uz
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ko'proq ko'rsatish
1 064
Obunachilar
-224 soatlar
-77 kunlar
+130 kunlar
Postlar arxiv
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች እና የግል ኮሌጆች ላይ ኢንስፔክሽን አካሄደ። በዋናነት ኮሌጆቹ ህጋዊ የስልጠና ፍቃድ ያገኙባቸዉ የስልጠና ፕሮግራሞች፤ የንድፈ ሀሳብ እና የተግባር ምዘና በአግባቡ ስለመከናወኑ፤ ዉጤቶች በመመርያዉ መሠረት ሪፖርት ስለመደረጋቸዉ እንዲሁም የ2018 ዓ.ም ቅድመ ዝግጅት ስራዎች በተለይም የእቅድ ዝግጅት፤ የሰዉ ሀይል እና ግብዓት ማሟላታቸው ትኩረት ተሰጥቶበታል፡፡ በዚህም ኢንስፔክሽን ኮሌጆች የሚሰጡትን ትምህርትና ስልጠና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተሰጠ ስለመሆኑ በማረጋገጥ የሚታዩ ችግሮችን በቀጣይ በአጭር ጊዜ በማስተካከል እርማት እንዲወስዱ ታሳቢ ያደረገ ነው። የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ስለ ኢንስፔክሽኑ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናን ጥራት ለማምጣት ይህም ለዘርፉ እድገት አስፈላጊ በመሆኑ ጉዳዩ ትኩረት ተሰጥቶት መካሄዱን ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

አጫጭር ስልጠና ለሚሰጡ ተቋማት የ2018 ዓ.ም  የትምህርትና ስልጠናዉን ጥራት ስታንዳርድ ለማስጠበቅ  ክትትልና ድጋፍ ተደረገ፡፡ በዚህም ድጋፍና ክትትል የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት  የስልጠና ፍቃድ በተመለከተ በተሰጠው ፈቃድ ልክ እየሰሩ ስለመሆናቸውና ህጋዊ  ፈቃድ ሳይኖር ስልጠና የሚሰጥበት የሥልጠና ዘርፍ ላይ ማስተካከያ ለማድረግ በሚቻልበት እንዲሁም በእቅድ በመመራት ማሰልጠኛ ማንዋሎችና መሳሪያዎች በሚገባ መኖራቸውን ጨምሮ የአጠቃላይ ሰልጣኞችን መረጃ በማደራጀት ሰርተፍኬት የሚያገኙበትን አግባብ ተመልክቷል፡፡ በድጋፍና ክትትሉ ወቅትም ከተቋማቱ  ለኤጀንሲው  የሚቀርቡ   ቅሬታዎቸ፤  የሚሻሻሉ  አሰራሮችና  አሰተያየቶች የተሰጡ ሲሆን በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ እንደተናገሩት ይህ የድጋፍና ክትትል ልክ መደበኛ ስልጠና እንደሚሰጡ ተቋማት ሁሉ አጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማትም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ በመሆናቸው ትምህርትና ስልጠናው ጥራት ስታንዳርድ ለማስጠበቅ በቅርበት በመከታተል መደገፍ አስፈላጊነቱ  ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለአስተዳደሩ የሚዲያ አርሚ አባላት በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ። በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ ለሚዲያ አርሚዎች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ላይ በተለይም የ2018 ዓ.ም አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎች ቅበላን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ተዘጋጅቷል። በአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመድረኩ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የስልጠናውን አላማ አስመልክተው እንደገለፀት የዘርፉን አውድ የተረዳ እና የማህበራዊ ሚዲያ ቴክኒካል እውቀት ካለው የሚዲያ አርሚ ጋር በቅንጅት መስራት ውጤታማ የሚያደርግ መሆኑን አመላክተዋል። በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን በአስተዳደሩ የሚገኙ የሚዲያ አርሚዎች የአስተዳደሩን ነዋሪ ተጠቃሚ ለማድረግ ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ መረጃዎችን ለማህበረሰቡ ተደራሽነቱን ለማስፋት ባገኙት ግንዛቤ እንደከዚህ ቀደሙ በንቃት እንዲሳተፉ አሳስበዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

