ገመድ ለመውደቅ እየተንጋደደ 2 አመት ቢቆይ ዘወር ብሎ የሚመለከት አይኖርም። ይልቅ ፖሉ ወድቆ ሰው ከጎዳ ወይ ኤሌክትሪክ ተበጥሶ ጉዳቱን ለመከላከል እንፋጠናለን። ለምን? የሚለውን ዋቃ ነው የሚያውቀው። ልክ እንደዛ ሁሉ የትምህርት ቤት ምገባ ከዛ የተለየ አላየውም። በ 2011 ዓ.ም በ ታከለ ኡማ ከንቲባነት ጊዜ በይፋ የተጀመረ በ አዲስ አበባ ከተማ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ የፈጠረ ፕሮግራም ነው። አሁን ላይ በ አዲስ አበባ ብቻ በቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶች ላይ 779 ሺ ህፃናት በትምህርት ቤቶች ላይ ቁርስና ምሳ ይመገባሉ። ቢያንስ ለ አንዱ ህፃን 54 ብር ይወጣል ብለን ብናስብ በቀን ብቻ 42 ሚሊዮን ብር ለህፃናቱ ምገባ ይወጣል። ይሄ እንግዲህ የሰራተኞችን ወጪ አይጨምርም። ይሄን ነገር በብዙ መልኩ ጠቃሚ ቢሆንም ግን ለኔ ጉዳቱ ያመዝናል። አላማው የተማሪዎችን የትምህርት መገኘት (attendance) ፣ ማቋረጥ ፣ በክፍል ውስጥ ርሀብ ለመቀነስና ከወላጆች ጫንቃ ለማላቀቅ የታሰበ ነው። ከላይ ከላዩ ጥሩ ጎኖች ያሉት ይመስላል። ግን አሁን ላይ የመንግስት ት/ቤት ምገባ በመኖሩ ብቻ ልጆችን በድፍረት ይወልዳሉ (ጥናት ቢሻም) ከብዙ ቦታ ተሰደው ወደ ምገባ ወዳለበት ቦታ ይጣሉ ፣ የተፈጠረውን ዕድል ተጠቅመው ህይወታቸውን ከመቀየር ይልቅ ሌላ ለመውለድ ይነሳሳሉ። አሁን ላይ ትምህርት ቤቶች ከትምህርት ቤትነት ይልቅ የሆድ መሙያ ገበታነታቸው በዝቷል። ልጆች ከትምህርቱ ይልቅ ስለ ምግቡ ነው የሚሄዱት ቤተሰቦቻቸውም (ሁሉንም አይወክልም) ከትምህርት ይልቅ እንዲመገቡ ብቻ የሚልኩ ናቸው። ትምህርት ቤቶች በግዴለሽ ለሚወለዱ ልጆች የሆድ መሙያነት ብቻ የተቀየረ ይመስላል። የመማር ማስተማር ስራው ሁለተኛ የሆነ ይመስላል። አሁን ላይ ትምህርት ቤቶች ለ 2 ወር በመዘጋታቸው ልጆችን የሚመግባቸውና የሚውሉበት የጠፋ ይመስላል። ብዙዎቹ ቤተሰቦች ልጆቻቸውን ማብላት አቅቷቸው ለልመና እጃቸውን የሚዘረጉበት የ ጭንቅ 2 ወራቶች ናቸው። ልጅ እንደ ልጅ ሳይሆን ምግብ የሚበላና ቤት ውስጥ የሚውል መሆኑ ትዝ የሚላቸው አሁን ነው። በርግጥ ጉዳዩ ጥናት የሚፈልግ ቢሆንም ግን ለምን ሆነ? ብለን ብንጠይቅ መልሱ ቀላል ነው። ለችግሩ ጊዜያዊ መፍትሄ መስጠት እንጂ ዘላቂ መፍትሄ ላይ አናተኩርም። በወር ብቻ እስከ 935 ሚሊዮን ብር በጀት የሚወጣበት ማዕከል ልጆቹን አብልቶ ከመላክ እናቶቹን የስራ ዕድል መፍጠር ላይ አያተኩርም። ምናልባት ይሄ ገንዘብ ብቻ በየወሩ ለምገባ የሚወጣው ገንዘብ በየወሩ አነስተኛ ፋብሪካ እየተከፈተ እንደየ ችሎታቸው እናቶቻቸውን የስራ እድል ቢፈጠር የተሻለ የጥገኝነት እና የድህነት መጠኑን መቀነስ የሚቻልበት መንገድ ጥሩ ነው ባይ ነኝ። በዚህ መንገድ ከቀጠልን ቤተሰብ መሸከም የሚገባውን ሀላፊነት ወደሌሎች ተቋሞች ባዞርነው ቁጥር የ ተረጂነት ሱስና ልጆቻቸውን የበለጠ ከመዘንጋት ያለፈ ጥቅም አይኖረውም። ብዙዎቹ በግዴለሽነት የሚወልዱ አሉ። መንግስት ለሚያበላቸው ለምን እጨነቃለሁ? የሚሉ ገጥመውኛል። ችግሩ እንዳይፈጠር መፍትሄ ማበጀት እንጂ ለችግሩ መፍትሄ መመለስ አስተማማኝ አይደለም። ብዙ የመንግስት ትምርህት ቤቶች ባለ 3 ፎቅ ሆነው ምንም የሚከላከል ብረት ሳይኖረው ልቅ ናቸው። ልጆች ከወደቁ በኋላ ለህክምና እና ለሌላ ወጪ የሚወጣው ብዙ ነው ግን ማንም ያንን ፎቆች በብረት ወይ በ ሽቦ ፍርግርግ ለማጠር የሚሞክር የለም። ልጆች ሲወድቁ ግን ልጆች ማሳከሚያ መለመን ይቀለናል። ከመጎዳታችን በፊት መፍትሄ ሰጪ ያድርገን። @ourrthought
1
17
[በቀበሮ ጉድጓድ ያለፈው ኤቲስት] 'የድፍድፍ ኩራቱ ውሃ እስኪገባው ነው!' 'ማንም በቀበሮ ጉድጓድ ተቀምጦ ኢአማኒ አይሆንም!' 'ባክህ በጭንቅ ስአት ማረኝ ትላለህ!' ይሄን እና የመሳሰሉትን ብዙ ጊዜ ሰምተናል : በርግጥ ይሄ ያን ያክል ውሸት ላይሆን ይችላል : የሰው ልጅ በፍርሃት እስር የተያዘ ፍጥረት ነው : ለዚህ ይመስለኛል ሲግመንድ ፍሮይድ ከሞት ፍርሃት እስካላመለጥን ድረስ ከሃይማኖት ጥላ እንደማንወጣ የሚነግረን። ብዙ ጊዜ ሳናስበው የፓስካልን ቁማርም ስንቆምር እናገኛለን : የሰው ልጅ አስቦ በደረሰበት አቋሙ እና ሞት ሲገናኙ : ለፍርሃቱ እጅ እንደሚሰጥ አልክድም : በውቀቱ ስዩም ከአሜን ባሻገር በተሰኘው መፅሐፉ ላይ ኢአማኒነቱን ደጋግሞ ከነገረን በኋላ : ፕሌን ላይ ሲወጣ ግን ጊዜያዊ አማኝ እንደሚሆን ይናዘዝልናል። የሰው ልጅ ደመ-ነፍስ በዚህ ሁኔታ የሚዘወር ሳይሆን አይቀርም : ሃይማኖትም ከፓተርን እና ለነገሮች agency ከመፈለግ ባለፈ : survival mechanism ሁኖ ይሆናል ኑረታችንን የያዘው። ለዚህም ሳይሆን አይቀርም : አማኞች የሆነ ኤቲስት በሞተ ቁጥር 'አምኖ ሞተ!' የሚል ድርሰትን የሚደረድሩልን። ከዚህ የደመነፍስ እስር ካመለጡት ውስጥ አንዱና በዋናነት የሚጠቀሰው ዴቪድ ሂውም ነበር : በሞት አልጋ ተቀምጦ ሰይጣንን ክዶ እግዜሩን እንዲቀበል ሲጠየቅ 'አሁን አዲስ ጠላት ለማፍራት ጊዜው ጥሩ አይደለም!' የሚመስል ሃሳብ እንደሰጠ እናስታውሳለን። ፕሪሞ ሌቪ በ1944 በኦሽዌት ማከማቻ ካምፕ ውስጥ የነበረ የጣሊያን ይሁዲ ነው :  ስለአይሁድ ማከማቻ ካምፕ ያነበበ ሁሉ አንድ የማይረሳው ታሪክ አለ - የምርጫ ስርአት! ማለትም ተሰልፈው የSS ወታደር ፊት ተሰልፈው : አንዱ ለሞት አንዱን ለአሰቃቂ ስራ የሚወሰንበት