uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 064
Obunachilar
-224 soatlar
-77 kunlar
+130 kunlar
Postlar arxiv
የ2018 ዓ.ም የአዲስ ተማሪዎች ቅበላ ሂደት አፈጻጸም አተገባበር ምልከታ ተደረገ። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊና የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እና በቢሮው የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን በኮሌጆች በመገኘት የአዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎች የምዝገባ ሂደትን ጎብኝተዋል። የምዝገባ ሂደቱም በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን የተመለከቱ ሲሆን ዜጎች ግንዛቤ ተፈጥሮላቸው ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች መምጣታቸው የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው ምዝገባ ሊጠናቀቅ የቀረው ጊዜ አጭር በመሆኑ ያልተመዘገቡ እንዲመዘገቡ ጥሪ አስተላልፈዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

💡ተሰጥዎንና ፍላጎትዎን ወደማይነጥፍ ሀብት መቀየር ይፈልጋሉ? 🛠ሙያ የማይነጥፍ ሀብት ነው፡፡ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ደግሞ ፍላጎትና ተሰጥዎን ወደ ወደማይነጥፍ💰ሀብትነት ቀይረው ወደ ስኬት የሚወስድዎ አውራ ጎዳና ነው፡፡ #አድራሻችን ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወደ ኤርፖርት በሚወስደው መንገድ 150 ሜትር ላይ እንገኛለን

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ለተቀበላቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እና የኦረንቴሽን መድረክ አካሄደ:: ለሰልጣኝ ተማሪዎቹ በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ል ሀላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሲሆኑ በመልዕክታቸውም ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን መርጣችሁ እዚህ በመገኘታቸው እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ወቅቱ ሚጠይቀውን ምርጫ አውቃችሁ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለመሰልጠን ዘርፉን በመቀላቀላችሁ እጅግ እድለኞች ናችሁና እንኳን ደስ አላችሁም ብለዋል:: ለአዲስ ገቢ ሰልጣኝ ተማሪዎቹ ኦረንቴሽን የሰጡት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በቅድሚያ ሰልጣኞች የልዩ ክህሎት ባለቤት ወደሚያደርጋችሁ ኮሌጃችሁ እንኳን በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ለመሰልጠን እዚህ የተገኛችሁ ወጣቶች አሁን የምትገኙበት እድሜ በራሳችሁ ውሳኔ ምትወስኑበት እድሜ በመሆኑ ትክክለኛውና ጠቃሚውን መንገድ ለይታችሁ በመምረጥ የወጣትነት ጊዜያችሁን ውጤታማ ነገር ላይ እያሳለፋችሁ መሆኑን ከወዲሁ እርግጠኛ መሆን ይገባችኃልም ብለዋል:: የኮሌጁ ዲን አክለውም በኮሌጁ የትኩረት ዘርፍ ተብለው የተያዙና በዓለም ባንክ ፕሮጀክት ጭምር የሚደገፉ ሶስት የትኩረት ማዕከል የሆኑ የሙያ ዘርፎች መኖራቸውን ለሰልጣኞች ገልፀው እነርሱም የማኑፋክቸሪንግ ፣ የኤክትሪካል/እሌክትሮኒክስ እና የአውቶሞቲቭ ዘርፎች መሆናቸውን በመጥቀስ በእነዚህ ሶስት የትኩረት ዘርፎችን ምርጫቸው አድርገው ለሚቀላቀሉ ሰልጣኞች ከየትኛውም ዘርፍ በተለየ ሁኔታ እድለኞችና የላቀ ተጠቃሚ መሆናቸውንም በመድረኩ አብስረዋል:: በተጨማሪም ለአዲስ ገቢ ሰልጣኞች ስለ Psychometric Test አወሳሰድ ግንዛቤ የተፈጠረላቸው ሲሆን ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በቀጣዮቹ 3ቀናት በኮሌጁ በሚኖራቸው ቆይታ የህይወት ክህሎት(Life Skill) ስልጠና እንደሚወስዱ የተገፀ ሲሆን ጎን ለጎንም የPsychometric Test የሚውስዱ ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር  የሚገኙ ሶስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆችን ያቀፈ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ፡፡ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ  በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ባሳየው ከፍተኛ የስራ አፈፃፀምን ጨምሮ አጠቃላይ በኮሌጁ ባስመዘገባቸው ተጨባጭ ውጤቶች ጋር ተያይዞ በሀገሪቱ የሚገኙ በርካታ ኮሌጆች ለልምድ ልውውጥ ወደ ተቋማችን እየመጡ የሚገኝ ሲሆን በዛሬው እለትም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ አቃቂ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኮሌጅ ዲኖች እና የፕሮጀክት አስፈፃሚዎችን ጨምሮ ከአዲስ አበባ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የምክትል ቢሮ ሀላፊና በቢሮው የተለያዩ የስራ ሀላፊዎችን ያካተተ የልዑካን ቡድን በኮሌጃችን ተገኝተው የፕሮጀክት አፈፃፀም እና የስራ ልምድ ልውውጥ አካሂደዋል:: ልዑካን ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያሳየውን የላቀ የስራ አፈፃፀም ሂደትን በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ የነበረውን ሂደት እና ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገለፃና ማብራሪያም ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ በተደረገላቸው ገለፃና በተመለከቱት የኮሌጁ እንቅስቃሴ መነሻነት በነበረው ውይይት ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው በሚገኘው ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች መደነቃቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ በአጭር ጊዜ ያሳየው የላቀ የስራ አፈፃፀም በሌሎች አቻ ኮሌጆችም ጭምር ሞዴል ተደርጎ እንዲታይ ያስቻለው መሆኑንም ገልፀዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ የፕሮጀክቱን ማስተባበርያ ቢሮ እና በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን እዚህ በኮሌጁ ያገኟቸውን በርካታ ልምዶችንም ወደራሳቸው ወስደው ተግባራዊ በማድረግ እንደሚጠቀሙባቸውም ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ምዝገባ ላይ ነን#mamedire_official1 #xhaka34 #diredawapolytechniccollege

#ይምጡ... #ይሰልጥኑ... ዓለም አቀፋዊ ተፈላጊነትን ይላበሱ!!

ኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢንፍሌሽን እንዲቀንስ ማድረግ ችላለች! ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ አዲስ ምዕራፍ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ስልጠና ጥራትና አግባብነት፤ ተደራሽነትና ፍትሃዊነትን ለማሻሻል መሰረተ ሰፊ የሪፎርም አጀንዳዎችን ቀርፆ ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የዘርፉ የሪፎርም አዳዲስ እሳቤዎች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና መስኩን ሳቢ ለማድረግ እና ሀገራዊ የሥራ ገበያውንና የልማት ፍላጎቱን መመለስ እንዲያስችል ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ሪፎርሙን ተከትሎ በዘርፉ ወደ ሥራ ከገቡ ስርዓቶችና አሰራሮች መካከል ዲጂታላይዝድ በሆነ መልኩ የሚተገበረው የሳይኮሜትሪክ ምዘና አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ምዘናው በዋናነት ዘርፉን በአዲስ መልክ ለሚቀላቀሉ አዲስ ሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን ይህም ለሰልጣኞች፣ ለስልጠና ተቋማቱ እና ለሀገር ትልቅ አበርክቶ እንዳለው ታሳቢ ተደርጎ የተቀረፀ ስርዓት ነው፡፡ ምዘናው የሰልጣኞቹን ፍላጎቶት ብቻ ሳይሆን ተሰጥኦና ዝንባሌን መሰረት በማድረግ ውጤታማ ሊሆኑባቸው የሚችሉ የሙያ መስኮች እንዲመርጡ ያግዛቸዋል። ይህም ውድ ጊዜያቸውን ውጤታማ በማይሆኑበት የትምህርትና ስልጠና ዓለም ውስጥ እየማሰኑ እንዳያባክኑ ያደርጋል፡፡ ከዚህ ባሻገር የማሰልጠኛ ተቋማት የሰልጣኞች ምደባ ሥራቸውን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለመምራት፣ በኮሌጁ የአቋራጭ ምጣኔን ለመቀነስ እና መረጃ ላይ የተመሰረተ ውጤታማ የካውንስሊግ ሥራ እንዲሰሩ የማይተካ ሚና ይጫወታል፡፡ ከሁሉም በላይና ባሻገር ደግሞ የሥልጠና ጥራትና አግባብነት እንዲሁም ውጤታማነትን ከሥራ ገበያ ፍላጎቱ ጋር በማጣጣም ብቁ፣ በቂና ተወዳዳሪ ሰልጣኞችን በማፍራት እንደ ሀገር ለሥራ ገበያው ፍላጎት ምላሽ የሚሰጥ የቴክኒክና ሙያ ስርዓት ባለቤት እንድንሆን ያደርገናል፡፡ ይህም ምርትና ምርታማነትን በማሻሻልና ቅልጥፍና በመጨመር ሀገራዊ ተወዳዳሪነታችንን በሁሉም መስክ በማሳደግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ ያስችላል፡፡ ከዚህ ባሻገር የሥራ አጥነት ምጣኔን ትርጉም ባለው መልኩ ከመቀነስ አኳያም ሚናው የላቀ ነው፡፡ በዚህ አዲስ የሪፎርም እሳቤ መሰረት በፓይለት ደረጃ የተመረጡ የፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የ2018 የስልጠና ዘመን አዲስ የሰልጣኞች ቅበላቸውን በተቀመጠው አግባብ ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛል፡፡ የሳይኮሜትሪክ ምዘናውን መስጠት ከጀመሩ መካከልም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ደቡብ ወሎ ዞን የሚገኘው አንጋፋው የወ/ሮ ስኂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አንዱ ነው፡፡ ኮሌጁ እንዳስታወቀው ከጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ምዘናውን እየሰጠ ይገኛል፡፡ የሞጣ ፓሊክኒክ ኮሌጅም እንደ ወ/ሮ ስኂን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሁሉ ከጥቅምት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ምዘናውን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ክህሎት ለሁለንተናዊ እድገትና ውጤታማነት ነው! ጥቅምት 20/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: t.me/fdre_mols TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