🇪🇹ሕልምዎን እውን ለማድረግ ትክክለኛውን መንገድ ይምረጡ! በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ሆነው ዓላማዎን ለማሳካት ትክክለኛ መረጃ ማግኘት ይኖርብዎታል። በርካታ ዜጎች ህጋዊና ደህንነቱ የተጨበቀ
🇪🇹ሕልምዎን እውን ለማድረግ ትክክለኛውን መንገድ ይምረጡ! በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ሆነው ዓላማዎን ለማሳካት ትክክለኛ መረጃ ማግኘት ይኖርብዎታል። በርካታ ዜጎች ህጋዊና ደህንነቱ የተጨበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት በማግኘታቸው መብትና ደህንነታቸው እንዲሁም ክብርና ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ችለዋል። ህጋዊ ያልሆነ ስምሪት መብትና ደህንነትዎን አደጋ ላይ የሚጥል አደገኛ መንገድ መሆኑን ያስተውሉ። እርስዎም በህጋዊ የሥራ ስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን ካሰቡ፤ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ፣ ከትክክለኛ የመረጃ ምንጭ ያግኙ! 9138 የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት የመረጃ ማዕከል ነፃ የስል መስመር ነው። ☎️ በ9138 ይደውሉ፡- 👉ስምሪቱ ህጋዊ መሆኑን ያረጋግጡ፣ 👉ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ያግኙ፣ 👉 አጠራጣሪ ጉዳዮችን ሪፖርት ያድርጉ #ህጋዊስምሪት #ደህንነቱየተጠበቀሥራ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: t.me/fdre_mols TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

የድሬዳዋ አሰተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በዛሬው ዕለት በቀበሌ 05 አስተዳደር ስር የሚገኙ የሶስት አቅመ ደካማ እናቶችን የፈራረሰ ቤት በአዲስ ገንብቶ አስረከበ። በሀገር አቀፍ ደረጃ በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶት እየተተገበረ ከሚገኘው የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ውስጥ አንዱ አቅመ ደካማ የሆኑ ዜጎችን መደገፍ ነው። በዛሬው ዕለትም በ05 ቀበሌ የሚገኙት እኚህ ቋሚ የገቢ ምንጭም ሆነ በአጠገባቸው የሚረዳቸው የሌለ፤ በፈረሰና ለመኖር እጅግ የሚከብድ ቤት ውስጥ በሚያሳዝን ሁኔታ እየኖሩ የሚገኙ እናቶች ናቸው። የሥራና ክህሎት ቢሮ ሠራተኞችና አመራሩ ይህን ችግር በመረዳት የሶስቱን እናቶች መኖሪያ  ቤት በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰርቶ በማጠናቀቅ ከአስፈላጊ የቤት ዕቃዎች ጋር የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ከንቲባ ክቡር አቶ ሀርቢ ቡህ፤ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዲሁም ሌሎች የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ርክክብ ተደርጓል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ማስታወቂያ ለዲግሪ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ!! በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የድሬደዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሳተላይት ካምፓስ በ2018 የትምህርት ዘመን በመደበኛው ከሚሰጣቸው ስልጠናዎች
ማስታወቂያ ለዲግሪ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ!! በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የድሬደዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሳተላይት ካምፓስ በ2018 የትምህርት ዘመን በመደበኛው ከሚሰጣቸው ስልጠናዎች በተጨማሪ በመጀመርያ ዲግሪ በምሽት (Extension) እና በቅዳሜ እና እሁድ (weekend) መርሃግብር፤ በAutomotive Technology: በConstruction Technology: በElectrical Electronics Technology: በGarment Technology እና በManufacturing Technology የቅበላ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾችን ለማሰልጠን ዝግጅቱን አጠናቆ ምዝገባ መጀመሩን በደስታ ይገልፃል::