ሁኔታ : እንዲሁ አይተው እንዱን ለሞት ሌላውን ለተጨማሪ ቀን የማጨት ፕሮግራም። ሌቪ ኤቲስት ነው : አሁን ዝግመተ ለውጥ አብሮ ከሰራለት የደመነፍስ እስር ጋር ፊት ለፊት ተገናኘ : በረጅሙ ሰልፍ ላይ ተሰልፏል : አሁን የአንድ ሰው ውሳኔ ሌቪን ከህይወት መዝገብ የመሰረዝ እድል አለው : አሁን በሞትና በህይወት የመቆየቱ ነገር ግማሽ በግማሽ ሁኗል። ከዚህ የሚከፋው ግን ያለአምላክ ከዚህ አለም መሠናበቱና : ፈጣሪን ቀጥታ ሲያገኘው የሚሆነው ነገር ደግሞ ያስፈራል : በዚህ ስአት ሁሉም በዙሪያው ፀሎት ይዟል : የአዕሁድ ህዝብ አምላኩን ይለማመናል 'ኤሎሄ አሌሄ' ሌቪ ምን ይበል? የሚጠራው የሰማይ አባት የለውም። ለመፀለይ አሰበ ነገር ግን ይህ ሁሉ መከራ እንዲፈፀም ወደፈቀደ አምላክ መጮህ ምን ይሉታል? ቤተሰቦችህን ሁሉ ተሰቃይተው ሲገደሉ ቁጭ ብሎ የሚመለከትን አካል መለማመጥ ምን ይባላል? የምንስ ይቅርታ? የምንስ ንስሃ? ማነው ንስሃ መግባት ያለበት? አምላክ ወይስ ሌቪ? ደግሞስ ይሄ በመጨረሻ ስአት ልትሸነፍ ሰትል የጭዋታውን ህግ መቀየር : አምላክን መማጭበርበር መሞከር ትክክልን ነው? እስከዛሬ የቆምክለትን ሃሳብ በፍርሃትስ መሻር ተገቢ ነው? ሌቪ ይሄን ሁሉ የራስ ሙግን 'The Drowned and the Saved' ላይ ነው የሚያጫውተን : ደግሞም ይላል : ብተርፍስ? አቋሜን በፍርሃት እንደቀየርኩ እያወኩ እንዴት ነገ ራሴን ላከብረው እችላለሁ? እንዴት ከራሴ ጋር ልኖርስ እችላለሁ? በርግጥ አምላክን እንደ አማኞቹ አውሬ አድርጎ የሚስል ያለ አይመስለኝም : ሼህ ሁሴን ጅብሪል 'ተመስገን ነው'ይ ሰው ባያሌው ታሞ ያማረሩት እንዴው : ይጨምራል ዴሞ' ሲሉ የአምላካቸውን ባህሪ እየነገሩን ነበር። አሁን ጥያቄው እንዴት በሞት ፊት ተሰልፈን እኛ ስለተረፍን ብቻ አምላክን እናመሠግናለን : እንዴት Innocent የሆኑ አካላት ሲሞቱ እያየን በአምላክ እናምናለን? ስለተረፍን? ያልተረፉትስ? አንተ ገነት ገብትህ እናትህ ለዘላለም በገሃነም ስለምትቀጣ የምን ደስታ ነው? የምር በፀሎታችሁ እና ምስጋናችሁ አምላካችሁ ይደሰታል? ማታ ዝናብ ዘንቦ : ጎርፍ ልጅን ከእናቱ ነጥቆ መድረሻውን ወደ ሙታን አለም ያደረገበት ጎዳና ላይ እዛው ቦታ : እዛው ስፍራ ላይ ፀሃይ ስላወጣ የተመሠገነን አምላክ ሳስብ 'አቤት የሰው ልጅ ግፍ' እንድል ያደርገኛል። ሌቪ አሁንም በሌላ ስራው [If This Is a Man] ላይ ሌላ ስለዛ ሰልፍ ላይ አንድ ኹን የተባለ ሰው ስላልተመረ : ድምፁን ከፍ አድርጎ ሲያመሠግን የነበረበትን ክስተት ያስታውሰናል : ታዲያ በዛው ከሱ ጋር የግሪኩ ቢፖ : የሃያ አመት ታዳጊው ምስኪን እንዲሞት ተፈርዶበታል : በአንድ ሰልፍ አንዱ 'ሃሌ ሉያ' ይላል : ቢፖ በቁሙ በድን ሁኗል : ገና እስኪሞት እክኪገደል ደግሞ ውስጡ በፍርሃት የሚሆነውን ባሰብኩ ጊዜ እንባዬ ይመጣል : የምር ይሄን ስፅፍም ከምባ ጋር ነው : በዝምታ ኦናው ላይ አፍጥጦ ከሞት መንፈስ ጋር የሚታገለውን ቢፖ ባሰብኩ ቁጥር ሁሉ ከአዕኖቼ ጋር ለመታገል እገደዳለሁ። 