uz
Feedback
ETHI-JAP GENERAL SECONDARY SCHOOL/ኢትዮ ጃፓን ህዳሴአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት Mana barumsaa Itiyoo Jaappaan Hiddaasee Sadarkaa 2ffaa waliiga

ETHI-JAP GENERAL SECONDARY SCHOOL/ኢትዮ ጃፓን ህዳሴአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት Mana barumsaa Itiyoo Jaappaan Hiddaasee Sadarkaa 2ffaa waliigalaa

Kanalga Telegram’da o‘tish

For students

Ko'proq ko'rsatish
1 864
Obunachilar
+124 soatlar
+67 kunlar
+3530 kunlar
Postlar arxiv
ቀን 28/9/2018 ማስታወቂያ ውድ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ ነገ ማለትም በ29/9/2018 የመፈተኛ አድሚሽን ካርድ ስለሚሰጥ ሁሉም ተማሪ በሰዓቱ (2:30) ተገኝቶ እንዲወስድ እያሳሰብን በሰቱ ተገኝቶ ያልወሰደ ተማሪ የማይስተናገድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን። ት/ቤቱ

ቀን 27/9/2018 ማስታወቂያ ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ ነገ ማለትም በ28/9/2018 በሞዴል ፈተና ዙሪያ አጠቃላይ ኦረንቴሽን ስለሚሰጥ ሁሉም ተማሪ በሰዓቱ ተገኝቶ የመፈተኛ ክፍሉን እንዲያውቅ ስንል በጥብቅ እናሳስባለን ። ት/ቤቱ

ቀን 19/9/2018 አስቸኳይ ማስታወቂያ ለት/ቤታችን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ በቅድሚያ ለሙስሊም ወንድም እህቶቻችን እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አለድሃ አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ነገ ማለትም በ20/9/2018 ሁለም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ የመፈተኛ አድሚሽን ካርድ በመውሰድ username ወደ ፈተና ዌብሳይት በማስገባት መስራት አለመስራቱን ማረጋገጥ የመጨረሻ ቀን መሆኑን በጥብቅ እንገልፃለን። ማሳሰቢያ ፦ ነገ መጥቶ አድሚሽን ካርድ ያልወሰደ እና username ያላረጋገጠ ተማሪ ለሚፈጠረው ችግር ሀላፊነቱን እራሱ ተማሪው መሆኑን ት/ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል ። ት/ቤቱ

ቀን 16/9/2018 ማስታወቂያ ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ነገ ማለትም በ17/9/2018 ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የሚመጡ አመራሮች የሰኞ before class አቴንዳንስ ቸክ ስለሚያደርጉ  ትምህርት የሚጀምረው ከጥዋቱ 1:30 መሆኑን  አውቃችሁ እስከ 1:45 ያልደረሰ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪ የማያስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን ። ማሳሰቢያ ፦ የቅዳሜ ማጠናከሪያ ላይ የቀራችሁ ተማሪዎች ያለ ህጋዊ መረጃ መደበኛ ትምህርት እንደማትስተናገዱ እንገልፃለን። - የነገው የሰኞ before class ላይም ያለ መረጃ የቀረ በተመሳሳይ እንደሚያስተናግድ እንገልፃለን።                         ት/ቤቱ

ቀን 14/9/2018 ማስታወቂያ ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ነገ ማለትም በ15/9/2018 ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የሚመጡ አመራሮች የቅዳሜ አቴንዳንስ ቸክ ስለሚያደርጉ  ትምህርት የሚጀምረው ጥዋት በተላለፈው መሠረት ከጥዋቱ 2:30 መሆኑን  አውቃችሁ እስከ 2:25 ያልደረሰ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪ የማያስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን ። ማሳሰቢያ ፦ ያለ ህጋዊ መረጃ የቀረ ተማሪ መደበኛ ክፍል እንደማይስተናገድ ቢሮው በደብዳቤ እንዳሳወቀን መግለፃችን ይታወቃል።                         ት/ቤቱ

ለ12ኛ ክፍል ተመሪዎች http://exam3.ethernet.edu.et በዚህ ሊንክ በመግባት ፓስዋርድ 1234 በመጠቀም የመለማመጃ ጥያቄዎችን መስራት ትችላላችሁ