ለዲግሪ ፕሮግራም ትምህርትና ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ
ለዲግሪ ፕሮግራም ትምህርትና ስልጠና ፈላጊዎች በሙሉ

#ዜና|ድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በራስ አቅም ያስጠናው የምሩቃን እና የስራ ገበያና ፍላጎት የጥናት ውጤት ሪፖርት የተለያዩ ባለድርሻ አካላቶች ባሉበት ቀረበ፡፡ ይህ ጥናት እንደ አስተዳደር እንዲሁም በኮሌጅ ደረጃ ያለብንን ክፍተት የለየና በቀጣይ በምን አይነት መልኩ ስራዎችን መስራት እንዳለብን ያሳየ ጥናት ነው ያሉት የኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ምክትል ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ ወጣቶችን አሰልጥኖ ማስመረቅ ብቻ ሳይሆን በሰለጠኑበት ሙያ ለሀገር እድገት አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችሉ ሰልጣኞችን ወደ ገበያው ማስገባትና ክትትል ማድረግ ይገባናል ሲሉ ም/ዲኗ በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም በዳሳ ጥናቱ የተገኙ ግብአቶችን እቅድ ውስጥ በማካተት የሚሰራ ይሆናል ።በመጨረሻም ለዚህ ጥናት መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላቶች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ጥናቱን አስመልክቶ የኮሌጁ ጥናትና ምርምር ቡድን መሪ የሆኑት ዶ/ር ሲሳይ አበራ እንደገለጹት ከዚህ ቀደም በኮሌጁ አቅም ተመሳሳይ ጥናት መደረጉን አስታውሰው አሁን የተጠናው ጥናት በራስ አቅም ማስጠናት መቻላችን በወጪ ረገድ ዋጋ ቆጣቢ የሆነና ከመረጃ ጥራት ጋር በትኩረት መስራት እንድንችል ያደረገ ሲሆን በቀጣይ ደግሞ ቴክኒክና ሞያ ኮሌጃችን ከኢንዱስትሪው ጋር የማስተሳሰር ስራ እንዲሁም ቀሪ ጥናቶችን ደግሞ ሁሉን አሳታፊ አድርገን የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም staff exchange የተገኘውን ተሞክሮ በአቶ ሽመክት ክፍሌ የቀረበ ሲሆን ከተሞክሮው አንጻር የተገኘው ልምድ ለድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም አካላቶች ተግባራዊ ቢደረግ ብዙ ለውጦች ማምጣት እና ሰልጣኞቻችን ከተለመደው የስልጠና አሰጣጥ በመቀየር ፕሮጀክት ላይ ትኩረት ባደረገ እና ኢንዱስትሪውን መሰረት ባደረገ መልኩ ስልጠናዎችን መስጠት እንድንችል ረድቶናል ብለዋል፡፡ በመድረኩ ላይም የሁለቱም ኮሌጆች ዲኖችና ም/ዲኖች እንዲሁም ፤የኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድ አባላቶች እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ተካፋይ ሆነዋል፡፡ ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ ለወቅታዊ ትኩስ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መረጃ You tube: Dire Dawa Polytechnic College(DDPTC) Facebook: https://web.facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute Telegram: t.me/Dire Dawa Polytechnic College TikTok: tiktok.com/@diredawapolytechnicollege

እንደ ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየተነቃቃ ከመጣው ኢንዱስትሪዎች የተነሳ የነፃ ንግድ ቀጠና፣ ደረቅ ወደብና ትልልቅ አቅም የሆኑ ተቋማት አየተፈጠሩ ስለሆነ ለሀገር ውስጥ ስራ ፈጠራ ትልቅ አቅም ሆኖልናል። አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