'Kuhn is out of his senses. Does he not see Beppo the Greek…? Does he not understand that what has happened today is an abomination, which no propitiatory prayer, no pardon, no expiation by the guilty nothing at all in the power of man can ever heal again? If I was God, I would spit at Kuhn’s prayer.' አንደኛ አመት በኮሮና ጊዜ ኮመን ኮርስ ትምህርቶችን ስንወስድ : አንድ መምህር በማይመለከተው ነገር ሁሉ ስለፈጣሪ ሲያነሳ እጀን አውጥቼ 'መምህር ይኑር አይኑር ስለማናውቀው አካል ያለክፍለ ጊዜው ባትነግረን መልካም ነው!' ባልኩት ጊዜ 'እንደዚህ አሳምሮ ፈጥሮህና ዛሬ እንድትነቃ ያደረገህ እሱ ነው' ነበር ያለኝ። መልሴ ተማሪዎች በመምህሩ እንዲስቁበት አድርጎቸው ነበር 'አሃ ትናንት ያልነቁትና መልከ ጥፉዎች ላለመኖሩ ማስረጃ ናቸው ማለት ነው?' የሚል ነበር መልሴ : ዛሬም ከመኪና አደጋ እና ከትልቅ አደጋ የተረፉ ሰዎች 'እግዚአብሔር ይመስገን' ብለው ሲያወድሱት ሳይ 'አይ የሰው ልጅ ግፍ!' ያሰኘኛል። አዎ! የደመነፍስ ፍርሃታችን እንድናምን ሊገፋፋን ይችላል : ነገር ግን የምር ካሰብን አምላክን ያወደሰነውና ያከበርነው ሁሉ በሰራው አስቀያሚ ስራ መሃል ነው። ሰው እንዴት የዋህ ህፃናት በሞት ማጭድ ተጋደመው እያዬ : ራሱ ስለተረፈ ብቻ አምባገነን የሰማዩን አለቃ ሊያመሠግን ይዳዳዋል? ጓደኞችህን ሁሉ ባላጠፉት ጥፋት ያሰረን መንግስት አንተን ስላላሰረህ ብቻ በየመድረኩ እየሄድክ የዛን መንግስት ትልቅነት ትሰብካለህ? ካላደረክ ስለምን ለሰማዩ አምባገነን ሲሆን ቀዳህን አለሰለስክ? በአምባገነንነት የሚወዳደረው ስለሌለ? ከምድር አምባገነኖች በሞት ስለምታመልጥ? ከዛኛው አምባገነን የትም ስለማትሄድ? ለአምላክ ምስጋናውን ቀርቶ ነቀፋውም ሲበዛበት ነው። ያ በዛ ካምፕ ውስጥ የነበረው ይሁዲ '"If there is a God, he will have to beg for my forgiveness' ያለው ወዶ አይደለም። 'በአምላክ ተናደሃል?' በሌለ ነገር አልናደድም : የምናደደው አዕምሯችሁ ውስጥ በሰቀላችሁት የምናብ ተረት ነው። Join 👇 https://t.me/Jonahism
1 078
18
Sin texto...