#ምዝገባ ላይ ነን
#ምዝገባ ላይ ነን

🚨 ከመወሰንዎ በፊት፣ ደጋግመው ያስቡበት!መንገዶች ሁሉ ከአሰቡበት አያደርሱም! 🚫 ሕገ-ወጥ የሥራ ስምሪት ለከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ ለአካል ጉዳትና ሞት የሚያጋልጥ የጨለማ መንገድ ነው። ሕጋዊ የሥራ ስምሪት አማራጮችን ብቻ በመጠቀም መበት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትዎን ያረጋግጡ! ✈️ለህጋዊና ደህንነቱ ለተረጋገጠ የሥራ ስምሪት:- ✅በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ ይመዝገቡ(lmis.gov.et)፣ ✅የቅድመ ጉዞ ስልጠና ይውሰዱ፣ ✅ስለሚሄዱበት ሀገር በቂ መረጃ ይኑርዎት፣ ✅መበትና ግዴታዎን ጠንቅቀው ይወቁ፣ መነሻዎ ትክክል ካልሆነ መዳረሻዎ ፈፅሞ ትክክል ሊሆን አይችልምና በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ መሆን ሲያስቡ ህጋዊ አማራጮችን ብቻ ይከተሉ። 📞ለማንኛውም መረጃና ጥቆማ 👉9138 ነፃ የስልክ መስመርን ይጠቀሙ ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: t.me/fdre_mols TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

ፔትኮ ኢትዮጵያ ማብቃት ፕሮጀክት ከሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር ሶስት በፕላስቲክ መልሶ መጠቀም እና አንድ በወረቀት ቦርሳ ማምረት ዘርፍ የተደራጁ ማህበራት ድጋፍ ተደረገላቸው። በዚህም ከአስተዳደሩ ወረዳ አንድ እና ሁለት የተደራጁ ስራ ፈላጊ ወጣቶችና ሴቶች በፔትኮ ኢትዮጵያ ማብቃት የተዘጋጀላቸውን ስልጠና በመውሰድ እና የስራ ማስጀመሪያ ዕቃዎች ድጋፍ  እንዲሁም አልባሳት ርክክብ መደረጉ ታውቋል። በመርሃግብሩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እና በቢሮው የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሀ/ማርያም ተገኝተዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በአጠቃላይ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ https://lmis.gov.et የሚከናወነው ምዝገባ  እንቅስቃሴን አስመልክቶ ከወረዳ የአንድ ማዕከል ባለሙያዎች ጋር ውይይት አካሄደ። በዋናነት ምዝገባ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እሰከ አሁን የተመዝጋቢዎች ቁጥር የደረሰበት ደረጃ ተገምግሟል፤ በተለይም ስራ ፈላጊ፣ ስራ ያላቸው እና ኢንተርፕራይዞችን ምዝገባ በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የታየ ሲሆን በዚህም ሂደት የተመላከቱ ክፍተቶችን ለማስተካከልና በቀጣይ በሁሉም የወረዳ አንድ ማዕከላት ደረጃ ያለውን አፈጻጸም ለማሻሻል እንዲሁም ቁጥሩንም ከፍ ለማድረግ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ የሥራ ዕድል ፈጠራውን የተሳለጠ ለማድረግ የሚረዳው ይህ የዲጂታል ስርአት ተዘርግቶ ወደ ሥራ መገባቱ የሚታወቅ ሲሆን በዚህም ባለሙያዎቹ E-LMIS በዘርፉ ያመጣውን ለውጥ በመረዳት የምዝገባውን ውጤታማነት ለማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መግባባት መፈጠሩን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