657
19
ዕውቀታችን ግልብ ከሆነ፣ ድርሰታችን እንደዚያው ቀሊል ይሆናል… ለደራሲያን በሙሉ የምመክረው አንድ ነገር አለ፡፡ ንቃትም፣ ትጋትም ያጠጠበት ዘርፍ መስሎ የታየኝ ነገር ስላለ፡፡ ድርሰት ትልቅ ዝግጅትን
ዕውቀታችን ግልብ ከሆነ፣ ድርሰታችን እንደዚያው ቀሊል ይሆናል… ለደራሲያን በሙሉ የምመክረው አንድ ነገር አለ፡፡ ንቃትም፣ ትጋትም ያጠጠበት ዘርፍ መስሎ የታየኝ ነገር ስላለ፡፡ ድርሰት ትልቅ ዝግጅትን ይጠይቃል፡፡ ከዝግጅቶቹ አንዱና መሰረታዊው ዕውቀትን በመመልከት፣ ዙርያን በመቃኘት፣ በተለይ ደግሞ በማንበብና ያነበቡትን አጣጥሞ ራስን በመመርመር አዕምሮን ከልቡና ጋር ማዳበር ነው፡፡ ዝም ብለን፣ አንድ ቀን  ወፈፍ ጨምደድ ያደረገን ዕለት ተነስተን እስቲ ወደገበያ ልውጣ እንደሚባለው፣ እስቲ ድርሰት ልጻፍ አይባልም፡፡ ድርሰት ከባዶ ስለማይፈልቅ፣ ያለፉትን፣ የቀደሙትን፣ ዘመናትና ደራሲያን ድርሰቶችን ማንበብ ያስፈልጋል፡፡ ሳይ ይዞ ስርቆት፣ ቂም ይዞ ጸሎት በሚለው ላይ ስንፍ ይዞ ድርሰት የለም የሚለውን እጨምራለሁ፡፡ አፈታሪኩን፣ ተረታ ተረቱን፣ ሚቶሎጂውን፣ ሃይማኖታዊ መጻሕፍቱን፣ ታሪክን፣ ፍልስፍናን ማንበብ ለደራሲ የምርጫ ጥያቄ መሆን ያለበት አይመስለኝም፣ ሙያዊ ግዴታም፣ የሰብዓዊነት መርህም እንጂ፡፡ ዕውቀታችን ግልብ ከሆነ፣ ድርሰታችን እንደዚያው ቀሊል ይሆናል፡፡ ስለዚህ የንባብ ዋጋ ከመድረስ ዋጋ ቢበልጥ እንጂ አያንስምና ቀደምት ድርሰቶችን ዘርታችሁ ልታፈሩ ላሰባችኋቸው ድርሰቶች ግብዓት ይሁናችሁ፡፡ ዮናስ አድማሱ (ዶ/ር)፣ መድብለ ጉባኤ -የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ጉዞ፣ 2001 ዓ.ም
878
20
“ ለመከራ የተፈጠረ ትክሻ የአበባ ነዶ - ሳይቀር ያስጎነበስዋል ! © የአባ ልጅ !
“ ለመከራ የተፈጠረ ትክሻ የአበባ ነዶ - ሳይቀር ያስጎነበስዋል ! © የአባ ልጅ !
955